በቀጥታ ለአቶ እንዳልክ ዘነበ
ከኦርቶዶክስ ተዋህዶ በላይ የአማልክትን አምላክ ኢየሱስን ማን አከበረ ?
=============================================================
‹‹ ‹ቅል እንኳን ማንጠልጠያ አለው› የሚል የገረጀፈ ጸረ-ኢየሱስ የሆነ የመንደር ትርክት የምትነግሩኝ የዚህ መንደር የእሁድ ክርስትያች›› በማለት ዲያቆን ነበርኩ የሚል፣ምናልባትም ዲያቆን ሆኖ ‹‹እግዚኦ መሃረነ ክርስቶስ›› የሚለውን ብሎ የማያወቅ ሰው ነው ይሄን ያለን፡፡አሁን አሁን ፕሮቴስታንትነት ስለበዛ በእነሱ መንገድ የተሳብን እንጂ ስሙን እንዲህ ነበር የምንጠራው ‹‹ጌታችን አምላክችንና መድሃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ››፡፡ይሄን አጠራር ነው እንዳልክ የተባለው ሰው መንጠልጠያ እያለ አክብሩት የሚለንን የእየሱስን ስም አጠራር የሚያጣጥለው፡፡‹‹ ማንጣልጠያ የሚፈልገው ብቻውን ሙሉ ሆኖ መቆም ለማይችል ስም ነው›› ይለናል፡፡ ጨምሮም ‹‹ኢየሱስ የሚለው ስም ውስጥ መድሃኒት፣ጌትነት፣ስልጣን አለቅነት ገዢነትና ሀይል አለ›› በማለት የብራራል፡፡ በሌላ ጽሁፉ ደግሞ ‹‹በቀን ውስጥ ሳልጠራው የማልውለው ስም ኢየሱስ›› ይላል፡፡ እንዲሁም ፕሮቴስታንቶች በሚያዘዋውሩት አንድ ቪዲዮ ላይ ‹‹ከማንም የሀይማት ተቋም ውስጥ መወሸቅ እልፈልግም ›› ይለናል፡፡ እንግዲያው እኛ ኦርቶዶክስ ውስጥ ያለነው እውነት ስሆነ እንጂ ለመወሸቅ ፈልገን አይለም፡፡፣መጽሃፍ ቅዱስ ይዳኘን፡፡
የእንዳልክን መንጠልጠያ ስላቅ እንፈትሽ፡፡ በቲቶ 2፡13 ላይ ‹‹የአምላካችንንና የመድኃኒታችንን የኢየሱስ ክርስቶስ›› ይላል፣ 2ኛ ቆሮ 1፡2 ላይ ‹‹ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ››፣ ፊልሞና1፡25 ላይ ‹‹ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ›› ይላል፡፡እንዳልክ ግን እየሱስ ብቻ በሉ ይለናል፡፡ማንጠልጣያ ተጨማሪ አያስፈልገውም ይለናል፡፡ማንን እንከተል እንዳልክን ወይስ መጽሃፍ ቅዱስን? ምርጫው የእናንተ ነው፣ኦርቶዶክስ ግን መጽሃፍ ቅዱስን ነው የምትከተለው፡፡የእንዳልክ አይነቱ ለስሙ ዲያቆን ነበርኩ የሚል ማንጣልጣያውን ተው እያለ የኢየሱስ ክርስቶስን አምላክነት መድሃኒትንት ጌትንት በሥም አጠራሩ እንዳንመሰከር ይቃወመናል፡፡እኛ ግን መጽሃፍ ቅዱስን ሃዋሪያትን እንከተላለን፡፡የተወሸቅነው መጽሃፍ ቅዱስ ውስጥ ጌታችን አምላካችንና መድሃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ጉያ ውስጥ ነው፡፡ተቃዋሚዎቹ ጌታ አምላክ ክርስቶስን በዚህ መልኩ ስላከበርነው ይከፋቸዋል፡፡
በእርግጥ በፖለቲካ ላይ በሚያነሳው ትችቶች በመንግስት አይን ውስጥ የገባው እንዳልክ፣ከኦርቶዶክስ ጠሉ መንግስት እና ስርዓት ጋር ለመታረቅ ኦርቶዶክስን ማብጠልጠሉ አይገርምም፡፡ ግናስ ለጥቂት ቀናት ሲታሰር ባር ባር ያለው እንዳልክ በኢየሱስ ስም ሞት እንኳን ቢመጣ ማለቱ ቀድሞውኑ ኦርቶዶክስን የሚዘልፍ መች ሞት ይመጣበትና በሚል ስርዓቱ ኦርቶዶክስ ጠል ስለሆነ ተማማኖ ነው፡፡አይገርመንም፡፡ብዙ አባቶቻችን ስለ ክርስቶስ ብለው መስዋዕት ተቀብለዋል፣በኦርተዶክስ ለክርስቶስ ብሎ መከራን መቀበል አዲስ አይደለም፡፡
እንዳልክ ‹‹ኢየሱስ ጌታ ነው ስትባሉ በቀጥታ አሜን ማለት ሲገባችሁ›› እያለ ኦርቶዶክሳዊያንን ይዘልፋል፡፡የትኛውን ኢየሱስ እንደሚያመልኩ አትጠይቁ ዝም ብለችሁ አሜን በሉ ይለናል፡፡መጽሃፍ ቅዱስ 1ኛ ዮሐ 4፡1 ላይ ግን እንዲህ የለናል ‹‹ ወዳጆች ሆይ፥ መንፈስን ሁሉ አትመኑ፥ ነገር ግን መናፍስት ከእግዚአብሔር ሆነው እንደ ሆነ መርምሩ፤ ብዙዎች ሐሰተኞች ነቢያት ወደ ዓለም ወጥተዋልና።›› ይለናል፡፡ እንዳልክ ግን መንፈስን ሁሉ እመኑ ይለናል፡፡ማቴ 24፡24 ላይ ሀሰተኛ ክርስቶሶች እንደሚነሱ ይነግረናል፡፡ሰዎች በአዕምሯቸው ሀሰተኛ ክርስቶስ ቢያስነሱ እንኳን አሜን በሉ ይለናል ዲያቆን ነኝ የሚለው እንደልክ፡፡2ኛ ቆሮ 11፡13-14 ላይ ‹‹እንደ እነዚህ ያሉ ሰዎች የክርስቶስን ሐዋርያት እንዲመስሉ ራሳቸውን እየለወጡ፥ ውሸተኞች ሐዋርያትና ተንኮለኞች ሠራተኞች ናቸውና።ይህም ድንቅ አይደለም፤ ሰይጣን ራሱ የብርሃንን መልአክ እንዲመስል ራሱን ይለውጣልና።›› ሀሳዊያን የክርስቶስን ሃዋሪያ የሚመስሉት እነዚህ ሰዎች የሚሰብኩትም ክርስቶስ ሀሳዊ ነው፣ባይሆንማ ሀሳዊያን አይባሉም፡፡የእነሱን ሀሳዊ ክርስቶስ ስም ሲነሳ እንኳን አሜን በሉ ሳትጠይቁ ይለናል እንዳልካቸው ዘነበ፡፡
እየሱስ ጌታ ነው እያልኩ እኖራለሁ ይላል እንዳልክ፣መጽሃፍ ቅዱስ ደግሞ ‹‹ጌታ ሆይ፥ ጌታ ሆይ፥ የሚለኝ ሁሉ መንግሥተ ሰማያት የሚገባ አይደለም።›› ይላል ትዕዛዛቱን የሚፈጽም እና ህይወቱን ከሚኖር ውጪ፡፡
[
https://www.facebook.com/endalkachew.zenebe.71/posts/887366125580438](https://www.facebook.com/endalkachew.zenebe.71/posts/887366125580438)
[
https://www.facebook.com/endalkachew.zenebe.71/posts/870399150610469](https://www.facebook.com/endalkachew.zenebe.71/posts/870399150610469)
[
https://www.facebook.com/endalkachew.zenebe.71/posts/478538026463252](https://www.facebook.com/endalkachew.zenebe.71/posts/478538026463252)
[
https://www.facebook.com/photo/?fbid=5121802881258024&set=a.104410396330656](https://www.facebook.com/photo/?fbid=5121802881258024&set=a.104410396330656)
[
https://www.facebook.com/watch/?v=2979223162222134](https://www.facebook.com/watch/?v=2979223162222134)