ሚሊዮኖች የሚታደሙበትን የህዳር 21 አክሱም ፂዮን ዓመታዊ ክብረ በዓል መሰረት አድርጎ የተዘጋጀው የዓመቱ አራተኛ የካምፒንግ ጉዟችን ከህዳር 18-21 ለአራት ቀናት ሊካሄድ ነው።
መነሻችን ህዳር 18 ከጠዋቱ 01:05 ከቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ሲሆን ፤ ከ 1:30 ሰዓት በረራ በኋላ ከጠዋቱ 2:35 መቀሌ ከተማ በሚገኘው አሉላ አባ ነጋ አየር ማረፊያ በመድረስ የዓመቱ ታላቁ ጉዟችንን እንጀምራለን።
👉በአራቱ ቀናት ቆይታችን ከባሕር ጠለል በላይ በ2,580 ሜትር ከፍታ ላይ የሚገኘው እጅግ አስገራሚው የገርዓልታ አቡነ ይምዓታ ፍልፍል ዋሻ ቤተ መቅደስ ፣ ጥንታዊ ታሪክ ያላቸው ቆርቆር ማሪያም ፣ አቡነ ዳንሄል ፣ አቡነ ገብረ ሚካኤል ቆራሮ ፣ ዮሐንስ ማህቁዲ ፣ ደብረ ፂዮን አቡነ አብርሃም ፣ አብርሃ ወሓፅብሃ ፣ ማሪያም ውቅሮ እንዲሁም ሌሎችም ጥንታዊ እና ታሪካዊ አብያተ ክርስቲያናት እና ገዳማትን የምንጎበኝ ይሆናል። እንዲሁም ህዳር 20 ወደ ጥንታዊቷ የ አክሱም ከተማ በማምራት የአክሱም ፂዮን ዓመታዊ ክብረ ዓልን ከዋዜማው ጀምሮ እስከ ዋናው የህዳር 21 ክብረ በዓል ድረስ የምንታደም ይሆናል።
ይህ ታሪካዊ ጉዞ በፍፁም እንዳያመልጣችሁ !!
👉 በዚህ ጉዞ የሚሳተፉ ተጓዦች ብዛት በቁጥር 15 ብቻ ይሆናሉ።
ቀድሞ የተመዘገበ ከልዩ ቅናሽ ጋር ፤ ቀድሞ ይስተናገዳል !!
ለተጨማሪ የጉዞ መረጃዎች እና ምዝገባ በተከታዮቹ የስልክ አድራሻዎች ያገኙናል።
👉 +251964423971 ፣ +251942545470 እንዲሁም በቴሌግራም
@guzoadwahiking ,
@guzoad ,
@miki_2012 ያገኙናል ።
#ethiopia #landoforigins #guzoadwahiking #tigrai #axum #gheralta #abuneyemata