CALVARY gospel ministry


Kanal geosi va tili: Efiopiya, Amharcha
Toifa: Sotish


"But we preach christ crucified, unto.
The jews a stumblingblock, and unto the Greeks foolishness;"
1corinthians 1: 23
☎️ 0989929053 addis ababa
☎️ 0910058808 addis ababa
☎️ 0982031334 addis ababa
☎️ 0989929052 hawassa

Связанные каналы

Kanal geosi va tili
Efiopiya, Amharcha
Toifa
Sotish
Statistika
Postlar filtri








Calvary group members dan repost
Video oldindan ko‘rish uchun mavjud emas
Telegram'da ko‘rish


46 በመቶ ምዕመናን ብቻ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ የሰጠውን 'ታላቁ ተልዕኮ' እንደ ‘አደራ’ እንደሚያዩት አንድ ጥናት ገለጸ፡፡
በማቴዎስ ወንጌል ምዕራፍ 28፡19 ላይ ‘“ስለዚህ ሂዱና ሕዝቦችን ሁሉ በአብ፣ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ስም እያጠመቃችኋቸው ደቀ መዛሙርት አድርጓቸው፤” የሚለውን ጌታ ኢየሱስ የሰጠውን ታላቁን ተልዕኮ በተመለከተ በመጋቢዎችና በሌላው ምዕመን መካከል ሰፊ የአመለካከት ልዩነት እንዳለ ባርና የተባለ አጥኚ ተቋም ያወጣው አዲስ መረጃ አሳይቷል፡፡
በዚህ ጥናት ውጤት መሰረት ታላቁ ተልዕኮ ለሁሉም ክርስቲያን የተሰጠ አደራ መሆኑን 85 በመቶ መጋቢዎች ሲያምኑ ከምዕመናኑ ግን 46 በመቶዎቹ ብቻ ተልዕኮው የሁሉም አማኝ 'አደራ' እንደሆነ ያምናሉ ብሎዋል፡፡
ሚሽን ኢንዲያ ከተባለ ተቋም ጋር በመተባበር የተደረገው ይህ የባርና አዲስ ጥናት ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ የሰጠ 'ታላቁ ተልዕኮ” የማን ሃላፊነት ነው? እና በምን አይነት መልኩ ሊተገበር ይገባል? በሚለው ላይ የቤተክርስቲያን መጋቢዎችንና የሌላውን ምዕመን ግንዛቤ ለማወቅ የተደረገ ሲሆን በርካታ መጋቢዎችና ምዕመናን ተካተውበታል፡፡
የጥናቱ ትንታኔ እንደሚያሳየው በአገልጋዮችና በሌላው ምዕመን መካከል ያለው ይህ ሰፊ የአመለከከት ልዩነት ለምን እንደተከሰተ የቤተክርስቲያን መሪዎች ሊፈትሹት ይገባል ብሏል፡፡
የቤተክርስቲያን መሪዎች ምዕመናኑ ይህንን ተልዕኮ በተገቢው ሁኔታ እንዲረዱትና ተሳትፏቸው በምን መልኩ ሊሆን እንደሚችል እንዲገነዘቡ ማስተማር እንዳለባቸው ጥናቱ ጠቁሟል፡፡


" ኢየሱስ ክርስቶስ ከሙታን በመነሣቱ ለሕያው ተስፋና ለማይጠፋ፥ እድፈትም ለሌለበት፥ ለማያልፍም ርስት እንደ ምሕረቱ ብዛት ሁለተኛ የወለደን የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አምላክና አባት ይባረክ፤ ይህም ርስት በመጨረሻው ዘመን ይገለጥ ዘንድ ለተዘጋጀ መዳን በእምነት በእግዚአብሔር ኃይል ለተጠበቃችሁ ለእናንተ በሰማይ ቀርቶላችኋል።"
(1ኛ የጴጥሮስ መልእክት 1:3-5)


አንድ ሰው ስለ ሕዝብ ይሞት ዘንድ ይሻላል። ዩሐ ፲፰፥፲፬
ስለ ሁላችን በደል በመስቀል ላይ ዕርቃኑን ያደረ፣ሐጢያታችንን ያጠበ፣ነቀፌታችንን ያስወገደ የእግዚአብሔር ልጅ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው!!
ይህ ቀን የእኔ ና የእናንተ ድህነት መሠረት ቀን ነው። አንዱ ስለ ሁሉ ሞተ፤ሐጢያት የሌለበት ሐጢያት ሆኖ ተቆጠረ።
ከዚህ የበለጠ ፍቅር ለማንም እንደሌለው፣የፍቅርን ምንነት፣የፍቅርን ጥግ አሳወቀን ኢየሱስ ቤዛ ሆኖ ሞተልን።
ራስን በመግዛት፣በፀሎትና በመንፈስ መመላለስ ይሁንልን አሜን።




ኢየሱስ ይመጣል

(የዮሐንስ ራእይ ምዕ. 22)
----------
20፤ ይህን የሚመሰክር። አዎን፥ በቶሎ እመጣለሁ ይላል። አሜን፥ ጌታ ኢየሱስ ሆይ፥ ና።

21፤ የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋ ከሁላችን ጋር ይሁን፤ አሜን።

ስለዚህ እናንተ በእርሱ ስራ
👉ከጨለማ ወደ ሚደነቅ ብርሃኑ የተጠራችሁ
👉ቅዱሳን
👉ለእርስቱ የተለየ ወገን የሆናችሁ

የእርሱን በጎነት እንድትናገሩ ተጠርታችኃል ይህም በመስቀል ላይ ዋጋ ከፍሎ ፍቅር ግድ ብሎት ከሰማያት ወርዶ እኛን ያደነበትን የተሰቀለውን ክርስቶስን እንድትሰብኩ ነው።

(1ኛ የጴጥሮስ መልእክት ምዕ. 2)
----------
9፤ እናንተ ግን ከጨለማ ወደሚደነቅ ብርሃኑ የጠራችሁን የእርሱን በጎነት እንድትናገሩ የተመረጠ ትውልድ፥ የንጉሥ ካህናት፥ ቅዱስ ሕዝብ፥ ለርስቱ የተለየ ወገን ናችሁ፤

10፤ እናንተ ቀድሞ ወገን አልነበራችሁም አሁን ግን የእግዚአብሔር ወገን ናችሁ፤ እናንተ ምሕረት ያገኛችሁ አልነበራችሁም አሁን ግን ምሕረትን አግኝታችኋል።

በዚህ ወንጌል፦
👉ወገን ያልነበርነው የእግዚአብሔር ወገን
ሆነናል
👉ምህረት ያላገኘን የነበርን ምህረት
አግኝተናል
👉በበደላችን ሙታን የነበርን በእርሱ ስራ
ህይወትን አግኝተናል
👉ከእግዚአብሔር ርቀን የነበርን በእርሱ ስራ
ቀርበናል
👉ልጆች ተደርገናል
👉ቤዛነታችንን አግኝተናል
👉እግዚአብሔር ርስታችን ሆኗል
👉በመንፈሱ ታትመናል
👉ጨለማ የነበርን ብርሃን ሆነናል .....

ይህን በጎነቱን በስፍራ ሁሉ በቤተሰቦቻንን በትምህርት ቤት በስራ ቦታ በጎረቤት በአደባባይ ... እናውራ ሙሽራው ኢየሱስ ይመጣል ለዘላለም ከእርሱ ጋር ሊያኖረን ይወስደናል። ከዚህ የሚበልጥ ምን ደስታ አለን።

ስለዚህ እርሱ ለአንድ ነፍስ መዳን ወዶ ይታገሳልና ያንንም የማስታረቅ ቃል በአንተ በአንቺ ውስጥ አኑራልና ወንጌልን በስፍራ ሁሉ በመስበክ እንዲሁም ሙሽራውን በሚጠባበቅ በተዘጋጀ ህይወት በመኖር ጌታ ሆይ ና ማራናታ እንበል።

ሉቃስ 12
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
³⁷ ጌታቸው በመጣ ጊዜ ሲተጉ የሚያገኛቸው እነዚያ ባሪያዎች ብፁዓን ናቸው፤ እውነት እላችኋለሁ፥ ታጥቆ በማዕድ ያስቀምጣቸዋል ቀርቦም ያገለግላቸዋል።
³⁸ ከሌሊቱም በሁለተኛው ወይም በሦስተኛው ክፍል መጥቶ እንዲሁ ቢያገኛቸው፥ እነዚያ ባሪያዎች ብፁዓን ናቸው።
³⁹ ይህን ግን እወቁ ባለቤት በምን ሰዓት ሌባ እንዲመጣ ቢያውቅ ኖሮ፥ በነቃ፥ ቤቱም እንዲቆፈር ባልፈቀደም ነበር።
⁴⁰ እናንተ ደግሞ ተዘጋጅታችሁ ኑሩ፥ የሰው ልጅ በማታስቡበት ሰዓት ይመጣልና።

በኢየሱስ ስም አናፍርም የተሰቀለውን ኢየሱስን በስፍራሁ ሁሉ እንጠራለን እንሰብካለን መዳን በሌላ በማንም የለምና።

እየሱስ ይመጣል
CALVARY EVANGELISM


በአሜሪካ በኮነቲከት ግዛትም የታገዘ ራስን ማጥፋት ሕጋዊ ለማድረግ የተዘጋጀው ረቂቅ ህግ ድጋሚ ውድቅ መደረጉ ተነግሯል፡፡
ላይፍ ኒውስ እንደዘገበው 5B 88 የሚል ስያሜ የተሰጠው ይህ ህግ ባለፈው መጋቢት ወር በግዛቱ የህዝብ ጤና ኮሚቴ በኩል ያለፈ ሲሆን ረቂቅ ህጒ ወደ ዳኝነት ኮሜቴ እንዳይሄድ የታገዘ ራስን ማጥፋት ሎቢ ቡድን ጥረት ቢያደርግም ህጉ በዳኞች ኮሜቴ ታይቶ ውድቅ እንዲሆን ተደረጓል ተብሏል፡፡
በተመሳሳይ ዜና የታገዘ ራስን ማጥፋት መፈቀድን በተመለከተ ሊደረግ የነበረን ህዝበ ውሳኔ የጣሊያን ፍርድ ቤት ማገዱም ተሰምቷል፡፡
ዘ ክርስቲያን ቱዴይ እንደዘገበው በመሞት መብት መከበር ላይ ህዝበ ውሳኔ እንዲደረግ ከ 750 ሺ በላይ ጣልያናዊያን የድጋፍ ፊርማ የተሰበሰበበት አቤቱታ የቀረበ ቢሆንም ፍርድ ቤቱ ውድቅ አድርጎታል፡፡
የጣሊያን የህገመንግስት ፍርድ ቤት ግን ጥያቄው በህገመንግስት የተቀመጠውን አስፈላጊን የሰው ልጅ ህይወትና ለደካሞችና ለአደጋ ለተጋለጡ ሰዎች የሚደረግ ዝቅተኛ ጥበቃን አያከብርም ብሏል፡፡
የካቶሊኩ ሊቀ ጳጳስ ፖፕ ፍራንሲስ ይህንን ረቂቅ ህግ ‘ተቀባይነት የሌለው የግድያ ህግ ‘በማለት ተችተውት የነበረ ሲሆን ድርጊቱ ሰብአዊም ክርስቲያናዊም አይደለም ብለውታል፤የህገመንግስታዊው ፍርድ ቤት ህጉን ውድቅ በማድረጉ አድናቆታቸውን አግኝቷል፡፡
በጣሊያን ህግ አንድ ሰው እራሱን እንዲያጠፋ የሚረዳ ማንኛውም ሰው ከአምስት እስከ 12 አመት እስራት ይጠብቀዋል።


በኢንዶኔዥያ አንድ ክርስቲያን ዩቲዩበር የ10 አመት እስራት ተፈረደበት።
ክርስትያን ዩቲዩበሩ የ10 አመት እስራት የተፈረደበት አብዛኛ ሙስሊም በሆነባት ኢንዲኔዥያ ሰዎችን ያስከፋ ነው የተባለን ቪዲዮ በዮቲዩ ቻናሉ ላይ በመለጠፉ ነው ተብሏል።
መሀመድ ካሴ የተባለው ቀድሞ የእስልምና እምነት ተከታይ የነበረውና እ.ኤ.አ. በ2014 ወደ ክርስትና በመጣው በዚህ ሰው ላይ በኢንዶኔዥያ ምዕራብ ጃቫ በሚገኘ ፍርድ የ10 አመት እስር የፈረደበት የቀድሞ እምነቱን የሚተች ቪዲዮ በዩቲዩብ ቻናሉ ሲጭን ነበር ተብሎ ነው።
ክርስቲያን ቱዴይ እንደዘገበው መሀመድ ካሴ በእስር ቤት ውስጥ በሙስና ክስ ተይዞ በነበረ ናፖሊዮን በተባለ የፖሊስ ባለስልጣን ድብድባና ስቃይ የደረሰበት ሲሆን በኢንዶኔዥያ በርካታ አብያተ ክርስቲያናት የአምልኮ ቤቶች ግንባታ ለማደናቀፍ ከሚሞክሩ ቡድኖች ተቃውሞና እንግልት የሚደረሰባቸ መሆኑም ይነገራል።


Video oldindan ko‘rish uchun mavjud emas
Telegram'da ko‘rish








ካልቨሪ ቻሪቲ: Calvary Charity
AGAPE KINDERGARTEN
✟ ✞ ✟

እንደምን ሰነበታችሁ የካልቨሪ ቤተሰቦች በያላችሁበት የእግዚአብሔር አብ ሰላም የክርስቶስ ፍቅር የመንፈስ ቅዱስ አብርሆት ይሁንላችሁ።

ካልቨሪ የወንጌል አገልግሎት ለብዙዎች የምስራቹን ቃል በጎዳና፣ እንዲሁም በsocial median አና በተለያዩ መንገዶች የሚያደረስ ከመሆኑም ባለፈ ሁለንተናዊ አገልግሎትን ባቀፈ መልኩ የተለያዩ የእርዳታ ሥራዎችን በመስራት ላይ ቆይቷል። አቅመ ደካማ ከሆኑት ቤተሰቦች ከ80 በላይ ህፃናት ልጆች የመዋዕለ ህፃናት(KG) ትምህርት እድል ባሉበት ስፍራ (መንደር) እንዲያገኙ ባሰባሰብናቸው አስፈላጊ የትምህርት ቁሳቁስ (ደብተር ፤ እርሳስ... ወዘተ) ጋር ሁለተኛውን ሴሚስተር ማስጀመራችንን ስንገልፅ በታላቅ ደስታ ነው።

ስለሆነም ለዚህ መልካም ስራ የተባበራችሁ ሁላችሁም ስለመልካም ልባችሁ በወረዳውና በአከባቢው ነዋሪ እንዲሁም በካልቨሪ ሚኒስትሪ ስም ምስጋና እያቀረብን ይህ መልካምነት ሳይቋረጥ ቀጥሎም ለሚያስፈልጉት ሰፊ ሥራዎች የበኩላችሁን እድታደርጉ እናሳስባለን።
----------------------------------
ለበለጠ መረጃ 👇👇
-Addis Ababa
Biruk +251910058808

-Hawassa
Amanuel +251989929052
----------------------------------
(መጽሐፈ ምሳሌ 19:17)
ለድሀ ቸርነትን የሚያደርግ ለእግዚአብሔር ያበድራል፥ በጎነቱንም መልሶ ይከፍለዋል።


CALVARY HOLISTIC MINISTRIES

@calvarygospelministry


ቲቶ 2
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹¹ ሰዎችን ሁሉ የሚያድን የእግዚአብሔር ጸጋ ተገልጦአልና፤
¹²-¹³ ይህም ጸጋ፥ ኃጢአተኝነትንና ዓለማዊን ምኞት ክደን፥ የተባረከውን ተስፋችንን እርሱም የታላቁን የአምላካችንንና የመድኃኒታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ክብር መገለጥ እየጠበቅን፥ ራሳችንን በመግዛትና በጽድቅ እግዚአብሔርንም በመምሰል በአሁኑ ዘመን እንድንኖር ያስተምረናል፤
¹⁴ መድኃኒታችንም ከዓመፅ ሁሉ እንዲቤዠን፥ መልካሙንም ለማድረግ የሚቀናውን ገንዘቡም የሚሆነውን ሕዝብ ለራሱ እንዲያነጻ፥ ስለ እኛ ነፍሱን ሰጥቶአል።
¹⁵ ይህን በሙሉ ሥልጣን ተናገርና ምከር ገሥጽም፤ ማንም አይናቅህ።


“ወንጌልን ብሰብክ እንኳ የምመካበት የለኝም፤ ግድ ደርሶብኝ ነውና፤ ወንጌልንም ባልሰብክ ወዮልኝ።”
— 1ኛ ቆሮንቶስ 9፥16


ወደ ኢየሱስ ተጠጋ!

አለም ካከበረው ኢየሱስ ያከበረው ይበልጣል ምክንያቱም ሰዎች ውጪህን ያያሉ ጌታ ግን ልብህን ያያል፤ ከኢየሱስ ጋር ስትጣበቅ ጉድለት የለም፤ ሰዎች መረጋጋትህን አይተው ያከብሩሀል፤ ሳር ቅጠሉ ላንተ ያጎነብሳል፤ ከምንም በላይ ህሊናህ ከዚህ አለም ጭንቀትና ፍርሀት በሰላም ያርፋል።

መዝናናት ጊዜያዊ እረፍት ይሰጥህ ይሆናል፤ ከሰዎች ጋር ስትቀላቀል ችግርህን ለጊዜው ትረሳው ይሆናል፤ ግን ወዳጄ የዚህን አለም አድካሚ ሸክም ከአይምሮህ የምታወርደው ወደ ኢየሱስ ስትጠጋ ብቻ ነው!


በሰይጣን ክለብ እንዲሳተፉ ለተማሪዎች የቀረበ ግብዣ
በአሜሪካ ኤሌኖይስ የሚገኙ ወላጆች ለልጆቻቸው በትምህርት ቤት የሰይጣን ክለብ ውስጥ እንዲሳተፉ የሚጋበዝ ጥሪ መቅረቡን ተከትሎ ቁጣቸውን እየገለጹ እንደሚገኙ ካሪስማ ኒውስ ዘገበ፡፡
በኤሌኖይስ ግዛት ሞሎኒ የሚገኘው የጃን አዳምስ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ከ 1ኛ እስከ 5ተኛ ክፍል ለሚማሩ ህጻናት ከትምህርት በኋላ በሰይጣን ክለብ እንዲሳተፉ የሚጋብዝ በራሪ የመጥሪያ ወረቀት እንዲደርሳቸው ከተደረገ በኋላ የተማሪዎቹ ወላጆች ተቃውሟቸውን ገልጸዋል፡፡
በሰይጣን አምልኮ ተከታይ ቡድኖች በሚዘጋጀው በዚህ ክበብ ላይ ተማሪዎቹ እንዲሳተፉ የሚጋበዘው ይህ መጥሪያ ‘ ስላም ልጆች፤ከትምህርት ሰዓት በኋላ በሰይጣን ክለብ በመሳተፍ የደሰታ ጊዜ ይኑረን’ የሚል መልክት ያዘለ ነው ተብሏል፡፡
በዚህ ጉዳይ ላይ ወላጆች በትምህርት ቤቱ ላይ ተቃውሞዋቸውን ያቀረቡ ሲሆን ድርጊቱ ሃገራችን በምን አይነት የጥፋት መንገድ ላይ እንዳለች የሚያሳይ ነው በማለት ተናግረው የትምህርት ቤቱ አስተዳደር ቦርድ በአዲስ ግብረገብና ስነምግባር ባላቸው ሰዎች እንዲተካ ጥያቄ አቅርበዋል፡፡
የትምህርት ቤቱ አሰተዳደር በበኩሉ የትምህርት ቤቱን አቅርቦት በመጠቀም መስራት በሚፈለጉ የትኛውም አይነት ቡድኖች መካከል መድልዖ እንደማያደርግና ሁሉም የሃይማኖት ድርጅቶች በእኩል እንደሚያሰተናግድ ግልጾ ለዚህም ማሳያ የሚሆነው በወንጌል ስርጭት ላይ የሚሰራ ጉድ ኒውስ የተባለ ክለብ በትምህርት ቤቱ ውስጥ እንደሚገኝና አሁን ደግሞ የሰይጣን መቅደስ የተሰኝ ድርጅት በትምህርት ቤቱ ውስጥ ክለብ ለመመሰረት እንደተፈቀደለት ተናግሯል፡፡
ሰይጣን በድብቅና በማታለል ሳይሆን እንዲህ በግልጽ መስራት መጀመሩ የዘመን ፍጻሜ ላይ ለመድረሳችን አንዱ ማሳያ ነው፤ ክርስቲያኖች እንትጋ፡፡

20 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.

1 647

obunachilar
Kanal statistikasi