✟የማለዳ ፀሀይ✟


Kanal geosi va tili: Efiopiya, Inglizcha


✝️የተወደዳችሁ ወንድሞቼ እህቶቼ ይህ ቻናል የተከፈተበት ዋናው ምክንያት ህልውናችን የሆነችውን የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ያልተመረመሩና ያልተነገሩላትን ታላላቅ እውቀቶቿን እና ትምህርቶቿን ለመማማር ነው።
ስለዚህም በእግዚያብሔር ስም ይህን ቻናል ለኦርቶዶክሳዊያን እውቀቷን ለሚሹ ቤተሰቦቻችሁ share በማድረግ ሁላችንም እንማማር ሀይማኖታችንን እንወቅ።👇
@ewkete_orthodox
@ewkete_orthodox

Связанные каналы

Kanal geosi va tili
Efiopiya, Inglizcha
Statistika
Postlar filtri


✝ በእውነትም እግዚአብሔር እኛን የወደደን ከመፈጠራችን በፊት ነው ስለሆነም ፈጠረን ። ስለዚህ የእኛ ሕልውና እግዚአብሔር ለእኛ ያለው ፍቅር ፍሬ ነው እኛ የእርሱ የሕሊናው አሳቡና የልቡ ደስታ ሆነን ነበርንና ።

" ፍቅርም እንደዚህ ነው እግዚአብሔር እርሱ ራሱ እንደ ወደደን ስለ ኃጢአታችንም ማስተሰሪያ ይሆን ዘንድ ልጁን እንደ ላከ እንጂ እኛ እግዚአብሔር እንደ ወደድነው አይደለም ። " [ 1ኛ ዮሐ 4*10 ]

አብነ ሺኖዳ ሣልሳዊ








Video oldindan ko‘rish uchun mavjud emas
Telegram'da ko‘rish


Video oldindan ko‘rish uchun mavjud emas
Telegram'da ko‘rish


"በሰው ላይ የምንመለከተው የእግዚአብሔር መልክ ነው። የእኛ ሰዓሊ ሲስለን እርሱን እንድንመስል አድርጎ ነው፡፡ የእርሱን ውበት በእኛ ውስጥ ይሰራዋል፡፡

በቀለም ፋንታ በተለያየ መንፈሳዊ በጎነት ያሳምረናል፤ የእግዚአብሔር ምስልና መልክም ከምንም ነገር ጋር ስለማይነጻጸር ሰውም ይህ እውነተኛ መልኩ በመሆኑ ከሌሎች ምድራዊ ነገሮች ጋር አይቀላቀልም፣... ተፈጥሯችንን ያስዋበ እግዚአብሔር ከተጠቀመበት ብሩሽ አንዱ #ፍቅር ነው።

#ቅዱስ_ጎርጎርዮስ_ዘኑሲስ


ንስሐ
በቅዱስ ኤፍሬም

ተወዳጆች ሆይ ኑ አባቶቼና ወንድሞቼ እግዚአብሔር ለርስቱ ለመንግሥቱ የለያችሁ ምእመናን ሆይ ኑ፡፡ የልጅነትን ማኅተም ያለባችሁ የክርስቶስ ወታደሮች ሆይ ኑ፡፡ ልጆቼ ይኽን ለነፍሳችን ድኅነት እግዚአብሔር ያዘጋጀውን ትምህርት ትማሩ ዘንድ ኑ፤ ጊዜ ሳለልን እንመካከር ዘንድ ኑ፡፡ ኑ ዘለዓለማዊ ሕይወትን ገንዘብ እናድርግ፡፡ ነፍሳችንን እንገዛት ዘንድ እንቻኮል፡፡

ዓይነ ልቡናችን ብሩህ ይኾን ዘንድ ኑ በዕንባ እንታጠብ (እናልቅስ)፡፡ ባለጸጋዉም ድኻዉም፣ ልዑላንም ሕዝቦችም፣ ወጣቶችም ጐረምሶችም፣ ሽማግሎችም ሕፃናትም፣ በአጣቃላይ ጣዕመ መንግሥተ ሰማያትን መውረስ ከምረረ ገሃነም መዳን የምትሹ ሁላችሁም ኑ፡፡

ከክቡር ዳዊት ጋር ሆነን ምሕረቱ የበዛ ባለጸጋውን እግዚአብሔርን “ነጽረኒ ወስምዓኒ እግዚኦ አምላኪየ" አቤቱ ፈጣሪዬ ልመናዬን ሰምተኽ በዓይነ ምሕረትህ እየኝ፤ ተመልከተኝ፡፡ "አብርሆን ለአዕይንትየ ከመ ኢኑማ ለመዊት" የሞት እንቅልፍ እንዳያንቀላፉ ዓይኖቼን አብራቸው” ብለን እንለምነው /መዝ.13፥3-4/፡፡ ከመንገድ ዳር ተቀምጦ ይለምን እንደነበረው እንደ ዓይነ ስዉሩ ሰውም፡- “ተሣሃለኒ ኢየሱስ ወልደ ዳዊት" የዳዊት ልጅ ኢየሱስ ሆይ ማረኝ” ብለን እንጩኽ/ማር.10፥48/፡፡ ዝም እንል ዘንድ የሚቈጡን ቢኖሩም እንደ በርጠሜዎስ ልጅ እንደ ጠሜዎስ ዓይነ ልቡናችንን እስኪያበራልን ድረስ አብዝተን ወደ ብርሃን ክርስቶስ እንጩኽ፡፡ ስለዚኽ ወደ ክርስቶስ እንቅረብ፤ ብሩህ ልቡናንም ገንዘብ እናድርግ፡፡ ገጻችንም ከቶ አያፍርም፡፡ ኑ! ሃይማኖትንና ምግባርን አንድም ልጅነትን መንግሥተ ሰማያትን ለመያዝ እንሩጥ። ይኽን ያደረግን እንደኾነም የዚህ ዓለም ነገር ከንቱ ሆኖ ይታየናል፡፡ ስለዚህ ራሳችንን ንቁ እናድርግ፤ በዐሥራ አንደኛው ሰዓት ላይ ብንመጣም አይዘጋብንምና ኑ እንፍጠን፡፡ ምሽቱ ቀርቧል፤ ለኹሉም እንደየሥራው የሚከፍለው ልዑለ ባሕርይ ኢየሱስ ክርስቶስም ሊመጣ ነው፡፡
@ewkete_orthodox
@ewkete_orthodox


በአንድነቱ ምንታዌ በሦስትነቱ ርባዔ በሌለበት በሥላሴ ስም ረድኤተ እግዚአብሔርን አጋዥ በማድረግ የምሉዓ ጸጋ እስጢፋኖስን ዜና መጻፍ እጀምራለሁ




አባ ጽጌ ድንግል

ቀዳሜ ሰማዕት ወሊቀ ዲያቆናት ቅዱስ እስጢፋኖስ ቀድሞ ከመምህሩ ከገማልያ ትንቢት የተነገረለትን ሱባዔ የሚቆጠርለትን መሲሕ ሲሰማ አደገ በኋላም ከመጥምቀ መለኮት ከቅዱስ ዮሐንስ ዮሐ 1፥19 የሚለውን የመጥምቁን ቃል በሰማ ጊዜ የቃሉን ትምህርት የእጁን ተዓምራት ለማየት የነበረውን ጉጉት እስከ ሞት ድረስ ሊታመነው ወዶ ተከተለው።
ለብሉያት አዲስ ያልነበረው መጋቤ ብሉይ እስጢፋኖስ የሐዲስ ኪዳን መግቢያ introduction ከመጥምቁ ዘልቆ የሐዲስ ኪዳን ትምህርቱንም ከሊቀ ሊቃውንት ኢየሱስ ክርስቶስ በቃልና በኑሮ ተማረ።

የመጀመሪያዎቹ ጳጳሳት ሐዋርያት የምዕመናኑን በዘርና በቋንቋ መከፋፈል ዐይተው ለዚያም ምክንያት የነበረውን የመዓድ ጉዳይ የሚያስተባብሩ መንፈስ ቅዱስ የሞላባቸው ሰባት ዲያቆናትን ሲመርጡ በምግባር በሃይማኖት ያጌጠውን በትምህርቱም ጣዕም ወደር የሌለውን አይሁድን በአፍ በመጻፍ አፍ የሚያሲዘውን እስጢፋኖስን ሊቀ ዲያቆናት አድርገው ሾሙት።

የስምንት ሺህ ምዕመናን አባት ሆኖ በአንደበቱና በሕይወቱ ወንጌልን ፤ በደግነቱ ምድራዊ መዓድን እያበላና እያጠጣ የምዕመናንን አንድነት እጅግ አጠነከረው።

ለምቀኝነት አያርፉም የተባለላቸው አይሁድ የአስጢፋኖስን የአገልግሎቱን ርቀት የአዕምሮውን ምጥቀት ተመልክተው በቅናት ተነሳሱበት ፤ የሀሰት ምስክር አቁመው በሸንጎ ፊት አቆሙት የሶስና በሀሰት ክስ ሸንጎ ፊት መቆም ሲማር ያደገው መጋቤ ብሉይ እስጢፋኖስ ለሚጠይቁት ሁሉ መልስ እያሳጣ የተነገረውን ትንቢት የተመሰለውን ምሳሌ መንፈስ ቅዱስን ተሞልቶ ይናገር በጀመረ ጊዜ መልኩ የእግዚአብሔርን ልጅ ይመስል ነበር ይለናል ጸሐፊው ቅ/ሉቃስ እርሱም እኔን ምሰሉ ያለውን ጌታ በምግባር መስሎት እንደነበር እናስተውላለን። ሐዋ 6፥15

እንግዲህ ይኼኔ ነው በአፍ በመጻፍ መልስ ቢያሳጣቸው ጊዜ ልማዳቸው የሆነው አይሁድ እስከ በወዲያኛው ሊሰናበቱት ማኅበሩንም ሊበትኑ እስጢፋኖስን ከከተማ ውጪ አየጎተቱ ይዘውት ወጡ መጠን አልባ ጥላቻቸውንም የድንጋይ ማዕበል በማዝነብ ይወጡበት ጀመር እርሱ ግን ሰማያት ተከፍተው የእግዚአብሔርን ልጅ በቀኝ ቆሞ ያይ ነበር የሚያዘንቡበት የድንጋይ ዝናብ እንዳለ ሊቁ እንደ ገለባ ይመስለዋል በክርስቶስ መዓዛ ፍቅር ታውዷልና ቀኑን ሙሉ ሊገደል ወደደ። ሮሜ 8፥36 ለገዳዮቹም ኦ አባ ሥረይ ሎሙ እስመ በዘኢየአምሩ ይገብሩ አባት ሆይ የሚያደርጉትን አያውቁምና ይቅር በላቸው ሐዋ 7፥60 ብሎ ወዳጆቻችንን መውደድ ላቃተን ለእኛ ጠላቶቹን ወዶ አምላኩን መምሰልን አስተማረን።

ጌታ ኢየሱስም መንፈስ ቅዱስ የሞላበትን በሕይወቱ እስከ ሞቱ እርሱን የመሰለውን ፤ ከእርሱ ጋር በአንድ መቅደስ የተራዳውን ገባሬ ሰናይ ዲያቆን ብሎ ሲጣራ በሰማ ጊዜ ከባሕርይ አባቱ ቀኝ ቆሞ ተቀበለው በሰማያዊ አክሊልም አጌጠው እስከ ሞት ድረስ በመታመን የመጀመሪያ የሆነውን (ቀዳሜ ሰማዕት) በሰማያት በሰማያዊ ማዕረግ አኖረው።


ሰኔ 21 የቤተ ክርስቲያን ልደት የሆነባት የሕንጻ ቤተ ክርስቲያን በዓል ነበረች። በዚያች እለት ዲያቆኑ እስጢፋኖስ የኪዳኑን ጸሎት እንደጨረሱ ከሐዲስ ኪዳኑ ሊቀ ካህናትና ከሊቀ ሐዋርያት ጴጥሮስ ጋር ገባሬ ሰናይ ዲያቆን ሆኖ ሊቀድስ ገባ በአማናዊቷ ምስራቅ በድንግል ማርያም ፊትም ቆሞ ወደ ምስራቅ ተመልከቱ ይል ነበር።

እስጢፋኖስ ሆይ ከአማናዊቷ መቅደስ ጋራ ወደ መቅደስ በገባህ ጊዜ ምን አስተዋልክ ፤ በአማናዊቷ መንበር ላይ መስዋዕቱ ሲቀርብ ምን ምስጢር ተረዳህ ፤ ማዕጠንቱን ይዘህ ፍሕም በጨመርክባት ሰከንድ ምን ቅኔ ደረደርክ ፤ ወደ አማናዊቷ መቅደስ ወደ አማናዊቷ ታቦት ስግዱ ባልክባት ደቂቃ እንዴት አይነት ስግደት ሰገድክ። ከቅዳሴው ፍጻሜስ በኋላ ወደ እርሷ ቀርበህ ምን ምስጢር አደላደልክ ምን ቅኔ ደረደርክ ፤ አባቴ ሆይ ይህንንስ ኃጢአት ባደቀቀው ሰውነቴ ምስጢር በራቀው አዕምሮዬ ምግባር በራቀው ስብዕናዬ ልረዳው አልችልምና እንዲያው እጹብ ብዬ ልመለስ።

መጋቢያችን በዘር በቋንቋ ለተከፋፈለች የመዓድም ነገር ለጨነቃት ጉባዔ ኢትዮጵያ ትደርስላት ዘንድ ማንን ሐዋርያ ልለምን ጴጥሮስን ነው ዮሐንስን?

በከመ ጸሐፈ ጳውሎስ እንዘ ይብል ሠናየ መልእክተ፤ ናሁ ዘራዕኩ ለውዳሴከ ሕጠተ፤ እርር ሊተ እስጢፋኖስ ፍሬ ከናፍርየ ዘንተ፤ በዘርዐ ሰብእ በሥጋሁ የዐርር ሞተ፤ ወዘዘርዐ በመንፈሱ የዐርር ሕይወተ።



ዲ/ን ዘ፲፪
ጥቅምት 16 2014
@ewkete_orthodox
@ewkete_orthodox


+ አቤቱ ቅጣኝ ነገር ግን እንዳታዋርደኝ! +

እግዚአብሔር ፍቅር ነው ፣ መሐሪ ነው ፣ ይቅር ባይ ነው፡፡ ፍቅር ይቆጣል ወይ? ይቅር ባይስ ይቀጣል ወይ? ብዙዎቻችን ስለ ክርስቶስ ሲነገረን መሐሪነቱና ፍቅሩ ብቻ ቢነገረን አንጠላም፡፡ ጨርሶ የማንፈራው እግዚአብሔር እንፈልጋለን፡፡ እንዲህ አታድርግ! የሚለን ሲመጣ ‘አትፍረድ’ እንላለን ፤ ቆይተን ግን የሰማዩን ዳኝም አትፍረድ ማለት ይቃጣናል፡፡ ቅጣት የሌለበት ክርስትና እንሻለን፡፡

ይህ ዓይነቱን ክርስትና ‘ጣፋጭ ክርስትና’ {የስኳር ክርስትና ይሉታል} ምንም ምሬት የሌለበት ሁሌም ማር ማር የሚል ሕይወት አድርገው ክርስትናን የሚሰብኩም ብዙ ናቸው፡፡ ‘አይዞህ ብትታመም ትፈወሳለህ ፣ ቤትህ ይሞላል ፣ ቀዳዳህ ይደፈናል ፣ ብትበድልም አትቀጣም’ ብቻ የሚሉ ስብከቶች የስኳር ክርስትና ስብከቶች ናቸው፡፡ ይህንን ብቻ የሚያጮሁ ሰዎች ክርስቶስ ‘የምድር ጨው ናችሁ’ ያለውን ትተው የምድር ስኳር ለመሆንና ዓለምን ለማስደሰት የሚፈልጉ ናቸው፡፡
በእርግጥ እግዚአብሔር ይቆጣል ወይ? አዎን ይቆጣል! እንዲህ ይላል መጽሐፉ

‘እግዚአብሔር ቀናተኛና ተበቃይ አምላክ ነው እግዚአብሔር ተበቃይና መዓትን የተሞላ ነው እግዚአብሔር ተቃዋሚዎቹን ይበቀላል፥ ለጠላቶቹም ቍጣውን ይጠብቃል። በቍጣው ፊት የሚቆም ማን ነው? የቍጣውንም ትኵሳት ማን ይታገሣል? መዓቱ እንደ እሳት ይፈስሳል፥ ከእርሱም የተነሣ ዓለቶች ተሰነጠቁ’ ናሆ 1፡1፣6
‘‘ከቍጣው የተነሣ ምድር ትንቀጠቀጣለች አሕዛብም መዓቱን አይችሉም’’ ኤር 10፡10
‘‘እኛ በቍጣህ አልቀናልና፥ በመዓትህም ደንግጠናልና’’ መዝ. 90፡7

እግዚአብሔር በተቆጣ ጊዜ የሚመልሰው የለም፡፡ ቅዱሳን የቁጣውን መጠን ስለሚያውቁ በትሕትና ይለምኑታል፡፡

ይሁንና መጽሐፍ ቅዱስ ስለ እግዚአብሔር ቁጣ ደጋግሞ ቢነግረንም አንድ ሌላ ደስ የሚያሰኝ ነገርም ነግሮናል፡፡ የእግዚአብሔር ቁጣው ለዘላለም አይደለም፡፡ "ምሕረቱ ለዘላለም ነውና" ይላል እንጂ "ቁጣው ለዘላለም ነውና" አይልም:: የእግዚአብሔር ቁጣ ጊዜያዊ ነው፡፡

‘መሐሪ ነኝና ለዘላለም አልቆጣም’ ኤር 3፡12
‘ቁጣው ለጥቂት ጊዜ ሞገሱ ግን ለሕይወት ዘመን ነው’ መዝ 29፡5
‘ጌታ ለዘላለም አይጥልም ቢያሳዝንም እንደ ምሕረቱ ብዛት ይራራል ፤ የሰው ልጆችን ከልቡ አያስጨንቅም አያሳዝንምም’ ሰ.ኤር 3፡31

የፈጣሪን የነነደ የቁጣ እሳት ማጥፋት የሚቻለን በዕንባ ነው፡፡ በደላችንን አምነን ቅጣት ይገባናል ነገር ግን መሐሪ ነህና ማረን ማለት ይገባል፡፡ ንጉሥ ዳዊት ‘አቤቱ በቁጣህ አትቅሠፈኝ በመዓትህም አትገሥፀኝ’ ብሎ የፈጣሪን ቁጣ አበረደ፡፡ /መዝ 38፡1/ ነቢዩ ኤርያስም ‘አቤቱ ቅጣኝ ነገር ግን እንዳታዋርደኝ በመጠን ይሁን እንጂ በቁጣ አይሁን’ ብሎ ተለማመጠ፡፡ ኤር 10፡24

አንድ ሠዓሊ በጣም ብዙ ደክሞ የተጠበበትን ሥዕሉን የፈለገ ቢበሳጭ ለረዥም ጊዜ ያንን ሥዕል ለመሳል የተጠበበትን ጥበብ አስቦ ሥዕሉን ወደ እሳት አይጨምረውም፡፡ አባ ጊዮርጊስ እንዲህ ሲል ይለምናል ‘ሠዓሊ ሥዕሉን ያጠፋል ወይ? [ጌታ ሆይ እኔን ስትፈጥር የተጠበብክበትን] የቀደመ ጥበብህን አስብ እንጂ! አስበህም ማረኝ! [ያጠፋዖኑ ለሥዕሉ ሠዓሊ ፤ ኪነተከ ዘትካት ኀሊ]

ይቅርታውን በንስሓ ለሚለምኑ ሁሉ ምሕረቱ ቅርብ ነው፡፡ በቀኝና በግራው ወንበዴዎች በተሰቀሉበት በዕለተ አርብ የግራው ወንበዴ ሲሰድበው ጌታ መልስ አልሠጠም፡፡ የቀኙ ወንበዴ ማረኝ ሲለው ግን ከአፉ ተቀብሎ በገነት ትሆናለህ አለው፡፡ ቁጣው የራቀ ምሕረቱ የበዛ እርሱ የራበው ሰው ለምግብ የሚቸኩለውን ያህል ይቅር ለማለት ይቸኩላል፡፡ ‘ምሕረትን ይወድዳልና ቁጣውንም ለዘላለም አይጠብቅም ተመልሶ ይምረናል ፤ ክፋታችንንም ይጠቀጥቃል ፤ ኃጢአታችንንንም በባሕሩ ጥልቅ ይጥለዋል’ ሚክ 7፡18

ልጆች ሳለን ጥፋት ስናጠፋ ከወላጆቻችን እንደበቃለን፡፡በተደበቅንበት ሰዓት ውስጣችን በፍርሃት ይርዳል፡፡ ‘ዛሬ ገደለኝ’ ‘ዛሬ መሞቴ ነው’ ብለን እንጨነቃለን፡፡ የሚደርስብንን ቅጣት እጅግ አጋንነን ከመፍራታችን የተነሣ መሬት ተሰንጥቃ ብትውጠን አንጠላም፡፡ በዚያ ሁሉ ጭንቀት ውስጥ ግን ወላጆቻችንም እስኪያገኙን ይጨንነቃሉ፡፡ እግዚአብሔርም እንዲህ ነው፡፡ አጥፍቶ በገነት ዛፎች መካከል የተሸሸገ አዳምን ወዴት ነህ ብሎ የፈለገ እርሱ እኛንም ይፈልገናል፡፡ አዳም ከገነት ሳይባረር ገነት ውስጥ እንደጠፋ ፈጣሪ ሳያባርረን ራሳችንን በኃጢአት ተሸማቅቀን ያባረርን እኛን ይፈልገናል፡፡ እርሱ ስለመጥፋትህ ይጨነቃል አንተ ‘ዛሬስ አይምረኝም’ ትላለህ፡፡

የሚገርመው በጥፋታችን ከተደበቅንበት ወላጆቻችን ካገኙን በኋላ ሁለተኛው ዙር ጭንቀታችን ‘ምን አጥፍተህ ነው የተደበቅከው’ መባል ነው፡፡ ጥፋታችንን ሲያውጣጡን እንንቀጠቀጣለን፡፡ ያጠፋነውን ስለምናውቀው ስንት እንደሚያስገርፈንም እናውቀዋለን፡፡ ‘ብትናገር ይሻላል? ግዴለህም!’ ብለው አግባብተውም አስፈራርተውም ወላጆቻችን ጥፋታችንን ያውጣጡናል፡፡ እየፈራን ያጠፋነውን ጥፋት ስንናዘዝ ግን ወላጆቻችን በጥፋታችን ቅጥል ብለው ‘አልመታህም ተናገር’ ያሉንን ረስተው የዱላ ዝናም ያዘንቡብናል፡፡ እግዚአብሔር ግን ጥፋትህን ስትነግረው ቁጣው የሚገነፍል አባት አይደለም፡፡
’’ኃጢአታችንን ብንናዘዝ ኃጢአታችንን ይቅር ሊለን ከዓመፃም ሁሉ ሊያነፃን የታመነና ጻድቅ ነው’ 1ዮሐ 1፡9

ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ


#መስከረም_29

#ሰማዕት_ቅድስት_አርሴማ

በዚችም ቀን ከቅድስት አርሴማና ከእመምኔቷ ከአጋታ ጋር ደናግል በሰማዕትነት አረፉ። ይህም እንዲህ ነው በከሀዲው ዲዮቅልጥያኖስ ዘመን እርሱ መልኳ ውብ የሆነ ብላቴና ድንግል ሊአገባ ሽቶ በየሀገሩ ሁሉ ሒደው መርጠው ያመጡለት ዘንድ አሽከሮቹን አዘዘ።

ይችንም የሚመስላት የሌለ ቅድስት አርሴማን በሮሜ አገር በአንድ የደናግል ገዳም ውስጥ አገኙዋት። ሥዕሏንም ሥለው ለንጉሥ ዲዮቅልጥያኖስ ላኩለት ንጉሡም ሥዕሏን በአየ ጊዜ እጅግ ደስ አለውና ለሠርግ እንዲመጡ ወደ መኳንንቱ ላከ።

እሊያ ደናግልም ይህን ነገር በአወቁ ጊዜ ይረዳቸው ዘንድ ድንግልናቸውንም ይጠብቅ ዘንድ አልቅሰው ወደ እግዚአብሔር ለመኑ። ከዚህም በኋላ ተነሥተው በሥውር ሸሹ የንጉሥ ድርጣድስ ግዛት ወደ ሆነ ወደ አርማንያ ሀገርም ደርሰው በአንድ ቦታ ተቀመጡ ከእርሳቸውም ጋር የተሰደዱ ቁጥራቸው ሰባ አምስት የሆነ ወንዶች፣ ሴቶችም ሠላሳ ዘጠኝ የሆኑ ከእርሳቸው ጋራ አሉ። ምግባቸውን አያገኙም ነበርና በታላቅ ችግር ውስጥ ኖሩ ከእነርሱም መብራት የምትሠራ አንዲት ሴት ነበረች ከእርሷም የእጅ ሥራ ከሚገኘው በየጥቂቱ ይመገባሉ።

ንጉሥ ዲዮቅልጥያኖስም የከበረች አርሴማን በፈለጋት ጊዜ አላገኛትም ግን በአርማንያ አገር እንዳለች ስለርሷ ሰማ። ደግሞ ለአርማንያ ንጉሥ ለድርጣድስ ስለርሷ ከዲዮቅልጥያኖስ ሸሽታ እንደ መጣች የአርሴማን ሥራ ነገሩት እርሱም አንዱን የአርማንያ መኰንን ለእኔ ጠብቃት ወደ እኔም ላካት ብሎ አዘዘው።

ደናግሉም ይህን በሰሙ ጊዜ ወደ ሌላ ቦታ ተሠወሩ ወደ ንጉሥም ወነጀሉአቸው ንጉሡም ቅዱስት አርሴማን በክብር አድርገው ያመጧት ዘንድ አዘዘ እርሷም ወደ እርሱ መምጣትን እምቢ በአለች ጊዜ እየጎተቱ ወስደው ወደርሱ አደረሷት።

የቅድስት አርሴማንም ላህይና ደም ግባቷን በአየ ጊዜ ድንግልናዋን ሊያረክስ ሽቶ እናቷ አጋታን አባብላ እሺ ታሰኝለት ዘንድ አዘዛት አጋታም ወደርሷ ሒዳ ልቧን አስጨከነች እንዲህም አለቻት። ዕወቂ ይህ ርኲስ አረሚ እንዳያረክስሽና ሰማያዊ ሙሽራሽን እንዳትተዪ እርሱም ክብር ይግባውና የእግዚአብሔር ልጅ ሕያው ክርስቶስ ነው።

ንጉሡም ይዞ ወደ እልፍኙ ሊአስገባት ከአደባባይ መካከል ተነሥቶ ድንግል አርሴማን ያዛት። በዚያንም ጊዜ በቅድስት አርሴማ ላይ የእግዚአብሔር ኃይል አደረባትና በምድር ላይ ጣለችው እርሱ ግን በጦርነት እጅግ የጸና አርበኛ ስለ ነበር በታናሽ ሴት ብላቴና ስለተሸነፈ ያን ጊዜ አፈረ። ራሷንም በሰይፍ ይቆርጡ ዘንድ አዘዘና ቆረጧት ከዚህም በኋላ ደናግሉን ሁሉ ከእናታቸው አጋታ ጋር ይገድሏቸው ዘንድ አዘዘ።

አንዲት የታመመች ድንግል ነበረች በዐልጋዋ ላይም እንደተኛች ወደ ወታደሮች ጮኸች መጥተውም እንደ እኅቶቿ ራሷን ቆረጡ ሁሉም የሰማዕትነት አክሊልን ተቀበሉ እነዚያንም ከሮሜ አገር አብረው የመጡ ወንዶችን ገደሏቸው ቁጥራቸውም ሰባ አምስት ናቸው ሥጋቸውም በተራራ ላይ የተጣለ ሁኖ ቀረ።

ሰማዕታትም ከተገደሉ በኋላ በንጉሡ ላይ ጋኔን ተጫነበት መልኩም ተለውጦ እንደ እርያ ሆነ። ቅዱስ ጎርጎርዮስ ወደርሱ መጥቶ በላዩ ጸልዮ እስከ አዳነው ድረስ ስለዚህም ክብር ይግባውና በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አመነ። የቅዱሳን ሰማዕታትንም ሥጋቸውን ከተጣለበት ሰብስበው በአማረ ቦታ አኖሩአቸው ያማረች ውብ የሆነች ቤተ ክርስቲያንም ተሠራችላቸው። ከእነርሱም ታላላቅ ድንቆች ተአምራት ተገለጡ።

ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በሰማዕት ቅድስት አርሴማ ጸሎት ይማረን በረከቷም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።

(#ስንክሳር_ዘወርኅ_መስከረም)
https://t.me/joinchat/D8TC9g_CJ-plM2U8


አንተ ክርስቲያን ከኾንህ፥ ከምድራውያን ከተሞች (አገሮች) አንዲትዋስ እንኳን የአንተ አይደለችም፡፡ [አንዲት ከተማስ ይቅርና] ምድርን በሞላ በእጃችን ጭብጥ በእግራችን እርግጥ ብናደርጋትም እንኳን፥ አሁንም ቢኾን መጻተኞችና እንግዶች ነን፡፡ አገራችን በላይ በሰማይ ነውና፡፡

#ቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ
@ewkete_orthodox
@ewkete_orthodox


✝ የቻናላችን ቤተሰቦች እንኳን ለብርሃነ መስቀሉ በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን
#share & join
🔻 subscribe 🔻 
@ewkete_orthodox
@ewkete_orthodox
🔻 subscribe 🔻 




የደመራ ዓመት

መስቀል የከበረው ትናንት መስሏቸው
ያዩ ተገረሙ ክብሩ አስደንቋቸው
ትናንትና አይደለም የበራው ደመራ
ዘንድሮ ዓመት ፈጀ የመስቀሉ ሥራ

ስንት አይሁድ ተነሥተው መስቀሉን ቀበሩ?
ስንትስ እሌኒዎች ሊያወጡት ቆፈሩ?
ጅጅጋ ሲዳማ ውጡ ተናገሩ

ቤተ ክርስቲያን ልክ እንደ ደመራ
በእሳት ተለኩሳ ደምቃ ስታበራ
ካህናት ምእመናን እንደ ችቦ ነድደው
ስንቴ አከበሩት ለመስቀሉ ታርደው?

ስንት ጊዜ አፏጨ ዲያቢሎስ ተቆጣ
ስንት ሟርት ተሰማ ስንት ቁጣ መጣ?
በዕጣን ያልተገኘ ጌታ ያልሞተበት
ቅርፁ መስቀል ሆኖ መዳን የሌለበት
የወንበዴው መስቀል መስቀሉ መስሏቸው
ስንቶች ትተው ሔዱ ከእሌኒ እናታቸው?

ዓለም የዳነበት መስቀሉን ጨብጦ
ስለዘር የሚሰብክ እጅግ ተመስጦ
የተቃጠለውን መቅደስዋን እያየ
"ራስሽን አድኝ" ሲል ሲስቅ የታየ
ዘንድሮ አይደለም ወይ አይሁዱ የለየ?

ዘንድሮ ከበረ ለአንድ ዓመት ደመራ
በማያቆም ጥቃት በማያቆም ሴራ
ቅድስት ተዋሕዶ በጭንቅ ተወጥራ
አባቶችዋን ከፊት እንደ ጦር ሰድራ
በልጆችዋ ጩኸት በገና ደርድራ

በሰማዕታትዋ ደም ተረጭታና ርሳ
በየአደባባዩ ምሕላን አድርሳ
በፓትርያርክዋ ዓይን በምሬት አልቅሳ
እንደ ራሔል ለአምላክ ዕንባዋን አፍስሳ

ለመስቀሉ ቀን ግን ነጭ ልብስዋን ለብሳ
እንደ ቆስጠንጢኖስ በድል ልትነሣ
አምላክዋን ከፍ አድርጋ ኀዘንዋን ልትረሳ
ተስፋ ያደረገችው በመስቀል ታድሳ

ዘንድሮ ነው በዓል ዘንድሮ ደመራ
በዚህ ዓመት ተገኘን ከመስቀሉ ሥፍራ!!


++ በሰንበት መፍረስ ++

የኢያሪኮ ሰዎች የሠራዊት ጌታ የእግዚአብሔርን ኃይል በመናቃቸው ምንኛ ተጎዱ?! እርሱ ዓለምን የፈጠረ መሆኑን ስላላመኑ እንዳልተፈጠሩ የሆኑት የኢያሪኮ ሰዎች መጨረሻ እጅግ አሳዛኝ ነበር፡፡

ቅጥራቸው ከመፍረሱ በፊት እስራኤል የእግዚአብሔርን ታቦት ይዘው ለስድስት ቀናት ያህል በዝምታ ኢያሪኮን ዞሯት፡፡ ዓለምን በስድስት ቀናት የፈጠረውን ጌታ እንዲያስተውሉ ስድስት የዝምታ ቀናት ተሠጧቸው፡፡ በሰባተኛው ቀን ግን ጮኹ የኢያሪኮም ቅጥር ፈረሰ፡፡

ሰባተኛ ቀን የዕረፍት ቀን ነው፡፡ ለኢያሪኮ ግን የመፍረስ ቀን ሆነባት፡፡ ሰባተኛ ቀን ፈጣሪን ለሚያምኑ የተቀደሰ ቀን ነበር ፤ ለኢያሪኮ ግን የመረገም ቀን ሆነባት፡፡
እግዚአብሔር የፈጠረው ሁሉ መልካም እንደሆነ ባየበት ሰባተኛ ቀን ኢያሪኮ ግን ከፉ እንደሆነች ታየባት፡፡

እግዚአብሔር የሌለበት ሕይወት እንዲህ ነው፡፡ ወዳጄ እግዚአብሔር በሕይወትህ ውስጥ ከሌለ የሰንበት ቀን የነፍስህ ዕረፍት ቀን መሆኑ ይቀርና እንደ ኢያሪኮ የመፍረስ ቀን ይሆናል፡፡ በዚያ ቅዱስ ቀን ቅጥርህን በመጠጥ ፣ ብስካር ብዝሙት ስታፈርስ ትውልና ታድራለህ፡፡ ራስህን አንድደህ ትሞቃለህ ፤ እያራገብህ ትቃጠላለህ፡፡ ታቦት ይዘው ቢዞሩህም የኃጢአት ግንብን አጥረሃልና አትሰማም፡፡ በላይህ ላይ ቢቀደስብህም እንደ ኢያሪኮ ሰዎች ካህናቱን እያየህ ‘ዝም ብሎ መዞር ምንድር ነው?’ እያልክ ትስቃለህ፡፡ የካህናቱ የቅዳሴ ዜማ ለአንተ የሚያፈርስ ጩኸት ይሆንብሃል፡፡ የኢያሪኮ ሰው ከመሆን ፣ በሰንበት ፈራሽ ከመሆን ያድንህ!

ቅዳሴያችን መካከል ካህኑ ዕጣን እያጠኑ ዞረው ሲመለሱ የዚህች አጭር ጽሑፍ መነሻ ሃሳብ የሆነውን ይህንን ጸሎት ይጸልያሉ፦ አምላካችን እግዚአብሔር ሆይ አስቀድመህ በባሪያህ በነዌ ልጅ በኢያሱ እጅ የኢያሪኮን ግንብ እንዳፈረስከው የእኔንና የሕዝብህን የኃጢአታችንን ግንብ አፍርሰው፡፡

ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
ለተጨነቀች ነፍስ ዕረፍት የሆነው የእግዚአብሔር ቃል ለሁሉ ይዳረስ ዘንድ ጸልዩ! ሌሎች እንዲያነቡትም የሚከተሉት አድራሻዎች Like እና Share ያድርጉ


እናቴ አማላጄ ወዳጄ መጠጊያዬ ተስፋዬ ብርሀኔ
አረ ምኔ ብልሽ ምን ይገልፅሻል


"እኔስ ክርስቲያን እንድባል ክርስቲያን ሁኜም እንድኖር እወዳለሁ:: እንደ አባቶቼ ሐዋርያት ትምህርት በሕይወቴ ዘመን ሁሉ ክርስቲያን ሁኜ እንድውል ክርስቲያንም ሁኜ እንዳድር እወዳለሁ:: እንደ አባቶቼ ሐዋርያት ክርስቲያን ሁኜ በመቃብር ውስጥ እንዳንቀላፋ እወዳለሁ:: በትንሣኤዬም ከአባቶቼ ሐዋርያት ጋር ክርስቲያን ሁኜ እንድነቃ እወዳለሁ:: በጽዮን ተራራም በአባቶቼ ሐዋርያት እቅፍ ውስጥ እንዳርፍ እወዳለሁ::"

አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ
@ewkete_orthodox


✞ ኦ ቅዱስ ሚካኤል

ሚካኤል በአምላኩ በእግዚአብሔር ፊት ቆሟል
ለተጨነቀች ነፍስ ምህረት ይለምናል
ጨለማው እንዲሸሽ እንዲሆን ብርሃን
ኦ ቅዱስ ሚካኤል ሰዓለነ እንበል (2)

እረቂቁመላዕክ መብረቅ ተጎናጽፏል
ለሰማይ ሰራዊት አለቃቸው ሆኗል
የምክሩ አበጋዝ ስሙ የተፈራ
እሱ ነው ሚካኤል ለሕዝቡ የሚራራ (2)

አዝ__________________

እግዚአብሔር ኃይሉን የሚገልፅበት
ፀሎት የሚያሳርግ የሚያሰጥ ምህረት
ስለ ትህትናው ከአምላክ የተሾመው
ቅሩበ እግዚአብሔር ቅዱስ ሚካኤል ነው (2)

አዝ__________________

እርህሩነው እና የነፍሳችን ወዳጅ
ለፍጥረቱ ሁሉ የታመነ አማላጅ
ከቅጥረ ፀሎቱ ነፍሳችን ትጠጋ
ተግቶ እንዲጠብቀን ሲመሽም ሲነጋ (2)

አዝ__________________

የነፀብራቅ ዝናር ሚካኤል ታጠቀ
በቅድመ እግዚአብሔር ሕዝቡን አስታረቀ
በእሳታዊው አክናፍ ከክፉ ጋረደ
ልጆቹን ሊባርክ ሚካኤል ወረደ (2)


🙏ዝማሬ መላእክትን ያሰማልን🙏

ሊቀ መዘምራን ቴዎድሮስ ዮሴፍ
ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
•➢ ሼር // SHARE


ቅዱስ ሚካኤል:-
አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም መስከረም ዐሥራ ሁለት በዚህች ቀን የመላእክት አለቃ የቅዱስ ሚካኤል የበዓሉ መታሰቢያ ነው::

በዚህች ቀን ክብር ይግባውና እግዚአብሔር ወደ አሞጽ ልጅ ወደ ነቢይ ኢሳይያስ ላከው::

ኢሳይያስም መልአኩ እንደነገረው ይቅርም ብሎት ወደ ይሁዳ ንጉሥ ሕዝቅያስ ሔዶ እግዚአብሔር ይቅር እንዳለው ከደዌው እንዳዳነው በዕድሜውም ላይ ዐሥራ አምስት ዓመት እንደ ጨመረለት ይነግረው ዘንድ አዘዘው::

ሚስት አግብቶም ምናሴን እስከ ወለደው ድረስ በተጨመረለት ዕድሜ እያመሰገነ ስለኖረ እንዲህ ሆነ::

የእግዚአብሔር ቤተሰቦች እግዚአብሔር ለእኛ ያለውን ቸርነት አያችሁን!

አብቅቶልአል በቃ ልትሞት ነው ብሎ ብቻ አይተወንም:: መልአኩን ልኮ ይመክረናል::

በተለያዩ መምህራን በተለያዩ የሕይወት ውጣ ውረድ እያባበለ አስተምሮ ይመክረናል::

ሰምተንም በቶሎ ስለ ኃጢአታችን ተጸጽተን ንስሐ ስንገባ በዕድሜአችን ላይ አምስት ዐሥር ዐሥራ አምስት ሠላሳ ከዚያም በላይ ዓመት ይጨምርልናል::

ከእኛ የሚጠበቀ ስለ ሠራናት ኃጢአት መናዘዝ ስለተደረገልን ነገር ማመስገን ብቻ ነው::

በእውነት ፍጹም ፍቅሩን ከእኛ ያላራቀ የቅዱሳኑ አምላክ ልዑል እግዚአብሔር ይመስገን::

ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በዚህ በከበረ መልአክ በሚካኤል አማላጅነት ይማረን ለዘላለሙ አሜን::
🇪🇹@ewkete_orthodox⛪️⛪️

20 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.

904

obunachilar
Kanal statistikasi