የመጽሐፍት ትሩፉት : The Legacy Of Book's 📓📖📘🖊


Kanal geosi va tili: Efiopiya, Amharcha
Toifa: Kitoblar


የተመረጡ መጽሐፍትን ማንበብ የተሻለ ሠው ያደርጋል !

Связанные каналы

Kanal geosi va tili
Efiopiya, Amharcha
Statistika
Postlar filtri


ሊሞቱ የደረሱ ሰዎች የሚቆጫቸው 10 ነገሮች
(ከዶክተር ወዳጀነህ)

በተለያየ ህመም ምክኒያት በህይወት ጥቂት ጊዜ የቀራቸው ሰዎች ቀሪ ጊዜያቸውን ያለ ስቃይ እንዲያሳልፉ ህክምና የሚያገኙበት ቦታ Hospice ይባላል። ሆስፒስ ውስጥ የሚሰሩ የጤና ባለሞያዎች እነዚህን ከጥቂት ሳምንታት እስከ ጥቂት ወራት የቀራቸው ሰዎች በህይወታቸው ምን እንደሚቆጫቸው ጠይቀዋቸው የሚከተሉትን 10 ነጥቦች አግኝተዋል።

1) ደስተኛ አልነበርኩም- ህይወቴን በሚገባ enjoy አላደረግሁም።

2) በእውቀት ራሴን አላሳደግሁም። ለመማር ብዙ እድል ነበረኝ ግን አልተማርኩም።

3) እራሴን አልተንከባከብኩም-ጥሩ እንቅልፍ አልተኛሁም፤ ስፖርት አልሰራሁም፤ አመጋገቤ ላይ አልተጠነቀቅኩም፤ የጤና ምርመራ በሰአቱ አላደረግሁም።

4) የኖርኩት በቂምና በጥላቻ ነው-ሁሉም ነገር እንደዚህ ማለፉ ለማይቀር ለምን በቂምና በጥላቻ ራሴንም ሰዎችንም ጎዳሁ?

5) ለቤተሰቤ ጊዜ አልሰጠሁም-ላይ ታች ስል ከልጆቼ ጋር አልተጫወትኩም፤ ወላጆቼን እንደምወዳቸው አልነገርኳቸውም። አብሬያቸው ጊዜ አላሳለፍኩም።

6) ሰዎችን አልረዳሁም- ብዙ የእኔን እርዳታ የሚፈልጉ ሰዎች ነበሩ። አቅሙ እያለኝ እኔ ግን 'ቢዚ' ስለነበርኩ አልደረስኩላቸውም።

7) ህልሜን አልኖርኩም- ለብዙ አመታት ለአንድ መስሪያቤት ተቀጥሬ ነው የሰራሁት እንጂ የራሴን ህልም አልኖርኩም።

8) ያለምክኒያት ነው የለፋሁት- በማይጠቅሙኝ ነገሮች ተጠምጄ በጣም ስለፋ ነበር።

9) ለሰዎች ፍቅሬን አልገለፅኩም- ለምወዳቸው ሰዎች 'እወድሀለሁ' ወይም 'እወድሻለሁ' አላልኩም።ፍቅሬን ከመግለፅ ይልቅ እኮሳተራለሁ።

10) ሀይማኖትን እንቅ ነበረ- መንፈሳዊነትን እጠላ ነበር። አሁን መጨረሻዬ ላይ እስከምደርስ ወደ አምላኬ ዞር አላልኩም ነበር።

ዶ/ር ወዳጄነህ ማህረነ Dawit Dreams ላይ ከተናገረው የተወሰደ።

ሞት መቼ እንደሚመጣ አይታወቅም። በየሰአቱ በአለማችን 7500 ሰዎች ይሞታሉ። በየቀኑ በአለም አቀፍ ደረጃ 180ሺ ሰዎች ይሞታሉ። ሞት ማን ጋር መቼ እንደሚመጣ አይታወቅም። ደስተኛ ሆነን፣ ህልማችንን እየኖርን፣ ራሳችንን እየተንከባከብን፣ብዙም ኮስታራ ሳንሆን፣ ከምንወዳቸው ሰዎች ጋር ጊዜ እያሳለፍን በይቅርታ ልብ እንዲሁም በመንፈሳዊነት መኖር ሞት ሲመጣ እዳንፀፀት የሚያግዙ ነጥቦች ይመስሉኛል።

ያለ አእምሮ ጤና፤ ጤና የለም!!!


ፍትሐዊ የሃብት ክፍፍል ይደረግ ቢባልና ሐብት ከባለጸጎች እጂ ተነጥቆ ለሁሉም የድሃ ማህበረሰብ እኩል ቢከፋፈል እና ቢታደል ፣ ከጥቂት ወር ወይም አመት በኋላ ብሩ ተመልሶ ወደ ባለጸጎቹ እጅ ይገባል 😃

ምክንያቱም ሃብታሞች የብር መሰብሰብ እውቀት (የብር ልህቀት) ሲኖራቸው ድሃዎች ግን ይህ እውቀት የላቸውም። ድሃው ብርን ለእለት እና ለአመታዊ ፍጆታው ሲያውለው ሃብታሙ ግን ብሩን ለመስሪያና ለሌላ ገንዘብ ማግኛ ያውለዋል። ድሃዎች ባንክ ሲቆጥብ ሃብታሞ እቃ ገዝተው ያስቀምጣሉ። ወይም ይነግዳሉ። እንግዲህ በድሃና በሃብታሞች ያለው ልዩነት ይሄ ነው።

አለም በሁለት ጉራ፣ በሃብታምና በደሃ የተከፈለችው የመስራት ያለመስራት ጉዳይ ሳይሆን የmind set ጉዳይ ነው። ምክንያቱም ድሃው ከሃብታሙ የበለጠ ይሰራል ነገር ግን ጠብ አይልለትም። ጠንክረህ ከመስራት ይልቅ ጠንክረህ አስብ ! ጠንክረህ ብትሰራ ኮከብ ሰራተኛ ይሉሃል ጂ ባለ ኮከብ ሆቴል አይኖርህም ወይም ኮከብ ባለሃብት አትሆንም !


🏆 #አርጀንቲና

አርጀርቲና የFIFA የዓለም ሀገራት ዋንጫን አነሳች።

የአርጀንቲና ብሔራዊ ቡድን የ2018 ዓለም ዋንጫ አሸናፊዎቹን ፈረንሳይን በመለያ ምት በመርታት ሻምፒዮን ሆነዋል።

ሊዮኔል ሜሲ በእግር ኳስ ህይወቱ የመጀመሪያ የዓለም ዋንጫውን ማሸነፍ ችሏል።


"ኢትዮጵያ ታንብብ"
ሀገር የምትለማው፤
ሰላምም የሚገኘው፤
ፍትህም የሚሰፍነው፤
ሥልጣኔም የሚመጣው፤
የሰው ልጅ አእምሮ በዕውቀትና በምግባር ሲለማ ብቻ ነው።
ሀገራችን በሰው ቁጥር ብዛት እና በተፈጥሮ ጸጋ ሀብታም ብትሆንም፥
ከድህነት አረንቋ፣ ከድንቁርና አዙሪት፣ ከፍጅት እና ጦርነት ድግምት ግን ልትወጣ አልቻለችም።
ይኽ ለምን? የሚል መሠረታዊ ጥያቄ ያስነሳል።
መልሱ ቀላል ነው።
በዕውቀትና በሥነ ምግባር የታነፀ፣ አእምሮው የለማ ማኅበረሰብ ስለሌላት ነው። ሕዝቧ የቁጥር ብዛት እንጅ የዕውቀት ቅንጣት የሥነ ምግባርም ዘይቤ የለውም።
ጀብደኝነት እንጅ ጀግንነት የለውም፤ ችግርን የሚያወራ እንጅ መፍትሔ የሚዘይድ እምብዛም የለም። የሚያሾፍና ሳይኖረው በባዶ የሞላ እንጅ ለዕውቀት ቅንጣት ራሱን ክፍት ያደረገ የለም።
አዎ ኢትዮጵያ ማንበብ አለባት። ሕዝቡ ከቆመበት መንቀሳቀስ አለበት። ያኔ መሪዎችን መውለድ ይችላል።
አእምሮው የለማ መሪ ሲመራት ሀገርም በእውነት ትለማለች። ፍትኅን ተጎናፅፋ ሰላምን ተላብሳ ማበብ ትችላለች።
አዎ መሪ የወለደች እለት። በምግባርና በዕውቀት የተገነባ፣ ስሜቱን የገራ ኢትዮጵያዊ መንፈስን የተላበሰ መሪ የወለደች እለት።
ይኽ የሚኾነው ግን በቅዠታዊ ሕልም አይደለም። ትውልድ በዕውቀት እና በምግባር ሲቃኝ ነው።
ይኽ ደግሞ በመደበኛ ትምህርት ብቻ አይመጣም። በንባብ ባሕል ጭምር እንጅ።
የንባብ ባሕል ከመቸውም ጊዜ በላይ ማበብ አለበት።
ከመቸውም ጊዜ በላይ።
ምክንያቱም፥
ትናንትን በሚገባ የሚያውቅ፣
ዛሬን በአግባቡ የተረዳና
ነገን በእግረ ኅሊና ተጉዞ የሚያይና ዛሬ ላይ ኹኖ ነገንም የሚሠራ ድንቅ መሪ ያስፈልጋታልና።
ይኽም በዶክይሬት ጋጋታ ሳይኾን በንባብ የሚገኝ በመኾኑ
ንባብ ባሕል ሊኾን ይገባል።
=========>>>>>>>>
"ኢትዮጵያ ታንብብ በዕውቀትም ታብብ"
ዘ-አንኤል

@Kebiek 🖋


ከሁሉም በላይ የሚደንቀኝ የጃፓናዊያን የስራ ባህል ነው። የእረፍት ትርጉሙ አይገባቸውም! የዓለማችን ረጅም ሰዓታቸውን በስራ ላይ የሚያሳልፉ ዜጎች ጃፓናዊያን ናቸው። በስራ ብዛት የሰው ልጅ የሚሞተው ጃፓን ውስጥ ብቻ ነው! ሞቱን "Karoshi" ብለው ይጠሩታል። በዓመት ካላቸው የ 20 ቀን እረፍት ውስጥ 10 የሚሆነውን እንኳን በአግባቡ አይወስዱም። 63% የሚሆኑ ጃፓናዊያን በእረፍት ሰዓታቸው በሚከፈላቸው ገንዘብ ደስተኛ አይደሉም። መንግስት "....የአመት እረፍታችሁን እባካችሁ ውሰዱ! በስራ ብዛት እና ጭንቀት እየሞታችሁ ነው! እስቲ ትንሽ ዘና በሉ!..."ብሎ ሲለምን የምትሰማው የጃፓን መንግስትን ብቻ ነው።

የጃፓን ዋና ከተማ የሆነችው "ቶክዮ" 38 ሚልዮን ህዝብ ይኖራል! ይህንን 38 ሚልዮን ህዝብ በብዛት ከቤት ወደ ሥራ ከስራ ወደ ቤት የሚያመላልሰው ባቡር ነው። ባቡር ስልህ ታድያ መሃል ላይ መብራት ጠፍቶበት የሚቆመውን አይደለም! የዓለማችን ቁጥር አንድ ቀጠሮ አክባሪ ባቡሮች ያሉት እዛ ነው። አረፈዱ ከተባለ 6 ሰከንድ ነው! አንዴ አንድ ባቡር 18 ሰከንድ አርፍዶ ጉድ ተብሏል! ስራ በሃገሪቷ ባቡሮች መዘግየት ምክንያት ብታረፍድ እራሱ ባቡር ጣብያው "...እገሌ የሚባለው ስራተኛችሁ ያረፈደው በእርሱ ድክመት ሳይሆን በእኛ እንዝላልነት ነውና ይቅርታ!..." የሚል ደብዳቤ ሰጥቶህ ትሄዳለህ! በሰዓት ከ 320 ኪሎ ሜትር በላይ የሚበሩ "bullet train" የሚባሉ ባቡሮች ያሉት እዛ ነው! ጃፓኖች ጋር ባቡር ውስጥ ድምፅን ከፍ አድርጎ ማውራት ሳይቀር እንደ ነውር ይቆጠራል!

ጃፓን ውስጥ በምትስተናገድበት ሆቴል ወይም ሬስቶራንት ውስጥ "Tip" ለአስተናጋጅ መስጠት ነውር ነው። ለአንድ አስተናጋጅ "Tip" አስቀምጠህለት ብትሄድ እየሮጠ ተከትሎህ ይመልስልሃል! "ለምን?" ስትለው "...አንተን ማስተናገድ እና መንከባከብ ግዴታችን ነው፣ ስራችን ነው! ለዚህ ስራችን ደግሞ ደሞዝ ይከፈለናል! ስለዚህ ተጨማሪ ብር በ "Tip" መልክ መስጠት አይጠበቅብህም!..." ይሉሃል! እጅግ ሰው አክባሪ እና ትሁት ከመሆናቸው የተነሳ ማንኛውንም እቃ፣ ምግብ ወይም መጠጥ በሁለት እጃቸው እንጂ በአንድ እጃቸው በፍፁም አይቀበሉህም! እሱንም ከወገባቸው ጎንበስ ብለው ነው። የሚገርመው ቤት ውስጥ ውጪ የዋልክበትን ጫማ አድርጎ መግባት ነውር ነው። አይደለም ቤትህ አንዳንድ ምግብ ቤቶች ሳይቀር ተስተናጋጆች ጫማቸውን አድርገው እንዲገቡ አይፈቀድም! በር ላይ ሸበጥ/ሲሊፐር ስለሚቀመጥልህ ቀይረህ መግባት ግድ ነው።

ከዓለማችን ብቁ ተማሪዎች ተርታ ይሰለፋሉ። 100% የሚሆነው የሃገሪቷ ወጣቷ በሚገባ ፊደል የቆጠረ እና ቀጥቅጦ የተማረ ነው። ህፃናት ሃገራቸውን እንዲወዱ፣ ቤተሰባቸውን እና ማህበረሰባቸውን እንዲያከብሩ ተድርገው ያድጋሉ! የጃፓን ትምህርት ቤቶች ውስጥ የፅዳት ሰራተኛ አይቀጠርም! "ለምን?" ካልከኝ ከትምህርት በኃላ ሁሉም መምህራን እና ተማሪዎች ለ 15 ደቂቃ ልብሳቸውን ቀይረው ትምህርት ቤቱ ውስጥ የሚገኙ ሁሉንም ክፍሎች(መፀዳጃ ቤትን ጨምሮ) እኩል ያፀዳሉ! የጃፓን ተማሪዎች በሂሳብ፣ ፊዚክስ እና ቋንቋ መጎበዝ ግዴታቸው ነው። ተማሪዎች የፍቅር ግንኙነት መመስረት አይችሉም! እሱ ብቻ ሳይሆን ትምህርት ቤት ውስጥ መሳሳምም ሆነ መተቃቀፍ አይቻልም፣ ያስቀጣል፣ አለፍ ካለም ያስባርራል!

ከ Wendye Engida የፌስቡክ ገፅ የተቀነጨበ !


አባዬ እንዴት ነህ? ይህንን ፅሁፍ አንብበህ ስትጨርስ አፍሪካዊ ሆነህ በመፈጠርህ ልትፀፀት ስለምትችል ይቅርብህ!😀

ምን መሰለህ!?

ዓለም ላይ 7.8 ቢልዮን ህዝብ አለ። ከዛ ውስጥ ከ 1 ቢልዮን በላይ የሚገመተው ሰው የሞባይል ስልክ አለው! ተንደላቀህ የምትጠቀመው ስልክ እና ላፕቶፕ፣ በየሆስፒታሉ የምትታከምባቸው ዘመናዊ ማሽኖች እና ሌሎች በቻርጅ የሚሰሩ የኤሌክትሮኒክ መሳርያዎች አንዲት የአፍሪካ ሃገር ከሌለች የሉም!

እንዴት?

"Coltan" ከሚባለው መዓድን አለ። ከዚህ ድንጋይ መሰል መዓድን ውስጥ ደግሞ "Tantalum" የሚባል "powder" (ዱቄት) ይወጣል!

ለምን?

የያዝከው ስልክ ቻርጅ ተደርጎ ጥቅም ላይ የሚውለው(የሚሰራው) ከዚህ "Coltan" ከሚባል መአድን ውስጥ በሚወጣ "Tantalum" በሚባል "powder" ነው።

ይህ መዓድን ደግሞ በስፋት ያለው "Democratic Republic of Congo(DRC)" ውስጥ ነው! 80% የሚሆነው "Coltan" የሚገኘው ከዚህች የዓለማችን እጅግ ደሃ ከሆነች እና ከቆረቆዘች ሃገር ነው!

ጌታዬ! "Apple", "Microsoft", "Vodafone","Nokia", "Samsung", "Huawei".... የፈለከውን ምርት መጥቀስ ትችላለህ ስልካቸውን የሚሸጡልህ ከ "Congo" በህጋዊም ሆነ በህገ ወጥ መንገድ በሚያስኮበልሉት "Coltan" ሰርተውልህ ነው። አፍሪካ አይለፍልሽ የተባለች፣ በቸነፈር፣ በችጋር፣ በበሽታ፣ በድህነት፣ በስቃይ፣ በጦርነት እና በሞት የተሞላች ገፊ አህጉር ናት! "Congo" በታሪኳ ተረጋግታ የማታውቅ ትልቅ ሃገር ናት! ሃገሪቷ መረጋጋት እንኳን ብትፈልግ የውጪ ሃይሎች በተለይ ምዕራባዊያኖቹ እንድትረጋጋ አይፈልጉም!

ለምን መሰለህ! እቺህ ሃገር ተረጋግታ፣ ሰላማዊ መንግስት መስርታ፣ በየጫካው መሳርያ ታጥቀው የሚዋጉ አማፅያን ወደ ሰላም ድርድር መጥተው፣ ሙስናን አስወግዳ እና ተቋማቶቿን አጠናክራ ከመጣች አደጋው ለነሱ ከባድ ነው! እንደ "Coltan" ያለ የዓለም ቴክኖሎጂ ሳንባ የሆነ መዓድን ባለቤት የሆነችን ሃገር እንዴት ነው እንድትረጋጋ የምታደርገው? አባዬ! ነገ "....."Coltan"ን የምሸጠው በዚህ ዋጋ ነው! መደራደር አለብኝ!...ምናምን" ብላ ብታስቸግርስ?

ስለዚህ እንደልብህ እቺን ደሃ ሃገር መዝረፍ የምትችለው መቼም ሰላም እንድታገኝ ባለማድረግ፣ አማፅያኖቹን በተዘዋዋሪም ሆነ በቀጥታ መንገድ በገንዘብ እና በክላሽ እንደልብ እየረዳህ እርስ በእርስ እንዲጨራረሱ በማድረግ እና ያልተማረው ህዝቧ መቼም እንዳይሰለጥን በማድረግ ነው!

የሚያሳዝኑ ጥሬ ሃቆች!

ይህን "Coltan" የተሰኘ መዓድንን የሚያወጡ ምስኪን የኮንጎ ዜጎች በወር ጥሩ ተከፈላቸው ከተባለ እስከ "50 ዶላር" ድረስ ብቻ ነው። 40 ሺህ የሚጠጉ እድሜያቸው ከ 15 ዓመት በታች የሚሆኑ ህፃናት ትምህርታቸውን አቁመው ይህንን መዓድን ቀኑን ሙሉ ሲፈልጉ እና መሬት ሲጭሩ ይውላሉ!

እ.ኤ.አ ከ 1998 ጀምሮ ይህንን መዓድን በማውጣት የተሰማሩ ስድስት ሚልዮን የሚሆኑ የሃገሪቱ ዜጎች እስካሁን በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ መንገድ እንደሞቱ ይነገራል! በወር እስከ 10 ሺህ ሰው ይህንን መዓድን ለማውጣት ሲል በሚፈጠር ግጭት ይረግፋል!

ህዝቡ ይህንን መዓድን ፍለጋ ሲኳትን ደኖቹን መንጥሮ መንጥሮ ሃገሪቷን ምድረ በዳ ሊያደርጋት ነው። የዱር እንስሳት ማደርያ አጥተው እየተሰደዱ ነው!

መዓድኑን በዋነኝነት የሚያወጡት ህፃናት እና ሴቶች ናቸው! የመዓድን ቦታዎቹ ደግሞ ወጥ በሆነ መንገድ ከሃገሪቱ መንግስት ጋር የተያያዙ አይደሉም። ወይ በመዝባሪ የውጪ ባለሃብቶች ወይ ደግሞ ሃገሪቷ ውስጥ በሚንቀሳቀሱ ህገ ወጥ አማፅያን የተያዙ ናቸው! ደላላዎቹ እነሱ ናቸው! አብዛኛው መዓድን በህገ ወጥ መንገድ በአማፅያኖቹ አማካኝነት ከሃገር ይወጣል። ከዛም በዚህም ሆነ በዛ ቅድም የጠቀስናቸው ግዙፍ የስልክ አምራች ኩባንያዎች ጋር ይህ መዓድን ይደርሳል!

ሚሊሻዎቹ(አማፅያኖቹ) ከዚህ መዓድን ሽያጭ ያገኙትን ገንዘብ ትምህርት ቤት፣ ጤና ጣብያ ወይም መንገድ አይደለም የሚያሰሩበት! ጌታዬ! የሚገራርም ጥይት ነው የሚሸምቱበት! ከዛ እርስ በእርስ ይናጩበታል!

አብዛኛዎቹ የዚህች ሃገር መሪዎች ሃገሪቷን ሊያሳድጉ ወደ ስልጣን አይመጡም! ይልቁስን ዘርፈው...ዘርፈው...ከዛም የዘረፉትን ገንዘብ አውሮፓ እና አሜሪካ አስኮብልለው ጥለዋት ይሄዳሉ!

ይህ መዓድን በ "Rwanda" የዘር ጭፍጨፋ ወቅት ሳይቀር አስተዋጽኦ አበርክቷል! መዓድኑ በህገ ወጥ መንገድ አብዛኛውን ግዜ የሚኮበልለው በጎረቤት "Rwanda" በኩል ነው! በወቅቱ የሩዋንዳ መከላከያ ይህንን መዓድን በመሸጥ ብቻ ወደ "250 ሚልዮን ዶላር" አግኝቷል! ገንዘቡን ደግሞ በወቅቱ ለምን መሸመቻነት እንዳዋሉት አንተው ታውቃለህ።

ስናጠቃልለው!

"Congo" የዓለማችን እጅግ በጣም ሃብታም ሃገር ናት! 30% የዓለማችን ዳይመንድ እዛ ነው፣ 80% የዓለም "Coltan" የሚመጣው ከዛ ነው! 33% የዓለም ኮፐር ክምችት ያለው እዛ ነው! የወርቅ፣ የነዳጅ፣ የዩራንየም እና የዚንክ ከፍተኛ ክምችት ሳይቀር አላት!

በጣም የሚዘገንን ጥሬ ሃቅ!

"Congo" 24 ትሪልዮን ዶላር የሚገመት ገና ያልተነካ(Untapped) መዓድን አላት! ጌታዬ! እንዳትረሳ! የአሜሪካ "GDP" እራሱ 22 ትሪልዮን ዶላር ነው! እቺህ ሃገር ቢያልፍላት፣ ሰላም ብትሆን እና ህዝቦቿ ቢነቁ ሙሉ አፍሪካን ቁጭ አድርጋ መቀለብ ትችል ነበር።

ነገር ግን እንደ አለመታደል ሆኖ ይህንን ሁሉ የተፈጥሮ ሃብታ የያዘች ሃገር የዓለማችን እጅግ ደሃ ሃገር ሆና ህዝቦቿ ሲበዘበዙ፣ ሲራቡ እና በጦርነት ስትታመስ ከማየት በላይ የሚያበሽቅ፣ የሚያቃጥል፣ የሚያንገበግብ ሌላ ምን አለ? ይህንን ስትሰማ እቺን አህጉት ጥለህ ጥፋ ጥፋ አያሰኝህም ወይ?

መልካም ምሽት!🙏

Wendye Engida

@legacyofbooks12


በፍቅር እወዳቸዋለሁ! እጅግ አከብራቸዋለሁ! ፍፁም የተለዩ ህዝቦች ናቸው! ሰለጠኑ ከሚባሉት ምዕራባውያኖቹ ጋር ሲነፃፀሩ በትንሹ 20 ዓመታትን ጥለዋቸው ሄደዋል!

"...ህዝቦቿ ደማቸውን አፍስሰው፣ አጥንታቸውን ከስክሰው የዛሬዋን ሃገራቸውን ገነቡ!" ቢባልላቸው አያንስባቸውም!

ፀዴ ናቸው፣ ስልጡን ናቸው፣ ሰው አክባሪ ናቸው፣ ሃገራቸውን አብዝተው ይወዳሉ ሳይሆን ያፈቅራሉ። ስልጣኔ ማማው ቢታይ ጃፓን ላይ ነው። የህዝብ ቁጥራቸው ቀላል አይደለም! 126 ሚልዮን ገደማ ናቸው።

ቤትህ አልበላሽ ያለህ "Sony" ቴሌቪዥን የነሱ ነው፣ ያሳደገህ ብረቱ "Hitachi" ፍሪጅ የነሱ እጅ ያረፈበት ነው፣ ሃገራችንን ብቻ ሳይሆን ዓለማችንን ያጥለቀለቀው "Toyota" መኪና የነሱ ጥበብ ውጤት ነው፣ "Nikon" እና "Canon" ካሜራዎች የነሱ አሻራዎች ናቸው፣ እንደዛ በፍቅር የምትወደው "Toshiba" ላፕቶፕህ የነሱ ነው፣ "Mazda", "Lexus", "Mitsubishi", "Honda", "Nissan", "Isuzu", "Suzuki" ምናምን የምትላቸው መኪናዎች የተፈበረኩት በነሱ ነው። እጃቸው የነካው ምርት ሁሉ ብሩክ እና ብረት ነው።

... የዓለማችን ትልቁ አማካይ የመኖርያ እድሜ ያለው ጃፓን ነው። አንድ ጃፓናዊ በአማካይ 83 ዓመት ይኖራል። ውፍረት እንደ ሃጥያት የሚቆጠርባት ጃፓን ውስጥ የተዝረጠረጠው ህዝብ ከ 4% አይበልጥም። ጌታዬ! ይህ አሃዝ አሜሪካ ውስጥ 40% ነው! የመኖራችን ሚስጥር ስፖርት፣ አሳ እና ቅጠላ ቅጠል ነው ይላሉ! ብታምነኝም ባታምነኝም ጃፓን ውስጥ 50 ሺህ እድሜያቸው ከ 100 በላይ የሆኑ ሰዎች ይኖራሉ!

የጃፓናዊያን የስራ ፍቅር በቃላት አይገለጽም ከለሊቱ 9 ሰዓት ላይ የጃፓን መንገዶችን ብትመለከት ሽክ ብሎ ሱፉን ለብሶ እና "briefcase" ይዞ ወደ ስራ የሚሄድ ብዙ ሰው ታያለህ። አብዛኛው ጃፓናዊ "ለምን ትሰራለህ?" ተብሎ ሲጠየቅ "ሃገሬን ስለምወድ እና ብቁ ዜጋ ሆኜ መገኘት ስላለብኝ!" ብሎ ይመልስልሃል። ያለ እረፍት ከመስራታቸው ብዛት የጃፓን መስሪያ ቤቶች ውስጥ ጠረጴዛቸውን ተደግፈው የሚያንቀላፉ ሰዎችን ማየት የተለመደ ነው። የታታሪነት፣ የብርቱነት እና ሃገር ወዳድነት መገለጫ ነው። ከአጠቃላይ ህዝብ ቁጥሩ ውስጥ 3% የሚሆነው ብቻ ስራ አጥ ሲሆን ሰዎች ስራ ፈትተው በመቀመጣቸው ምክንያት በጭንቀት እራሳቸውን የሚያጠፉባት ሃገር ናት።

ከ Wendye Engida የፌስቡክ ገፅ የተቀነጨበ

@legacyofbooks12


ከተማሩ ሰዎች ይልቅ በመከራ ያለፉ ሰዎችን አከብራለሁ

አልማዝ የሚሆነው የድንጋይ ከሰል ነው !

አልማዝ በተፈጥሮ መንገድ እንዴት እንደሚሰራ ልንገራችሁ። አልማዝ የሚሰራው HPHT በሚባል Process ነው። HPHT ማለት High Pressure High Temperature ማለት ነው። አንድ አልማዝ አልማዝ ከመሆኑ በፊት አራት ደራጃዎችን ማለፍ ይኖርበታል። አንደኛ ከምድር በታች ከ300 እስከ 600 ኪሎ ሜትር ዝቅ ብሎ መቀመጥ። ሁለተኛ ከፍተኛ ሙቀት መታደል፣ ከ1200 ዲግሪ ሴንቲ ግሬት ቃጠሎ ውስጥ መቀመጥ። ሶስተኛ ከፍተኛ ጭነት ማግኘት። አራተኛ ለረዥም ጊዜ ውስጥ በነዚህ ሁኔታ ውስጥ መቆየት ! እንግዲህ አንድን የድንጋይ ከሰል ወስዳችሁ ከምድር በታች 600 ኪሎ ሜትር ብታወርዱት፣ 1200 ዲግሬ ስንቲ ግሬት ቃጦሎ ውስጥ ብታኖሩት፣ በከፍተኛ ፕሬዠር ውስጥ ብታስቀምጡት እና ለረዥም ጊዚያት በዚህ ሁኔታ ውስጥ ብትተዉት። ከሱሉ አልማዝ ይሆናል ! ከሰሉ ወደ ዳይመንድ ይለወጣል።

አንዳንዶቻችሁ በህይወታችሁ ግራ ይገባችኋል፣ በጣም የሚወዳችሁ አምላካችሁ ከጓደኞቻችሁ በታች 600 ኪሎ ሜትር አውርዷችሁ ይሆናል። በማይገባችሁ ፈተና 1200 degree cent great ቃጠሎ ውስጥ አስቀምጧችሁ ፤ በማጣት፣ በመገለል፣ በመገፋት ለረዥም ጊዚያት እየፈተናችሁ "ምንድነው እየተካሄደ ያለው" ብላችሁ እስክትጠይቁ ድረስ ለአምስት አመት፣ ለአስር አመት ከሰው፣ ከወዳጅ፣ ከዘመድ፣ ከጓደኛ ዝቅ አድርጓችሁ ይሆናል። ....

"ምን ማለት ነው የሚወደኝ አምላክ ይሄን የሚፈቅደው" ስትሉ .... አልማዝ አድርጎ ሊሰራችሁ፣ ውብ አድርጎ፣ ሊሰራችሁ፣ የምታበሩ አድርጎ ሊያበጃችሁ፣ እንቁ፣ ዳይመንድ፣ አልማዝ ሊያደርጋችሁ ስላሰበ ነው !

አልማዝ ሰባት ባህሪዎች አሉት። አንደኛ ጠንካራ ነው። ወስዳችሁ በድንጋይ ቀጥቅጡት አይሰበርም። በሰይፍ ምቱት አይሰነጠቅም። በመጋዝ ገዝግዙት አይቆረጥም። በአልመዝ ግን ብረት ይቆረጣል፣ በአልማዝ ግን ሰይፍ ይቆረጣል። በአልማዝ ግን ድንጋይ ይፈርሳል። አልማዝ የሚቆረጠው በሌላ አልማዝ ነው። ሁለተኛ የአልማዝ ባህሪ ልንገራችሁ። ከፍተኛ የማንጸባረቅ ባህሪ አለው። refractive index ይባላል። የተቀበለውን ብርሃን መልሶ የማብራት ባህሪ አለው። ያንጸባርቃል። ሶስተኛው የአልማዝ ባህሪ የተቀበለውን የጸሐይ ብርሃን፣ ነጩን ብርሃን ወደ ተለያዩ በርካታ ቀለማት የመበተን ችሎታ አለው። አራተኛ የአልማዝ ባህሪ ልንገራችሁ። እጅግ በጣም ንጹህ ነው። አልማዝ የሚታወቀው በነጹህነቱ ነው። አምስተኛ የአልማዝ ባህሪ ልንገራችሁ። አልማዝ በእሳት አይቃጠልም። አንድ ቤት ውስጥ አልማዝ አለ እንበል ያ አልማዝ ያለበት ቤት ሙሉ ለሙሉ ቢቃጠል አልማዙ ምንም አይሆንም። ምንም። በነበረው ቅርጹ፣ በነበረው ንጽህናው እናገኘዋለን። የሚያስገርመኝን ስድስተኛውን የአልማዝን ባህሪ ልንገራችሁ። ወርቅ ላይ አሲድ ድፉበት ወርቁ ይበላሻል። አልማዝ ላይ አሲድ አፍስሱበት ምንም አይሆንም። አይበላሽም። የመጨረሻው እና ሰባተኛው የአልማዝ ባህሪ በጣም ውድ ነው። በጣም ውድ ነው። የአውራጣትህን ራስ የምታክል ዳይመንድ አንድ ትልቅ ፎቅ ይገዛል። በጣም ውድ ነው።

ከጓደኞቻችሁ በታች 600 ኪሎ ሜትር ወርዳችሁ ፣ በ1200 ዲግሪ ሴንቲ ግሬት ስቃይ ውስጥ ያለፋችሁ፣ በፕሬዠር ውስጥ ለበርካታ አመታት ያለፋችሁ እናንተ አልማዝ ሁናችሁ የተሰራችሁ ሰዎች ናችሁ። ሰዎች ጠጠር ብትመስሏቸውም አልማዞች ናችሁ። ዋጋችሁ በጣም ውድ ነው። ... ከተማሩ ሰዎች ይልቅ፣ ብዙ ድግሪ ከተሳካላቸው ሰዎች ይልቅ፤ በመከራ ያለፉ ሰዎችን አከብራለሁ። ዋጋ የከፈሉ ሰዎችን አከብራለሁ። በስቃይ ውስጥ ያለፉ ሰዎችን አከብራለሁ። ምክንያቱም ዋጋቸው በጣም ውድ ነው።

መልካም ምሽት

(የዶክተር ወዳጀነህ ንግግርን ለንባብ እንዲመች አድርጌ አሳጥሬ አሰናደሁላችሁ 😃)



ጸሐፊ ሔኖክ ሠጠኝ ነኝ


"እኔ ወደየትኛውም ሃገር ተሰድጄ ወይም ጥገኝነት ጠይቄ አልሄድም። የተወለድኩት እዚሁ ነው። የምሞተውም በዚሁ በሃገሬ በሊቢያ ነው። እኔ ወደ ስልጣን ስመጣ ይህ ሃገር ሙሉ በሙሉ በረሃ ነበር። እኔ ግን ሁሉም እፅዋት እንዲበቅልበት አድርጌ ወደ ልምላሜ ቀይሬዋለሁ። ይህችን ሃገር ከራሷ ዜጎች በላይ ማንም አይወዳትም።

አሜሪካውያንና አውሮፓውያን እንወዳችኋለን ቢሏችሁ አትመኗቸው። ተጠንቀቁ! እነሱ የሚፈልጉት ሃብታችሁን ነው። እነሱ የሚወዱት የዚህችን ሃገር ነዳጅ እንጅ ህዝቦቿን አይደለም። ዛሬ እናንተ እኔን ትወጉ ዘንድ እያነሳሷችሁና እያገዟችሁ ነው። ነገር ግን እናንተ ከኔ ጎን ቆማችሁ እነሱን ብትዋጉ ብልህነት ነው። ምክንያቱም ምዕራባውያን አሁን እየወጉ ያሉት የወደፊት ተስፋና ራዕያችሁን ነው።

ለመላው ሊቢያውያን ማስተላለፍ የምፈልገው አንድ መልእክት አለኝ። ዛሬ ምዕራባውያን እናንተ እኔን ትወጉbዘንድ
እያስታጠቋችሁና እየደገፏችሁ ነው። ነገርግን እውነት እላችኋለሁ በኋላ ለዚህ ጥፋት በምትከፍሉት መራራ ዋጋ እጅግ ትጎዳላችሁ።

ለእናንተ ለአሜሪካኖችና ለአውሮፓውያንም ልነግራችሁ የምፈልገው ነገር አለኝ። እናንተ ትገሉኛላችሁ። ነገር ግን እኔ ከሞትኩ በኋላ ለምትጋፈጡት ማቆሚያ የሌለው የሽብር ጦርነት ራሳችሁን አዘጋጁ። እናንተ ከድንቁርናችሁ ሰመመን ከመንቃታችሁ በፊት አሸባሪዎች ጦርነቱን እደጃችሁ ድረስ ያመጡታል።"

ጋዳፊ በአሜሪካ ፊትአውራሪነትነና በምዕራባውያን ደጋፊነት በተከፈተባቸው ጦርነት ከመገደላቸውና ሊቢያም አሁን ባለችበት ሁኔታ ከመፈራረሷ በፊት ጋዳፊ የተገደሉት በሃገር ቤት ለዜጎቻቸው፣ በዓለም መድረክም ለተቀረው ዓለም አንባገነን ስለነበሩ ነበር ከተባለና የጋዳፊ መንግስትም ለውድቀት ሃገሪቱም ለመበታተን የበቃችው መንግስታቸው አምባገነን ስለነበረ ብቻ ነው ወደሚለው ከእውነታው ያፈነገጠ መደምደሚያ የምንደርስ ከሆነ "አምባገነን" እና "ዴሞክራሲያዊ" የሚሉት ቃላት ፍች በአተረጓጎም ቦታ ተቀያይረዋል ማለት ነው።

እስኪ ጋዳፊ በስልጣን ላይ በነበሩበት ዘመን ሊቢያውያን ያገኙ የነበሩትን የዜግነት ጥቅም አንድ በአንድ እንይና ኮለኔል ጋዳፊ በመጨረሻው ዘመናቸው የተናገሩትን ትንቢታዊ መልዕክት፣ የአሜሪካኖች በሰው ሃገር ጣልቃ የመግባት ውጤት ከሆነችው እና ዛሬ ብትንትኗ ወጥቶ ዜጎቿ ቁራሽ ዳቦ ብርቅ እንዲሆንባቸው ከተደረገችው፣ ለአለም ህዝቦች በተለይም ለመሃከለኛው ምስራቅ ሰላም ስጋት የሆኑ ሽብርተኞች መፈልፈያ ከሆነችው ከዛሬዋ ሊቢያ ጋር እናስተያየውና የራሳችንን ፍርድ እንስጥ…

1. #በጋዳፊ ዘመን በሊቢያ የኤሌትሪክ ሃይል ከክፍያ ነፃ ነበር። የኤሌትሪክ ፍጆታ ቢል ብሎ ነገር አልነበረም።

2. #ማንኛውም ሊቢያዊ የባንክ ብድር ከፈለገ ከወለድ ነፃ በ 0% interest የፈለገውን ገንዘብ መውሰድ ይችል ነበር።

3. #በሊቢያ የመኖርያ ቤት ማግኘት ከሰብዓዊ መብቶች እንደ አንዱ ይቆጠር ነበር።

4. #በሊቢያ ህክምናና ትምህርት በነፃ ይሰጥ ነበር። ከጋዳፊ በፊት 25% የነበረው የተማረ ሰው ሃይል መጠን በእሳቸው ግዜ 83% ደርሶ ነበር።

5. በሊቢያ በግብርና ስራ ላይ መሰማራት የሚፈልግ የእርሻ መሬት፣የግብርና ግብአት ማቀነባበሪያ ቤት፣መሳርያዎችና የተለያየ ቁሳቁስ ከመንግስት በነፃ እንደ ማበረታቻ ይሰጠው ነበር።

6. በሃገር ውስጥ የከፍተኛ ትምህርትና ህክምና ማግኘት ላልቻሉ ዜጎች እነዚህን ወደውጭ ሃገር ሄደው ያሟሉ ዘንድ መንግስት ድጎማ ያደርግ ነበር።

7. ሊቢያውያን አዲስ መኪና ሲገዙ የወጭውን 50% በመንግስት ይደጎሙ ነበር።

8. በሊቢያ የነዳጅ ዋጋ 0.14 ዶላር በሊትር ነበር።

9. ሊቢያ ምንም አይነት የውጭ ብድር ያልነበረባት ሃገር ከመሆኗም በላይ የመንግስት የመጠባበቂያ ካፒታል መጠኗም 150 ቢሊየን ዶላር ነበር።

10. በሊቢያ አዲስ ተመራቂ የሆነ ዜጋ እንደተመረቀ ስራ ካላገኘ በሙያው ቢቀጠር ያገኝ የነበረውን ደሞዝ 50% ያህል ስራ እስኪቀጠር መንግስት ይከፍለው ነበር።

11. ሊቢያ ከነዳጅ ታገኘው ከነበረው ገቢ ግማሽ ያህሉ ወደ እያንዳንዱ ሊቢያዊ የባንክ ሂሳብ ፈሰስ ይደረግ ነበር።

12. በሊቢያ አዲስ ህፃን የምትወልድ ሴት ከመንግስት 5ሺህ ዶላር በሽልማት መልክ ይሰጣት ነበር።

13. በሊቢያ በቁጥር 40 የሚደርስ ሙልሙል ዳቦ ዋጋው የአንድ ዶላር 15 ሳንቲም አካባቢ ነበር።

14. ከሊቢያ ዜጎች 25% ያህሉ የዩኒቨርስቲ የመጀመሪያ ዲግሪ ማግኘት ችለዋል።

15. ጋዳፊ በዘመናቸው በዓለም 1ኛ የሆነውንና ሰው ሰራሽ ወንዝ በመባል የሚታወቀውን ፕሮጀክት በመስራትና በእያንዳንዱ በረሃማ ከተሞች ውሃ በየቤቱ እንዲዳረስ ያስቻለ ስራ ሰርተዋል።

እንግዲህ ጋዳፊን ለሞት፣ ሃገሪቱን ደግሞ ለማያባራ የእርስ በእርስ ጦርነትና መበታተን የዳረጋት የአንባገነንነት መገለጫ ከላይ የተገለፀው ትሩፋት ከነበረ፣ የሰው ሃገር ሉአላዊነት ምእራባዊያን በፈለጉ ሰዓት እየደፈሩ፣መንግስታትና ህዝቦችን እየከፋፈሉ፣ ህፃናትን ሴቶችንና አረጋውያንን ለማያባራ ሰቆቃ እየዳረጉ ያሉትና ራሳቸውን የዴሞክራሲ መሲሆች አድርገው የሚቆጥሩት አሜሪካውያን እና አውሮፓውያን መገለጫቸው ምን ይሆን…

እኛስ ለሀገራችን ኢትዮጵያ ምን ማድረግ አለብን !
ሁላችንም ስለእውነት ቆም ብለን እናስብ!




እዚህ ብሄራዊ ቴአትር መድረክ ላይ : የዛሬ ሰላሳ አመት አካባቢ ... ማለትም በልጅነቴ ትንግርት የሆነ ሰው አየሁ፣ በጣም የሚገርም ሰው። ማረሳው ምን አልባት ያልተተካ የምለው ተዋናይ አየሁ። ወጋየሁ ንጋቱ የሚባል ሰው። እንኳን ኢትዮጵያ ውስጥ አለም ላይ የተፈጠረ አይመስለኝም እንደሱ አይነት ሰው። እና ሁሌም በህሊናየ ተስሎ አልረሳውም ወጋየሁ ንጋቱ : የተውኔት ሰው። ከዛ በኋላ የዛሬ አስር አመት ደግሞ ወጋየሁን ባየሁ በሃያ አመቱ ማለት ነው ሌላ ትንግርት የሆነ ሰው አየሁ ፣ አስገራሚ የሆነ ሰው አየሁ። ሽመልስ አበራ የሚባል። ... እንደ እኔ ሽመልስ የሚመጥነውን ስክሪፕት ያገኘ አይመስለኝም እስካሁን ድረስ። እንጂ በውስጡ ያለው ብቃት እጅግ በጣም በጣም አስገራሚ ነው። እና ስለ ሽመልስም በጣም ደስ ይለኛል 🙏

(በቅርቡ ዶክተር ወዳጀነህ ስለ ሽመልስ አበራ (ጀሮ) በብሄራዊ ቴአትር የተናገረው


ብዙ የክፍለ ሃገር ልጆች ግን አዲስ አበባ ከመጡ በኋላ ለምድነው በተወለዱበት ቦታ ባሳደጋቸው ባህል ማፈር የሚጀምሩት ? የሚያውቁትን ቋንቋ ለመናገር የሚሳቀቁት ? የክልላቸውን ቋንቋ ለመናገር የሚያፍሩት ፣ የሚሰሙትን የሚናገሩትን ቋንቋቸውን መናገር አልችልም ብለው እስኪክዱት ድረስ ለምድነው የሚክዱት፣ የሚሳቀቁት? ... የአዲስ አበባ ሰው ምን አይነት የስነልቦና ጉዳት ቢያደርሱባቸው ነው ? ምን አይነት የበታችነት ስሜት እንዲሰማቸው ቢያደርጓቸው ነው ? እንዴት ባሉ እራስ ወዳድ እና እንዴት ባሉ እራሳቸውን አግዝፈው በሚያዩ ሰዎች መሃል ቢመላለሱ ነው እንዲህ አይነት ስሜት እንዲሰማቸው የሆነው ?


በስምምነቱ ምን አገኘን?

ሰበር መረጃ ከፕሪቶሪያ

በደቡብ አፍሪካ በተካሄደው የሰላም ውይይት የህወሓት መዋቅር ፈርሶ የፌደራል መንግሥት የሚመራው ጊዜያዊ አስተዳደር እንዲቋቋም እና ቡድኑ ሙሉ በሙሉ ትጥቅ እንዲፈታ ስምምነት ላይ ተደረሰ።

በደቡብ አፍሪካ ለስምንት ተከታታይ ቀናት ሲካሄድ የነበረው የሰላም ድርድር የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት፣ የግዛት አንድነት እና ዘላቂ ሰላም በሚያረጋግጥ መልኩ በስምምነት መቋጨቱን ከውስጥ ምንጮች የተገኙ መረጃዎች ይጠቁማሉ።

ለሁለት አመታት የዘለቀው የሰሜኑ ጦርነት መቋጫ እንደሚሆን የተገመተ የሰላም ስምንነት ፊርማ በዛሬው እለት በደቡብ አፍሪካ ፕሪቶሪያ በኢትዮጵያና በህወሓት ተደራዳሪዎች መፈረሙን ያስታወቁት ምንጮች ፤ ውይይቱ የሀገራችንን ብሔራዊ ጥቅም ባስጠበቀ፣ የሕግ የበላይነትን ባረጋገጠ እና ለውጭ ጣልቃ ገብነት እድል በማይሰጥ መልኩ በስኬት መጠናቀቁን ገልጸዋል።

ቁልፍ የስምምነት አጀንዳዎች፦

ህወሓት ሙሉ በሙሉ ትጥቅ ለመፍታት መስማማቱን፦ በስምምነቱ መሰረት ከዛሬ ጀምሮ በሰላሳ ቀናት ውስጥ ቡድኑ ሙሉ በሙሉ ትጥቅ እንደሚፈታ፤ ይህንን ውሳኔ ተግባራዊ ለማድረግ የሁለቱ ወገን ከፍተኛ ወታደራዊ አመራሮች በ24 ሰዓት ውስጥ አመቺ ቦታ መርጠው ንግግር ያደርጋሉ፤

ስምምነቱ በተፈረመ አምስት ቀናት ውስጥ የሁለቱ ወገን ወታደራዊ አመራሮች የትጥቅ ማስፈታት ሂደቱ የሚመራበትን ዝርዝር አፈጻጻም በጋራ በማውጣት ተግባራዊ ሥራዎችን መሥራት ይጀምራሉ፤

የሁለቱ ወገን ከፍተኛ ወታደራዊ መኮንኖች በተገናኙ አስር ቀናት ውስጥ ህወሓት ያሉትን ሁሉንም የቡድን እና ከባድ መሣሪያዎች ለመከላከያ ሠራዊት ያስረክባል፤

ስምምነቱ በተፈረመ ሰባት ቀናት ውስጥ የፌደራል መንግሥት መቀሌን ተረክቦ በከተማው ውስጥ እና ዙሪያ ሁሉንም አይነት የጦር መሣሪያ ያስፈታል፤
በአጭር ቀናት ውስጥ አሁን ያለው የህወሓት መዋቅር ፈርሶ የፌደራል መንግሥት የሚመራው የጊዜያዊ አስተዳደር ይቋቋማል። በሚዋቀረው ጊዜያዊ አስተዳደር ውስጥም የትግራይን ሕዝብ የሚወክል አካል ይሳተፋል፤

የሀገር መከላከያ ሠራዊት ከጎረቤት ሀገራት የሚያዋስኑ የድንበር አካባቢዎችን ደኅንነትና ሰላም የሚያረጋግጥ ስምሪት የሚያደርግ ይሆናል። መከላከያ ሠራዊቱ በማንኛውም የትግራይ አካባቢዎች ተንቀሳቅሶ ሕግ የማስከበር ስልጣኑን ከህወሓት ሙሉ በሙሉ ይቀበላል። ህወሓት ለተግበራዊነቱ ምንም አይነት እንቅፋት እንደማይፈጥር ተስማምቷል።

የሚመሰረተው ጊዜያዊ አስተዳደር በሁሉም የትግራይ አካባቢዎች የማኅበራዊ አገልግሎቶች በፍጥነት እንዲጀመሩ ሁኔታዎች ያመቻቻል፤ ተግባራዊነታቸውን ያረጋግጣል፤
ህወሓት ያለ ፌደራል መንግሥት እውቅና ከማንኛውም የውጭ አካል ጋር ግንኙነት ማድረግ ያቆማል። እንዲህ አይነት ተግባር የሚፈጹ ግለሰቦች ካሉ በሀገሪቱ ሕግ የሚጠየቁ ይሆናል።




ሰው ሲታመም የምንጠይቀው ከቋጠሮ ሰሐን ጋር ነው
ሰው ሲታሰር ' እግዚአብሔር ያውጣህ ' የምንለው ከፍትፍት አገልግል ጋር ነው ፣ አራስ የምትጠይቀው ከፔርሙዝ አጥሚት ጋር ነው ፣ እዝንተኛ የምናስተዛዝነው ሰባት እንጀራ ከአንድ ሰሐን ወጥ ጋር ነው ፣ ሟች የምንሸኘው ከገንቦ ጠላና ከለምለም እንጀራ ጋር ነው ፣ ሰዕለታችን በሬ ወይም በግ ነው ...ሰርጋችን ፣ ልደታችን፣ ምርቃችን፣ ሹመታችን፣ አምልኳችን፣ በሚበላ ነገር ሙጥኝ ያሉ ናቸው።

በሽተኛ ስትጠይቅ ከብርቱካንና ከሙዝ ይልቅ መጽሐፍ መውሰድ እንደማላገጥ ይቆጠራል። ጊዜውን ይገፋበት ዘንድ መጽሐፍ ማበርከት በሽተኛው እንዳይድን ከመመኘት እኩል ነው። ለኛ ለኢትዮጵያውያን መጻሕፍት ከባዶ ገበታችን በስተዚያ የተቀመጡ ትርፍ ነገሮች ናቸው። መጻሕፍት የሚያስፈልጉት ገበታችን ሞልቶ ከገነፈለ በኃላ ነው ብለን በይነናል።

ገበታችንም አይሞላ ፤ መጻሕፍቱም አይነሱም። ያልተረዳነው ቢኖር ለገበታ መትረፍረፍ ዙሪያ ጥምጥም ጉዞ መጻሕፍት አቋራጭ መንገድ መሆናቸውን ነው። እንዴት ታዲያ ማንበብ መብላትን ይቅደም? መቼ ይሆን ከምንኮራባቸው ባህሎቻችን በላይ ማንበብ ባህላችን ሆኖ የምንታወቅበት ና የምንኮራበት?......'''''

🔺 አለማየሁ ገላጋይ
ከመረጃ!


ለማታውቁት ዶ/ር አለማየሁ ዋሴ ይባላል። እኔ በግሌ በጣም የምወዳቸውን መፃህፍት የእመጓ፣ የዝጎራ፣የመርበብት እና የሰበዝ መፃሕፍት ደራሲ ነው። የሚኖረውን የሚያስተምር ብርቱ ሰው ነው።ስለሱ የሰማሁትን እውነታዎች ልንገራችሁ፤

በሚሰራበት መስሪያቤት ተብሎ በቦርድ የተወሰነለትን ደመወዝ አልቀበልም ብሎ በደብዳቤ መልሷል።

ከአንድ መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት ውስጥ ለስራ ተወዳድሮ ካለፈ በኋላ፣ ደመወዙ ስለበዛ ቅጥሩን ሰርዞ ያውቃል. ከወር የቤትና የራሱ ወጪ ውጪ ያለውን የባንክ ገንዘቡን በየወሩ ለነዳያንና ለገዳማት ይሰጣል።

የዶክተር አለማየሁ መርህ ምን መሰላችሁ?የራሱንና የቤተሰቡን ኑሮ ስታንዳርድ አበጅቷል።
"ቤት አለኝ" ይልህና፤ "የቤቴን አይነት ግን አትጠይቁኝ"ይልሀል። "መኪና አለኝ" ይልህና፣ "የመኪናዬን አይነት ግን አትጠይቁኝ" ይልሃል። "የምኖረው ከተማ ነው" ይልህና፣"የት ከተማ ግን እንዳትለኝ" ይልሀል።

ምክንያቱም ይላል "ከቤት በላይ ቤት፣ ከመኪና በላይ መኪና፣ከከተማ በላይ ከተማ አለ፤ ከቀበቶ በላይ እንኳን ቀበቶ አለ፣የቀበቶ ስራው ግን ሱሪ እንዳይወልቅ ማድረግ ነው።" ይላል።

ባጠቃላይ ዶክተር አለማየሁ ምኞትን በጥልቅ ጉድጓድ ቆፍሮ የቀበረ፣ የገንዘብን አቅም ያሳነሰ ምርጥ ሰው ነው። ሲናገር እና ሲያስተምር ደግሞ አዝናኝ ነው። የፃፋቸው አስደማሚ መፃሕፍት የሱን ህይወት ቁልጭ አድርገው ያሳያሉ። የኔ የሁልጊዜም ምርጥ ሰው ነው።

ረጅም እድሜ ከጤና ጋር ተመኘሁልህ❤🙏#


#sheger_fm
ተራኪ ተስፋየ ማሞ
ጸሐፊ ሔኖክ ሠጠኝ


በርካታ የግሩፓችን ቤተሰቦች ሲጠይቁት የነበረው የአንባብያን የመወያያ ግሩፕ ይከፈትልን ጥያቄ ዛሬ ተመልሷል 🙂 ሁሉንም አንባብያን የሚያገናኝ ስለሆነ አንባብያን ሃሳባቸውን ከማጋራት ሌላ በርካታ ነገር ሼር ይደራረጉበታል። ወደ ግሩፑ ለመግባት ሊንኩን ይጫኑ

https://t.me/+NehqDsYg38xmNWI0


የዩናይትድ ኪንግደም ጠቅላይ ሚንስትር የነበሩት ዊንስተን ቸርችል ባንድ ወቅት ይህ አስቂኝና ቁም ነገር ገጥሞት ነበር .....

"አንድ ቀን ወደ ቢቢሲ ቢሮ ለቃለ መጠይቅ ለመሄድ ታክሲ ያዝኩኝ፤ቢሮዉ እንደደረስኩ ባለታክሲውን ቃለመጠይቁን ጨርሸ እስክመለስ ለ40 ደቂቃ ያህል እንዲጠብቀኝ ጠየቅኩት።ባለ ታክሲዉም ይቅርታን በማስቀደም "አልችልም ምክኒያቱም እቤቴ ሂጄ ከደቂቃዎች በኋላ ዊንስተን ቸርችል የሚያደርገዉን ቃለመጠይቅ መስማት እፈልጋለሁ።"አለኝ
የእኔን ንግግር ለመስማት ይህን ያህል በመጓጓቱ በጣም ተደነቅሁ፤ ኩራት ቢጤም ተሰማኝ።ማንነቴን ሳልገልፅለት ለታክሲ አገልግሎቱ መክፈል ከሚጠበቅብኝ በላይ መልሱ ስላስደሰተኝ 10 ፓዉንድ ሰጠሁት።ባለ ታክሲዉም የሰጠሁት ብር በደስታ አየቆጠረ"ጌታዬ እስከ ምትፈልገዉ ስዓት ድረስ እጠብቅሃለሁ ሲፈልግ ዊንስተን ቸርችል ገደል መግባት ይችላል!"ብሎኝ አረፈ

ሀሳብ ለብር ሲባል ይቀየራል፣ሀገርን ለብር ሲሉ ይሸጣሉ፣ክብርን ለብር ሲሉ ይሸጣሉ፣ቤተሰብ ለብር ሲባል ይበተናል፣ጓደኞች ለብር ሲሉ ይለያያሉ፣ሰዎች ለብር ሲሉ ክቡር የሆነውን የሰዉ ልጅ ይገድላሉ፣ሰዎች ለብር ሲሉ ባሪያ ይሆናሉ።

ብር....................
Jemal Ahmed Aragaw ገጽ የተወሰደ



20 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.

3 348

obunachilar
Kanal statistikasi