Students Book - የተማሪዎች መጽሐፍ


Kanal geosi va tili: Efiopiya, Amharcha
Toifa: Ta’lim


አገር አቀፍ የተማሪዎች መማሪያ እና አጋዥ መጽሐፍት📚
📘መጽሐፍቶችን ለመጠየቅ
@StudentsBook_etbot መጠቀም ይችላሉ

Связанные каналы

Kanal geosi va tili
Efiopiya, Amharcha
Statistika
Postlar filtri


EBC Educational Program dan repost
✨የዩኒቨርሲቲ ምደባ ይፋ ሆነ

የ2013 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ አገር አቀፍ ፈተና ወስደው ለትምህርት ሚኒስቴር ተጠሪ በሆኑ መንግስት ዩኒቨርሲቲዎች በወጪ መጋራት የመግቢያ መቁረጫ ነጥብ ላመጡ ተማሪዎች ምደባ ተደርጓል።

በዚህም መሰረት ተማሪዎች ከዛሬ ጀምሮ የተመደቡበትን ዩኒቨርሲቲ ለማየት በድህረገፅ፡-https://result.ethernet.edu.et ፣
በSMS፡- 9444 እንዲሁም
በቴሌግራም፡- @moestudentbot መጠቀም ይችላሉ።

ተማሪዎች ከምደባ ጋር ተያይዞ ላላችው ማንኛውም ጥያቄ በድረገፅ https://complaint.ethernet.edu.et በማመልከት ጥያቄዎቻቸውን ማቅረብ ይችላሉ ተብሏል፡፡

ዩኒቨርሲቲዎች እስከ ሚያዝያ 24 ቀን 2014 ዓ.ም ድረስ ተገቢውን ዝግጅት አድርገው የመጀመሪያ ዓመት አዲስ ገቢ ተማሪዎችን የቅበላ መርሐ ግብር የሚያሳውቁ በመሆኑ ተማሪዎች አስፈላጊዉን ዝግጅት እንዲያደርጉም ሚኒስቴሩ ጥሪ አቅርቧል።

ከዚህ በፊት በተገለጸዉ የመቁረጫ ነጥብ እና ከኦሮሚያ፣ አማራ፣ አፋር እና ቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልሎች ተጨማሪ ተማሪዎች ምደባ የሚያስገኝላቸው ውሳኔ መተላለፉ ይታወሳል፡፡
@malefiyatube @malefiyatubebot


ለክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለትንሣኤ በአል በሰላም አደረሳችሁ!
@studentsbook_et @studentsbook_etbot


የከፍተኛ ትምህርት ተቋም የመግቢያ ነጥብ :

በተፈጥሮ ሳይንስ ፦

- ለወንድ 380 ፤ ለሴት 368

- ለታዳጊ ክልሎች ደግሞ ለወንድ 368 ለሴት 358

- ለአካል ጉዳተኞች ለወንድ 350 ፤ ለሴት 345

- ለአርብቶ አደሮች አካባቢዎች 358

- በትግራይ እና መተከል ለወንድ 358 ፤ ለሴት 350

በማህበራዊ ሳይንስ ፦

- ለወንድ 370 ፤ ለሴት ደግሞ 358

- ለታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢዎች ለወንድ 358 ፤ ለሴት 348

- ለአካል ጉዳተኞች ለወንድ 340፤ ለሴት 335

- በትግራይና መተከል ለወንድ 348 ፤ ለሴት 340

@studentsbook_et @stud3ntsbook_etbot


📌የ2012 ዓ/ም የ12ኛ ክፍል የሀገር አቀፍ ፈተናን ከግማሽ በላይ ተማሪዎች ከ350 በላይ ማምጣታቸው ተገለፀ።

የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ውጤትን በተመለከተ የሀገር አቀፍ ትምህርት ምዘናና ፈተናዎች ኤጀንሲ ለጋዜጠኞች መግለጫ ሰጥቷል።

የሀገር አቀፍ ትምህርት ምዘና እና ፈተናዎች ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር የሆኑት ዶ/ር ዲላሞ ኦተሪ የ2012 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና በተመዝጋቢ ፣ በተፈታኝም እንዲሁም በውጤትም ደረጃ ከፍተኛ መሆኑ ገልፀዋል።

ፈተናውን ከወሰዱ አጠቃላይ ተፈታኞች ውስጥ 55.7 ፐርሰንቱ ከ 350 በላይ አምጥተዋል።

በመግለጫው የፈተና ውጤት ከባለፈው አመት ጋር ሲነፃፀር የተሻለ መሆኑ የተገለፀ ሲሆን በዚህም ከ600 በላይ ያመጡ ተማሪዎች 702 መሆናቸው ተገልጿል።

የዓመቱ ከፍተኛ ውጤትም 669 ሆኖ መመዝገቡን ዳይሬክተሩ ተናግረዋል።

ተማሪዎችም ውጤታቸውን በፈተናዎች ኤጀንሲ ድረገፅ እንዲሁም በአጭር የፁሁፍ መልዕክት 8181 የፈተና መለያ ቁጥራቸውን በማስገባት ከነገ ጀምሮ ውጤታቸውን መመልከት እንደሚችሉ ተገልጿል።

ወደ ዩኒቨርሲቲ መግቢያ ጊዜን እና ማለፊያ ነጥብን በተመለከተ ከሳይንስ እና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ጋር እየተሰራ መሆኑን ዳይሬክተሩ በመግለጫው ማስታወቃቸውን ከትምህርት ሚኒስቴር ኮሚኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ያገኘነው መረጃ ይገልጻል።
@Studentsbook_et @Studentsbook_etbot


📌መልካም ፈተና

የ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ፈተና መሰጠት ተጀመረ።

የ2012 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ፈተና ከዛሬ ጀምሮ በመላ ኢትዮጵያ መሰጠት ተጀምሯል።

@Studentsbook_et @Studentsbook_etbot




📌የ12ኛ ክፍል ፈተና የካቲት 29 ይሰጣል።

የ12ኛ ክፍል ሃገር አቀፍ ፈተና የካቲት 29 ቀን 2013 ዓ/ም እንደሚሰጥ የትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ።

ከየካቲት 22 እስከ 24 ቀን 2013 ዓ.ም የዲጂታል መታወቂያ ይሰራጫልም ብሏል።

የፈተናው ገለጻ የካቲት 26 ቀን ተካሂዶ ፈተናው ከየካቲት 29 እስከ መጋቢት 2 ቀን 2013 ዓ.ም ድረስ እንደሚሰጥም ሚኒስቴሩ በሰጠው መግለጫ አስታውቋል፡፡

በቀጥታ (ኦንላይን) ይሰጣል ተብሎ የነበረው ፈተና በወረቀት እንደሚሰጥም የትምህርት ሚኒስትሩ ዶክተር ኢንጂነር ጌታሁን መኩሪያ ገልጸዋል፡፡

ፈተናው በወረቀት እንዲሰጥ ውሳኔ ላይ የተደረሰው ታብሌቶች ወደ ሀገር ውስጥ ባለመግባታቸው ነው።

👉ለተማሪዎች እንዲደርስ ሼር ማድረግ አትርሱ
@Studentsbook_et @Studentsbook_etbot




📌የትምህርት ዕድል በአሜሪካ - Scholarship

👉በአዲስ አበባ የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ ጥሩ ውጤት ያላቸው ተማሪዎች በ2021 EducationUSA Scholars Program (ESP) ፕሮግራም ላይ እንዲሳተፉ ጠይቋል። ለ20 ተማሪዎችም የስኮላርሺፕ እድል ተመቻችቷል።

👉ተማሪዎቹ አሁን ላይ የ12ኛ ክፍል ትምህርታቸውን እየተከታተሉ ያሉና በ10 ክፍል የሀገር አቀፍ ፈተና በSTEM ትምህርቶች (Mathematics, Biology, Chemistry, Physics, and English ) ''A'' ያመጡ መሆን አለባቸው ብሏል።

ለማመልከት https://bit.ly/3bUfoL4

👉ለተማሪዎች እንዲደርስ ሼር ማድረግ አትርሱ
@Studentsbook_et @Studentsbook_etbot


ለክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለጥምቀት በዓል በሰላም አደረሳችሁ።
@Studentsbook_et @Studentsbook_etbot


📌በአዲስ አበባ ለምትገኙ ተማሪዎች የወጣ የቅበላ ማስታወቂያ!

የገላን የወንድ ተማሪዎች 2ኛ ደረጃ አዳሪ ትምህርት ቤት እና የእቴጌ መነን የልጃገረዶች አዳሪ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎችን ለመቀበል ጥሪውን አውጥቷል።
@Studentsbook_et @Studentsbook_etbot


📌ለ12ኛ ክፍል ተማሪዎች

ቀሪ የጥናት ጊዜያቹን ወቅቱን ባማከለ ሁኔታ በተዘጋጁት የኦንላይን ፈተናዎች እራሳችሁን እንድታዘጋጁ አቅርበናል። ፈተናዎቹን በጥንቃቄ እንድትሰሩ እና መልስ በመጨረሻው ታገኛላችሁ።

🎁በትክክል ለሰሩ የማበረታቻ ሽልማት ይኖረናል!

1. Civics & Ethical Education 👇
https://youtu.be/543vSbex2NY?t

2. Economics 👇
https://youtu.be/_OynQN0qIYc?t

3. Biology 👇
https://youtu.be/eXfcuQZv-p0?t

4. Physics👇
https://youtu.be/Ucux2kROwDs?t

👉የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች መጽሐፍት ቻናል 👇
https://t.me/joinchat/AAAAAEpEdAodgurFZ5ppkw

👉ጥያቄዎች ለተማሪዎች በአግባቡ ይደርሱ ዘንድ ሼር እናድርግላቸው።

👇👇👇👇👇
ለተጨማሪ ትምህርት እና መጻሕፍት
@Studentsbook_et @Studentsbook_etbot


🎄እንኳን አደረሳችሁ🎄


📌የአማራ ክልል የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ውጤት ይፋ ሆነ

በኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ምክንያት ዘግይቶ በ2013 ዓ/ም በአማራ ክልል የተሰጠዉ የ2012 ዓ.ም የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ውጤት ይፋ ሆኗል፡፡

ለክልላዊ ፈተና ከተቀመጡ ተማሪዎች መካከልም 96.85 % ተማሪዎች ወደ ቀጣይ ክፍል ተዘዋውረዋል።

በዚህ አመት የተሻለ ውጤት የተመዘገበት መሆኑ ተገልጿል።

የፈተናዉ ውጤት ማለፊያ ነጥቡን በተመለከተ ለሁሉም ዞንና ከተማ አስተዳደር ትምህርት መምሪያዎች የተላለፈ ሲሆን ተማሪዎችም በየትምህርት ቤታቸው ውጤታቸውን በማየት የ9ኛ ክፍል ምዝገባ ከታህሳስ 30 ቀን 2013 ዓ.ም ጀምሮ እንዲያካሂዱ የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ አሳስቧል።
@Studentsbook_et @Studentsbook_etbot


📌በኦሮሚያ ክልል የስምንተኛ ክፍል የሚኒስትሪ ፈተና ውጤት ይፋ ሆኗል!

በክልሉ የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ከወሰዱ 446,907 ተማሪዎች ውስጥ 417,411 የሚሆኑት ወደ ቀጣይ ክፍል መሸጋገራቸውን የኦሮሚያ ክልል ትምህርት ቢሮ አስታውቋል።

በዚህም ከተፈታኞች ውስጥ 93.4% የሚሆኑት ማለፋቸው ነው የተነገረው። 29096 (6.6%) የሚሆኑ ተማሪዎች የተሰጠውን ፈተና ወድቀዋል ሲል አክሎ ገልጿል።

የተማሪዎች ነጥብም ለየዞኑ ትምህርት ቢሮዎችና ከተማ መስተዳድሮች በቴሌግራም መላኩ የተገለጸ ሲሆን እነሱም ለየወረዳ ትምህርት ቢሮዎች የሚያስተላልፉ ይሆናል። ትምህርት ቤቶችም የተማሪዎችን ውጤት ከእነርሱ ወስደው ለተማሪዎች ያስታውቃሉ ተብሏል።

በሚቀጥሉት ሳምንታት ውስጥም የ9ኛ ክፍል ትምህርት በክልሉ የሚጀመር ሲሆን የሚኒስትሪ ካርዶችን አትሞ የማሰራጨት ሥራም በአጭር ጊዜ ውስጥ ይሰራል ሲል የክልሉ ትምህርት ቢሮ አስታውቋል።
@Studentsbook_et @Studentsbook_etbot


Students Book - Grade 8 Resources dan repost
📌እንኳን ደስ አላችሁ!

በአዲስ አበባ ከተማ የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ውጤት ይፋ ሆነ

በአዲስ አበባ ከተማ የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ውጤት ይፋ መሆኑን የከተማ አስተዳደሩ ትምህርት ቢሮ ዛሬ አስታውቋል።

በኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ ምክንያት ዘግይቶ በ 2013 ዓ/ም በ156 መፈተኛ ጣቢያዎች ለ71,476 ተማሪዎች የተሰጠዉ የ2012 ዓ/ም የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ውጤት ይፋ ሆኗል።

ለፈተናው ከተቀመጡ ተማሪዎች መካከል 80 % ተማሪዎች ወደ ቀጣይ ክፍል መዛወራቸውን የአ/አ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ገልጿል።

የክልላዊ ፈተናዉ ውጤትም ለ10ሩም ክፍለ ከተማዎች ዛሬ ተሰራጭቷል።

ከነገ ማክሰኞ ጀምሮ ተማሪዎች ውጤታቸውን በየትምህርት ቤቶቻችው መመልከት ይችላሉ ተብሏል።
@Studentsbook_et @Studentsbook_etbot


📌የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ዝግጅት !

የትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ዶ/ር ገረመው ሁሉቃ ከኢ.ፒ.ድ ጋር በነበራቸው ቆይታ የሀገር አቀፉን የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተናን በተመለከተ ተከታዮቹን ነጥቦች አንስተዋል ፦

• በ2012 ዓ.ም የትምህርት ዘመን በኮሮና ምክንያት ፈተና ያልወሰዱ በአጠቃላይ 450 ሺህ የሚሆኑ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ዘንድሮ ፈተና ይወስዳሉ።

• ለፈተናው ብቻ የሚውል ቪሳት ሌሎች አጋዥ መሳሪያዎች ተገዝተው 1 ሺህ 184 ፈተና ጣቢያዎች ተቋቁመዋል።

• ለ270 ቴክኒሻኖች ስልጠና ተሰጥቷል።

• ለፈታኝ መምህራን 12ሺህ ላፕቶፖች ተዘጋጀቷል።

• 2 ትልልቅ ሰርቨሮችም በተገቢ ቦታ ላይ በመትከል ተማሪዎች እንዲለማመዱ ከ2008 እስከ 2011 ዓ.ም የተሰጡት የ12ኛ ክፍል ፈተናዎችም እዚያው ላይ ተጭነዋል።

• በትምህርት ሚኒስትሩ ዶ/ር ኢ/ር ጌታሁን መኩሪያ አማካኝነት በእርዳታ የተገኙ 450 ሺህ ታብሌቶች እስከ ታኅሣሥ 30 ቀን 2013 ዓ/ም ወደ አገር ውስጥ ገብተው ለፈተናው ይውላሉ።

• ፈተናውም ጥር 30 የሚጠናቀቅ ይሆናል።
@Studentsbook_et @Studentsbook_etbot


📌ወደ ትምህርት ቤት እንመለስ!

ሁላችንም በየአካባቢያችን ከትምህርት ቤት የቀሩ ተማሪዎች ወደ ትምህርት ቤት እንዲመለሱ ትምህርታቸውን እንዲከታተሉ የማድረግ ግዴታ አለብን!!

መምህራን ፣ ወላጆች ፣የትምህርት ተቋማት ሰራተኞች እና አጠቃላይ ማህበረሰቡ ንቅናቄውን ከፊት በመምራት ተማሪዎችን ወደ ትምህርት ቤት እንመለስ።
@Studentsbook_et @Studentsbook_etbot


📌የ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ፈተና እስከ ጥር መጨረሻ ድረስ ለመስጠት እቅድ ተይዟል:- ትምህርት ሚኒስቴር

የትምህርት ሚኒስቴርና የአገር አቀፍ ፈተናዎች ኤጀንሲ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ሀብትና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የ12ኛ ክፍል ፈተናን ዝግጅት በማስመልከት ማብራሪያ ሰጥተዋል።

የትምህርት ሚኒስትሩ ጌታሁን መኩሪያ (ፒ ኤች ዲ) 450 ሺህ ታብሌቶች እስከ ታህሳስ መጨረሻ ድረስ ከውጭ እንደሚገቡ እና 12 ሺህ ላፕቶፖች ደግሞ ለፈታኞች ለማከፋፈል ዝግጁ መሆናችውን ተናግረዋል።

በትምህርት ቤቶች ላይ ተተክለው ከሚኒስቴሩና የፈተናዎች ኤጀንሲ ሰርቨሮች ጋር የሚገናኙ 1 ሺህ 500 ቪሳት ቴክኖሎጂ ዝግጁ መሆናቸውን ገልጸዋል።

መሳሪያዎቹን የሚተክሉ 250 ባለሙያዎች ስልጠና ወስደው ወደ ሥራ ለመግባት ዝግጁ መሆናቸውን ተናግረዋል።

በኦንላይን የሚሰጠውን የ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ፈተና እስከ ጥር መጨረሻ ድረስ ለመስጠት እቅድ ተይዟል።

@Studentsbook_et @Studentsbook_etbot



20 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.

2 177

obunachilar
Kanal statistikasi