አል አዝካር AL AZKAR


Kanal geosi va tili: Efiopiya, Amharcha
Toifa: Din


እናንተ ያመናችሁ ሆይ አላህን ብዙ ማዉሳትን አዉሱ።{አል አህዛብ፥41}
"አላህ አዋቂም ጥበበኛም ነው"🎨
☞ ኢስላም በራሱ ውበት ነው ፣ ጥበብም ነው።
♢አላህም ቆንጆ የሆኑ ነገሮቸን ሁሉ ይወዳል በሀዲስ ላይ ረሱል ሰ.ዐ.ወ እንዳሰፈሩት:-
 ❤“.. إن الله جميل يحب الجمال ..”♥ ☞
-
-
-
-
-

♡"ያ ረብ ለሰጠከኝ ፀጋ ሁሉ አመሰግናለሁ!"

Связанные каналы

Kanal geosi va tili
Efiopiya, Amharcha
Toifa
Din
Statistika
Postlar filtri


Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር) dan repost
አመጋገበዎን ያስተውሉ
=
1. ሐላል ብቻ ይመገቡ፡፡ ያለበለዚያ በሚመገቡት ይጠየቃሉ፡፡ ዱዐዎትንም አላህ ባይቀበለዎት አይደነቁ፡፡ ስለዚህ የሚመገቡት ነገር ምንጩ ሀላል መሆን አለበት፡፡ ከዚያ ባለፈ ለጤናም፣ ለዲንም፣ ለኢኮኖሚም፣ ለቤተሰብም፣ ለማህበረሰብም ጎጂ የሆነ ነገር ሁሉ ሀራም ነውና ይራቁ፡፡
2. አቀራረቦን ያስተካክሉ፡፡ አንዴ ሁለቴ ያጋጥም ይሁን፡፡ ሁሌ ግን ይበቃል ተብሎ ከሚገመተው በላይ እያቀረቡ ያለጥንቃቄ ነካክቶ መድፋት ከአላህ ዘንድ ያስጠይቃል፡፡ አባካኞች የሸይጧን ወንድሞች ናቸውና፡፡
3. ተስተካክለው ይቀመጡ፡፡ በምግብ ጊዜ ትራስ ላይ መደገፍ፣ መጋደም፣ ወይም ስርኣት የሌለው አቀማመጥ መቀመጥ ወይም ቆሞ መብላት ክልክል ነው፡፡
4. ቢስሚላህ ይበሉ፡፡
5. በቀኝ እጅዎት ይብሉ፡፡ በግራ መብላት የሸይጧን ስራ ነው፡፡ ሲጠጡም እንዲሁ፡፡ እቃው እንዳይጨማለቅ በሚል አጉል ምክንያት በግራ እንዳይጠጡ፡፡ ወይ አስተካክለው ይያዙ፡፡ ያለበለዚያ እቃው ኋላ ይታጠባል እንጂ የሸይጧን ስራ አይስሩ፡፡
6. በሶስት ጣት መብላት ከሱና ነው፡፡ (ግዴታ አይደለም።)
7. ከፊት ከፊቶ ይብሉ፡፡ እዚያም እዚህም መክለፍለፍ ከሱናም ከወግም ያፈነገጠ ነው፡፡
8. ከምግቡ አናት ወይም ከመሀሉ አይጀምሩ፡፡ መሀሉን ይደርሱበት የለ? ምን አናቱን/መሀሉን አስበረቆሰዎት? መናልባት ከመሀል ሳይደርሱ ከበቃዎትም ቀሪውን ሌላ ሰው ሊመገበው ይችላል፡፡ ከመሀል ሲጀመር ግን ለሌላ ሰው ደስ አይልም፡፡
9. በልክ ይብሉ፡፡ ሲበቃው ሳይሆን ሲያመው የሚያቆመው ህፃን ነው፡፡
10. ሲጨርሱ ጣትዎን ይላሱ፡፡ አንዳንድ በዚህ ሱና የሚያፍር አለ፡፡ ጠላ እሚጠጣ፣ አሳማ የሚበላ፣ እስቲንጃ የማያደርግ ሰው ሳቀብኝ ብሎ ሱናን መተው እንዴት አይነት አሳፋሪ ነገር ነው?! አንዳንዱማ ጭራሽ አስቂኝ ነው፡፡ “እጅን መላስ ያስጠላል” ይላል፡፡ የበላህበትን እጅ መላስ ከደበረህ በሪሞት ኮንትሮል ብላ ወይ ደግሞ ምግቡን ጭራሽ ቶወው፡፡ አጂነብይ ሲጨብጡ አያፍሩም አይደብራቸውም። ሲዘፍኑ፣ ሲያዳምጡ አያፍሩም አይደብራቸውም። ወለድ ሲበሉ አያፍሩም አይደብራቸውም። … ሱና ለመተግበር ግን ያፍራሉ፣ ይደብራቸዋልም፡፡ ከእንዲህ አይነት የተገለበጠ አሰተሳሰብ አላህ ይጠብቀን፡፡
11. ሲጨርሱ አላህን ያመስግኑ፡፡
12. ተጋብዘው ከሆነ ለጋበዘዎት ዱዐ ያድርጉ፡፡
13. ውሃ ሲጠጡ ይቀመጡ፡፡ ቆመው አይጠጡ፡፡
14. እንደማንቆርቆሪያ ባለ ነገር ሲጠጡ በጡቱ አይጠጡ፡፡ በጡቱ የሚመጣውን ውሃ ንፁህነት ማረጋገጥ አይቻልምና፡፡
15. የሚጠጡበት እቃ ውስጥ አይተንፍሱ፡፡ ለተመልካችም ያስጠላል። በሽታ የመተላለፍ እድሉም ሰፊ ነው፡፡ እንዲያውም በሶስት እስትንፋስ እያረፉ መጠጣት ሱና ነው፡፡ ሱናውን እኛ ካልሰራነው ማን ይስራው?
-
(ኢብኑ ሙነወር፣ 20/2/2005)
የቴሌግራም ቻናል፦
https://t.me/IbnuMunewor


🔷 ሐራምን መዳፈር

ኢስላም በማያሻማ መልኩ ከደነገጋቸው ህግጋቶች አንዱ የምስል ወይም ፎቶ ሐራምነት ነው ። ዛሬ ተውሒድ እናስተምራለን የሚሉ ወንድሞች ጭምር እየተዳፈሩትና እንደ ቀላል እያዩት ቻናላቸው የምስል ማስታወቂያ መለጠፊያ ሰሌዳ እስከሚመስል ድረስ የሴትና የወንድ ምስል ወይም የሚደንሱ ሴቶችን ምስል ማዥጎርጎሪያ እያደረጉት ነው ። ይህ ተግባር ሸሪዓን የሚፃረር የምናስተምረውን ተውሒድ የሚነካ ወደ ሽርክ የሚያዳርስን ሙንከር ማሰራጨት በመሆኑ አላህን ልንፈራ ይገባል ። ፎቶም ሆነ ምስል በየትኛውም መልኩ የተከለከለ መሆኑ የሰዎች ኢጅቲሃድ ሳይሆን ከልብ ወለዳቸው ከማይናገሩት የአላህ መልእክተኛ – ሶለላሁ ዓለይሂ ወሰለም – በወሕይ አማካይነት ለቁጥር በሚያታክቱ ሐዲሶች የተረጋገጠ ነው ። የተኛውም ምስል ይቻላል የሚል ዓሊም ምንም ነብያዊ ማስረጃ የለውም ። ምናልባት ደሩራ ነው የሚል ነው የሚሆነው ። ያ ደግሞ በደሩራው ልክ የሚታይ ነው ። የትኛውም አማኝ የአላህ መልእክተኛ እንዲህ ብለዋል ሲባል ሸኽ እገሌ እንዲህ ብለዋል ሊል አይገባም ። ይህን በተመለከተ የሰለፎችን ንግግር እንመልከት : –
قال ابن عباس – رضي الله عنه – :
" يوشك أن تنزل عليكم حجارة من السماء ، أقول: قال: رسول الله – صلى الله عليه وسلم – وتقولون : قال أبو بكر وعمر؟ "
أخرجه الإمام أحمد ( 3121 )
🔹 ዐብዱላሂ ኢብኑ ዓባስ እንዲህ አሉ: – ከሰማይ የድንጋይ ናዳ ሊወርድባችሁ የደረሰ ይመስላል , የአላህ መልእክተኛ ብለዋል እያልኳችሁ አቡበከርና ዑመር ብለዋል ትላላችሁን ? !!!!!!
ሱብሃናላህ ኢብኑ ዓባስ ዑመርና አቡበከር ብለዋል ስለተባሉ ነው ይህን ያሉት ። ባዮቹ መረጃውን ባለማወቃቸው ነው እንጂ የተነሳው የተመቱዕ መስአላ መረጃ የሌለው ሆኖ አይደለም ። ነገር ግን ከኢብኑ ዓባስ ጋር የተነጋገሩት መረጃውን ሳያቀርቡ አቡበከርና ዑመር ብለዋል ማለታቸው ነው ያስቆጣው ። አቡበከርንና ዑመርን እንድንከተል ታዘን እያለ ። ነገር ግን ነስ ከመጣ መቆም ግዴታ መሆኑን ለመግለፅ ነው ።
ሌላው አሰር እንዲህ ይላል : –
قال الإمام أحمد : عجبت لقوم عرفوا الإسناد وصحته ، ويذهبون إلى رأي سفيان ، والله تعالى يقول:
{ ۚفَلْيَحْذَرِ الَّذِينَ يُخَالِفُونَ عَنْ أَمْرِهِ أَن تُصِيبَهُمْ فِتْنَةٌ أَوْ يُصِيبَهُمْ عَذَابٌ أَلِيم ٌ}
النور ( 63 )
أتدري ما الفتنة ؟ الفتنة الشرك . لعله إذا رد بعض قوله أن يقع في قلبه شيء من الزغ فيهلك .
🔹 ኢማሙ አሕመድ እንዲህ ይላል : –
" የሰዎች ሁኔታ አስደነቀኝ ( አስገረመኝ) ሐዲስን ሶሒህነቱ ቃወቁ በኋላ ወደ ሱፍያን አስሰውሪ ረእይ ይሄዳሉ , አላህ እንዲህ እያለ
" እነዚያም ትዕዛዙን የሚጥሱ መከራ እንዳትደርስባቸው ወይም አሳማሚ ቅጣት እንዳያገኛቸው ይጠንቀቁ ፡፡"
ፈተና ( መከራ ) ማለት ምን እንደሆነ ታውቃለህን ? ፈተና ማለት ሽርክ ነው ። የነብዩን ከፊል ንግግር ከመለሰ በልቡ ላይ አንዳች ጥመት ይከሰትና እንዳይጠፋ ይፈራል "
ይህ ማለት ሐዲስ መጥቶለት እገሌ እንዲህ ብሏል ከሚል ሰው ጋር ሰለፎች የነበራቸው አቋም ነው ።
አሁን የአላህ መልእክተኛ በፎቶና ምስል ዙሪያ ከተናገሯቸው ሐዲሶች ጥቂቶቹን እንመልከት : –
روى البخاري ومسلم عن عائشة عن رسول الله صلى الله عليه وسلم أنه قال : «أشدّ الناس عذاباً يوم القيامة الذين يضاهئون بخلق الله "
🔹 ቡኻሪና ሙስሊም በዘገቡትና እናታችን ዓኢሻ ባወራችው ሐዲስ የአላህ መልእክተኛ እንዲህ ብለዋል ትላለች : –
" የቂያማ ቀን ብረቱ ቅጣት የሚያገኘው እነዚያ በአላህ አፈጣጠር የሚያመሳስሉ ናቸው "
روى البخاري ومسلم وأصحاب السنن أن النبي صلى الله عليه وسلم قال :
«إن اصحاب هذه الصور يعذبون يوم القيامة، يقال لهم: أحيو ما خلقتم».
🔹 ቡኻሪና ሙስሊም እንዲሁም የሱነን ባልተቤቶች በዘገቡት ሐዲስ የአላህ መልእክተኛ እንዲህ ብለዋል ይላሉ: –
" የእነዚህ ምስል ባልተቤቶች የቂያማ ቀን ይቀጣሉ, የፈጠራችሁትን ህያው አድርጉ ይባላሉ "
روى البخاري ومسلم والنسائي عن ابن عباس رضي الله عنهما أن رجلاً قال له: إني أصوّر هذه الصور فأفْتني فيها، فقال له: ادن مني فدنا، ثم قال: ادن مني فدنا، حتى وضع يده على رأسه وقال: إنبئك بما سمعت من رسول الله صلى الله عليه وسلم، سمعته يقول: «كلّ مصوّر في النار، يُجعل له بكل صورة صوّرها نفس فيعذب به في جهنم».
وفي رواية أخرى عنه: سمعته يقول:
«من صوّر صورة فإنّ الله يعذبه حتى ينفخ فيها الروح وليس بنافخ فيها أبداً»
🔹 ቡኻሪና ሙስሊም እንዲሁም ኢማሙ ነሳኢ በዘገቡትና ዐብዱላሂ ኢብኑ ዓባስ ባወሩት ሐዲስ አንድ ሰው ለኢብኑ ዐባስ እንዲህ አላቸው እኔ ይህን ምስል እስላለሁ እስኪ ፈትዋ ስጠኝ ። ኢብኑ ዐባስም ወደኔ ቅረብ አለው ቀረበ አሁንም ቅረብ አለው ቀረበም እጁ በጭንቅላቱ ላይ እስከሚያደርግ ድረስ ከዛም ከአላህ መልእክተኛ የሰማሁትን እነግርሃለሁ አለው ። የአላህ መልእክተኛ እንዲህ ሲሉ ሰምቻለሁ : –
" ምስል የሚስል ሁሉ የእሳት ነው ። በየአንዳንዱ የሳለው ምስል ነፍስ ይደረግለታል በሱም በጀሀነም ይቀጣል ። " በሌላ ዘገባ ላይ ደግሞ እንዲ ብለዋል
" አንድን ምስል የሳለ ሰው ሩሕ እስከሚነፋበት ድረስ አላህ ይቀጣዋል ። እስከመጨረሻውም ሩሕ የሚነፋ አይደለም "
እነዚህ ሐዲሶች ከብዙ በጥቂቱ ናቸው ። እንደምታዩት እንደ ጠዋት ፀሀይ ፍንትው ብለው የሚታዩ የፎቶ ወይም ምስል በየትኛውም መልኩ ክልክልነት የሚያረጋግጡ ሲሆኑ እነዚህን ሐዲሶች ትቶ ከስሜት ጋር የሚሄድ የዑለማዎች ንግግር መፈለግ የሰለፍዮች መገለጫ አይደለም ። በተለይም ወደ ተውሒድ የሚጣራ ሰው የዚህ ዛቻ ማረፈያ የሆነውን ምስል ከማሰራጨትና ሐላል ነው ብሎ ከመሞገት ሊቆጠብ ይገባል ። እንኳን እንዲህ አይነት መረጃ የመጣበትን ጉዳይ አይደለም የሚያጠራጥር ነገር ከሆነ እንኳን መጠንቀቁ የዲንንም የራስንም ክብር መጠበቅ ነው ። አላህ ከስሜት ወጥተን ሐቅን የምንከተል ያድርገን ።


ሶላት ለማይሰግድ ሰው አሳሳቢ ምክር‼️
==========================
✍ ወንድሜ ሆይ!
«ሶላትን በፍጹም እንዳትተው። በዚህ ወቅት ከቀብር ስር ሁነው ህይዎት ወደነርሱ ብትመለስላቸው አንድትን እንኳ ሱጁድ ለአላህ ማድረግ የሚመኙ ሚሊዮኖች ይገኛሉ።»

ታዲያ አንተ ኋላ ከምድር ስር ሁነህ እንደነርሱ ከምትመኝ፤ ዛሬ ከምድር በላይ ሳለህ አላህ ከሰጠህ 24 ሰዓት ውስጥ 1 ሰዓት እንኳ ለርሱ መስጠት ለምን ከበደህ⁉️
ኋላ ከመለደም አስተንትን!
ኋላ ብትጸጸትም ትርጉም የለውም።


✨✨✨ 💥💥💥 ✨✨✨

🌷የአንድ ባራያ ወንጀል የቱንም ያህል ቢገዝፍ
የአሏህ መሃርታ ከባሪያው ወንጀል የበለጠ ግዙፍ ነው !
[ ኢብን ረጀብ ]
°
🔸ወዳጄ ከሰራኸው ወንጀል በላይ
በአሏህ ላይ ተስፋ መቁረጥህ
የበለጠ ዋጋ ያስከፍልሃል ፡፡
°
🔹ምክንያቱም ተስፋ መቁረጥ የሚመነጨው
የአሏህን መሃሪነት ከማስተባበል አልያም
የአሏህን መሃሪነት ካለማወቅ ነውና !
°
🔸ለዚህም ነበረ አባታችን ኢብራሂም ( ዐለይሂ ሰላም ) ከሸበቱና ከጃጁ ወዲያ መላዕክቶች በልጅ ሲያበስሯቸው ...
" قَالَ أَبَشَّرْتُمُونِى عَلَىٰٓ أَن مَّسَّنِىَ ٱلْكِبَرُ فَبِمَ تُبَشِّرُونَ "
« እርጅና የደረሰብኝ ከመኾኔ ጋር አበሰራችሁኝን በምን ታበስሩኛላችሁ » አለ ፡፡
[ ሱረቱል ሂጅር 54 ]

🔹የዚህኔ መላዒካዎችም ቀበል አደረጉና
" قَالُوا۟ بَشَّرْنَٰكَ بِٱلْحَقِّ فَلَا تَكُن مِّنَ ٱلْقَٰنِطِينَ "
« በእውነት አበሰርንህ ፡፡ ከተሰፋ ቆራጮችም አትኹን » አሉ ፡፡
[ ሱረቱል ሂጅር 55 ]
ከዚያም ደጉ አባታችን ኢብራሂም ( ዐለይሂ ሰላምም ) መለስ አሉና ....

" قَالَ وَمَن يَقْنَطُ مِن رَّحْمَةِ رَبِّهِۦٓ إِلَّا #ٱلضَّآلُّونَ "
« #ከጠማማዎችም በስተቀር ከጌታው እዝነት ተስፋን የሚቆርጥ ማነው» አለ ፡፡
°
ተመለከታችሁ ....?
አባታችን ኢብራሂም ( ዐለይሂ ሰላም ) ተስፋ የሚቆርጥ አካል " መንገድ የሳተ ጠማማ ነው " እያሉን ነው ፡፡ ምክንያቱም ይህ አካል የአሏህን ትክክለኛ ማንነትን ( መሃሪነትን ) አላወቀምና ፡፡ የአሏህን ማንነት ያላወቀና አውቆም ያላመነ " መንገድ የሳተ " ይባላል !
°
💠 እናም ............. ተስፋ አትቁረጡ !!
🍂..


Video oldindan ko‘rish uchun mavjud emas
Telegram'da ko‘rish
⚠️ ምስክርነት በራስ በቃ
وشهد شاهد من اهلها

📛 ሙፍቲ ኡመር ገነቴ በራሳቸው አንደበት እውነታውን እንዲህ በማለት ይመሰክራሉ

🔸 መውሊድን የጀመረው መሊከል ሙዘፈር ነው !!

🔸 ትክክለኛው ሱና ሰኞ ሰኞ መፆም ነው

🔸 መብላት መጠጣት መሰብሰብ የነብዩ ሱና አደለም

🔸 ትክክለኛው ሱና ረሱልን መከተል የፈለገ መሰብሰብ መብላት መጠጣት አደለም ሰኞ ሰኞ መፆም ነው !

🔹እኛም እንጠይቃል ታዲያ የማንን ሱና እንከተል የረሱልን ሱና ወይስ ረሱል ከሞቱ ከ 600 ዓመት በሃሏ የተፈጠረውን ?

🔹ረሱል ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም በየሳምንቱ ጁምኣ አደራቹን አዲስ ነገር በዲን ላይ ከመፍጠር ተጠንቀቁ ብለው አላሳሰቡም ለምን የረሱልን ቃል አናከብርም ?

🔹 አመት ጠብቆ ተሰብብቦ መብላት ፣ መጠጣት ፣ መጨፈር ይህ የረሱል ሱና ካልሆነ ለምን ይፈፀማል አላህ ያዘዘን ረሱልን አደንድንከተል አይደለምን ?

🔘 " የዛኔ (በሰሃባዋች ግዜ) ዲን ያልነበረ ነገር አሁን ዲን ሊሆን አይችልም " ኢማሙ ማሊክ




ሰያ ስክሪን dan repost
ዐቂቃ ሌላ ለመውሊድ ሌላ!
~ ~ ~ ~ ~ ~~~~ ~
ከዚህ ቀደም እንደገለፅኩት የመውሊድ ጨፋሪዎች የማይገናኘውን ሁሉ ለዚህ የቢድዐ ድግስ ማስረጃ ለማድረግ ሲውተረተሩ ማየት የተለመደ ነው። በዚህ ረገድ ክሚያነሷቸው ከሸረሪት ድር የደከሙ ብዥታዎች ውስጥ አንዱ ነብዩ ﷺ ከነብይነታቸው በኋላ ለራሳቸው “ዐቂቃ አድርገዋል” የሚል ነው። “ህፃን እያሉ አቡ ጧሊብ ዐቂቃ እንዳደረጉላቸው ስለሚታወቅ ይህኛው ልደታቸውን በማስመልከት አላህን ለማመስገንና ለተከታዮቻቸውም ይህንኑ ለማስተማር ያደረጉት እንደሆነ ይታሰባል” ይላሉ በድፍረት።

መልስ፡-

1. በመጀመሪያ ሐዲሡ ብዙሃን ዑለማእ ዘንድ ደካማ ነው። ይህንንም በርካታ ዑለማዎች አስረግጠው ጠቁመዋል። ለምሳሌ፦

1.1. የሐዲሡ ዘጋቢ የሆኑት በይሀቂ እራሳቸው ስለ ሐዲሡም ስለ ሰውየውም እንዲህ ብለዋል፡- “ዐብዱረዛቅ እንዲህ ብሏል፡ ዐብዱላህ ብኑ ሙሐረርን የተውት በዚህ ሐዲሥ ሁኔታ ነው። በርግጥ በሌላ በኩል ከቀታዳ ይዞ፣ በሌላ ደግሞ ከአነስ ዘግቦታል። ነገር ግን እዚህ ግባ የሚባል አይደለም። ውድቅ የሆነ ሐዲሥ ነው።” [አሱነኑል ኩብራ፡ 9/300] ተመልከቱ እንግዲህ ዘጋቢው እራሳቸው በዚህ መልኩ ያጣጣሉትን ጉዳይ ቁም ነገር አርገው የሚጠቅሱት። አንዳንዶቹማ አይናቸውን በጨው አጥበው በይሀቂ ይህንን ሐዲሥ ለመውሊድ ማስረጃ አድርገው ጠቅሰውታል ብለዋል። ይሄ የለየለት ቅጥፈት ነው።
1.2. ሐዲሡን ኢማሙ ማሊክም ደካማ እንዳሉት ኢብኑ ሩሽድ ገልፀዋል። [አልሙቀደማቱል ሙመሂዳት፡ 15/2]
1.3. ኢማሙ አሕመድ ይህንን ሐዲሥ ሙንከር እንዳሉት፣ ሰውየውንም ደካማ እንዳሉት ኢብኑል ቀዪም ገልፀዋል። [ቱሕፈቱል መውዱድ፡ 57]
1.4. ቡኻሪም ሰውየውን “የተተወ ነው” ብለውታል። [ፈትሑል ባሪ፡ 3/348]
1.5. አልበዛርም ሰውየው ደካማ እንደሆነ ገልፀዋል። [ከሽፉል አስታር ሚን ዘዋኢዲል በዛር]
1.6. ነወዊም “(ባጢል) ውድቅ የሆነ ሐዲሥ ነው” ብለዋል። [አልመጅሙዕ ሸርሑል ሙሀዘብ፡ 8/412]
1.7. ዘሀቢም የሐዲሡን አስተላላፊ ዐብዱላህ ብን ሙሐረርን በከባዱ ያብጠለጠሉ ሙሐዲሦችን ከዘረዘሩ በኋላ “ከጥፋቶቹ ውስጥ ከቀታዳ ከአነስ ብኑ ማሊክ ብሎ ነብዩ ﷺ ከተላኩ በኋላ ለራሳቸው ዐቂቃ አድርገዋል ማለቱ ነው።” ይላሉ፡- [ሚዛኑል ኢዕቲዳል፡ 2/500]
1.8. ኢብኑ ዐብዲል ሃዲ ደካማ እንደሆነ ገልፀዋል። [ሪሳለቱን ለጢፋህ፡ 54]
1.9. ኢብኑ ሐጀርም ሐዲሡ ደካማ እንደሆነ ገልፀዋል። [ፈትሑል ባሪ፡ 9/509]
1.10. ኢብኑል ሙለቀንም “ሐዲሡ በጣም ደካማ ነው ምክንያቱም ይሄ ዐብደላህ በምሁራን ኢጅማዕ በጣም ደካማ ነውና” ይላሉ። [አልበድሩ ልሙኒር፡ 9/339]
1.11. ሸውካኢም ዶዒፍነቱን ጠቁመዋል። [ነይሉል አውጣር፡ 5/228]
1.12. አልሙባረክፑሪም እንዲሁ ሐዲሡ ሶሒሕ እንዳልሆነ ገልፀዋል። [ቱሕፈቱል አሕወዚ፡ 5/97]
ይህ ሁሉ ሂስ ከመሰንዘሩም ጋር ሐዲሡን የተወሰነ ዋጋ የሰጡት አጋጥመዋል። ለምሳሌ ሸይኹል አልባኒ።

2. ነገር ግን ሶሒሕ ነው ብንል እንኳን ዛሬ ለሚፈፀመው የቢድዐ መውሊድ ፈፅሞ መረጃ መሆን አይችልም። ምክንያቱም በሐዲሡ የተጠቀሰው ዐቂቃ እንጂ መውሊድ አይደለምና!! ቃል በቃል ሐዲሡ ውስጥ የተጠቀሰውን ጥሎ ያለ ተጨባጭ መረጃ በሌለበት “ድሮ አያታቸው ዐቂቃ ስላወጡላቸው ይሄኛው መውሊድ ነው” ማለት ከንፁህ ጥናት ያፈነገጠ ስሜት የተጫነው ድምዳሜ ነው። ከጥንት ጀምሮ ዑለማዎች ይህንን ሐዲሥ ያሰፈሩትና ያጠኑት ቀድሞ ዐቂቃ ያልወጣለት ሰው ኋላ በራሱ መፈፀም ይችላል ወይስ አይችልም በሚል ጉዳይ ላይ እንጂ ፈፅሞ ለመውሊድ አይደለም።

3. የሰነዱ አጠያያቂነት እንዳለ ሆኖ እሳቸው የፈፀሙት በህይወታቸው አንዴ ብቻ ነው። እናንተ መውሊድ ብላቸሁ የምትሰባሰቡት በያመቱ ነው። ምኑን ከምኑ ነው የምታገናኙት?

4. ደግሞስ ዐቂቃ የልደት በዓል ነውንዴ? ሰዎቹ ዐቂቃና መውሊድ አይለዩም ማለት ነው? ዐቂቃኮ አቅሙ የሚችልን ሙስሊም ሁሉ የሚመለከት እርድ እንጂ በነብዩ ﷺ ላይ የተገደበ አይደለም። ለመሆኑ ለህፃናት የሚታረደውን ዐቂቃ መውሊድ ብላችሁ ነው እንዴ የምትጠሩት? ዐቂቃውን የልጆቹን የልደት ቀናቸውን እየጠበቃችሁስ ነው የምትፈፅሙት? አንዴ ካረዳችሁ በኋላ በያመቱስ ነውንዴ የምታከብሩት?

5. ደግሞስ ነብዩ ﷺ ዐቂቃውን የፈፀሙት በልደት ቀናቸው ነው ወይም ረቢዑል አወል 12 ነው የሚለውን ከየት ነው ያመጣችሁት? እንዲህ አይነት ጥቆማ በሌለበት በምን ስሌት ነው ለመውሊድ ማስረጃ የሚሆነው?

6. እውነት እንደምትሉት ነብዩ ﷺ ዐቂቃውን ያደረጉት ተከታዮቻቸው መውሊድን እንዲያከብሩ ለማስተማር ከሆነ ምነው ታዲያ ሶሐቦች እርድ እየፈፀሙ በያመቱ መውሊዳቸውን ሳያከብሩት ቀሩ? መቼም እንደ ሺዐዎች ስላፈነገጡ ነው እንደማትሉ ተስፋ እናደርጋለን። ስላልተመቻቸው ነው ማለት የለየለት ቅጥፈት ነው። ከነብዩ ﷺ ሞት በኋላኮ አንድና ሁለት አመት አይደለም የኖሩት!! ያን ሁሉ ዘመን ሁሉም ሶሐባ አልተመቸውም ይባላል። ሁለቱን ዒዶች ሲያከብሩ አልነበር? ሌሎች ዲናዊ ተግባራትን ሲያከናውኑ አልነበር? እነሱም፣ ታቢዒዮቹም፣ አትባዑ ታቢዒንም፣ የሐዲሥ ምሁራንም፣ አራቱ ኣኢማዎችም አለማክበራቸው ምንድነው የሚያሳየው? “አክብረውትስ ቢሆን ምን አሳወቀን?” እንዳትሉ በነዚያ ነብዩ ﷺ ምርጥነታቸውን በመሰከሩላቸው ትውልዶች ዘመን መውሊድ የሚባል እንዳልነበረ ኢብኑ ሐጀር፣ ሰኻዊ፣ ሲዩጢ፣ ዒራቂ፣ ተዝመንቲ፣... መናገራቸውን አሳልፌያለሁ። ፈርተው ነው ያልፈፀሙት ማለትም አይን ያወጥዐ ቅጥፈት ነው። ምክንያቱ አንድና አንድ ብቻ ነው። መውሊድ የሸሪዐ መሰረት ስለሌለው ብቻ! ይህ ነው እነሱ ጋር የነበረው ግንዛቤ!! እንጂ የሸሪዐ መሰረት ቢኖረው ኖሮ ለእምነታቸው ሲሉ አገር ንብረታቸውን ጥለው የተሰደዱ፣ ህይወታቸውን አሳልፈው የሰጡ፣ ከስጋ ዘመዶቻቸው ጋር የተሞሻለቁ፣ በሕቅ ላይ የወቃሽን ወቀሳ የማይፈሩ፣ የጀኝነት፣ የቆራጥነት፣ የተቅዋ፣ ... ተምሳሌቶች ናቸው። ለነብዩ ﷺ የነበራቸውም ወዴታ ወደር አልነበረውም። በጭፈራ ሳይሆን በተግባር የሚገለፅ ነበር። ከሳቸው በመከላከል ለነፍሶቻቸው ሳይሰስቱ እራሳቸውን ፊዳ በማድረግ ደረታቸውን ለቀስት የሚሰጡ የተመረጡ ትውልዶች ናቸው። ይልቅ በተዘዋዋሪም ቢሆን አጉል ከነሱ በላይ ነብዩን ﷺ እንወዳለን ከሚመስል እብሪት ብትርቁ ይሻላችኋል።
~~

ኢብኑ ሙነወር
የቴሌግራም ቻናል፦
https://t.me/alazkare
https://t.me/alazkare


ሰያ ስክሪን dan repost
ያቁት አልሐመዊ ከሙዞፈር ጋር አንድ ዘመን የኖሩ በመሆናቸው ዘግይተው መጥተው ስለ ንጉሱ አድናቆት ብቻ ከሰፈሩ ፀሐፊዎች በተሻለ ምስክርነታቸው ሚዛን የሚደፋ ነው፡፡ በነገራችን ላይ ሙዞፈር ፃድቅ እንኳ ቢሆን፣ አይደለም እንጂ መውሊድ በሱ የተጀመረ ቢሆን እንኳ ይሄ ከቢድዐነት አያወጣውም፡፡ ከነቢዩ - ﷺ - ህልፈት በኋላ ስድስት መቶ አመታት ዘግይቶ የሚጀመር አዲስ ፈሊጥ ጥመት እንጂ ፈፅሞ ፅድቅ ሊሆን አይችልም፡፡ እምነታችን ከቁርኣንና ከሐዲሥ የሚቀዳ እንጂ እንደ ሌሎች እምነቶች ማንም እየተነሳ አዳዲስ ነገሮችን የሚለጥፍበት አይደለም፡፡

Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
(ጥቅምት 08/2013)
የቴሌግራም ቻናል። ይቀላቀሉ። ሌሎችንም ይጋብዙ።


ሰያ ስክሪን dan repost
መውሊድ በማን ተጀመረ? በሙዞፈር ወይስ በ“ፋጢሚያ” ሺዐ?
~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~
ሰሞኑን አሕባሾች መውሊድን በማስተዋወቅ ላይ ተጠምደው እያየን ነው። ከሚያነሷቸው ነጥቦች አንዱ መውሊድ “ታላቅ ዓሊም፣ ተቂይ፣ ሷሊሕና ጀግና በነበሩት” ንጉስ ሙዞፈር ነው የተጀመረው የሚል ነው። ሙዞፈር የሞተው ከ812 አመት በፊት በ630 ሂጅሪያ ነው። ሰዎቹ ሙዞፈር ላይ ችክ የሚሉት እጅግ አፈንጋጭ በሆኑት “ፋጢሚያ” ሺዐዎች ነው የተጀመረው የሚለውን ለመሸሽ ነው። እርግጥ ነው መውሊድ የተጀመረው በሙዞፈር ነው ያሉ አሉ። ሌሎች ደግሞ የለም ትንሽ ቀደም ብሎ በሸይኽ ዑመር አልመላ (571 ሂ.) ነው የሚሉም አሉ። ሁለቱም ሃሳቦች ግን በማንም - እደግመዋለሁ - በማንም ቢጠቀሱ ፈፅሞ ስህተት ናቸው፡፡ ምክንያቱም ከዚያ በፊት በአፈንጋጭ ሺዐዎች እንደተጀመረ የሚያሳዩ ተጨባጭ ማስረጃዎች አሉና፡፡ ማስረጃ ከቀረበ በኋላ ለማንም ሙግት እጅ አንሰጥም፡፡ ለሐቅ እጅ ለሚሰጡ፣ ከመንጋዊ አስተሳሰብ አግልለው ህሊናቸውን ለሚያከብሩ ሰዎች ብቻ ማስረጃዎቹን አሰፍራለሁ።

1. ኢብኑል መእሙን (587 ሂ.):—

በታሪክ ድርሳናት ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ መውሊድ ተጠቅሶ የተገኘው በኢብኑል መእሙን ስራ ነው። የኢብኑል መእሙን አባት የ“ፋጢሚያ” ንጉስ ከፍተኛ ባለሟል ነበር። የታሪክ ፀሐፊው አልመቅሪዚ (845 ሂ.) ኢብኑል መእሙንን በማጣቀስ በ517 ሂጅሪያ የተካሄደውን መውሊድ አስመልክተው እንዲህ የሚል መረጃ አስፍረዋል፡-
“የ‘ፊጢሚያ’ ገዢዎች በዓላትና ለተገዢዎቻቸው ነገሮችን ሰፋ የሚያደርጉባቸው እንዲሁም ችሮታ የሚበዘባቸው ዓውደ-አመታት” ካሉ በኋላ እንዲህ ይላሉ፡- ለፋጢሚያ ገዢዎች በአመቱ ውስጥ በዓላትና ዓውደ አመታት አሏቸው። እነሱም … የዓሹራእ ቀን፣ የነብዩ - ﷺ - ልደት (#መውሊድ) ቀን፣ የዐሊይ ብኑ አቢ ጧሊብ ረዲየላሁ ዐንሁ ልደት ቀን፣ የሐሰን የልደት ቀንና የሑሰይን የልደት ቀን (ሰላም በነሱ ላይ ይሁንና)፣ የፋጢመቱ ዘህራእ ዐለይሃ ሰላም ልደት ቀን፣ ስልጣን ላይ ያለው ገዢ የልደት ቀን፣ … የገዲር ዒድ (የሺዐዎች ነው)” እያሉ ይዘረዝራሉ። ከውስጣቸው የፋርስ መጁሳዎች፣ የሺዐና ከክርስትና ደግሞ እንደ ገና እና ትንሳኤ ያሉ በዓላት የተካተቱበት ሲሆን ባጠቃላይ 28 በዓላት ናቸው የተዘረዘሩት። [አልኺጦጥ፡ 1/436]
መውሊድ ከምን አይነት በዓላት ጋር እንደተጀመረ ተመልከቱ። በሌላ ኪታባቸው ላይም “በረቢዐል አወል ላይ (የ“ፋጢሚዮቹ” ንጉስ) ሌሊት ላይ በጎዳናዎችና መንገዶች ላይ ጧፎች እንዲበሩ ያስገድድ ነበር” ይላሉ። [ኢቲዒዙል ሑነፋእ፡ 2/48] ሌላ ቦታ ደግሞ “ረቢዐል አወል ላይ የነብዩን - ﷺ - ክቡር ልደት መፈፀም ብሄራዊ ልምድ ሆኖ ቀጠለ” ይላል። [ኢቲዒዙል ሑነፋእ፡ 3/101] ልብ በሉ! ይህንን መረጃ የሰጠን ኢብኑል መእሙን የሞተው መውሊድን ጀመረ የሚባለው ንጉስ ሙዞፈር ገና በተሾመ በአመቱ ነው፡፡ እያስተዋላችሁ!!

2. ኢብኑ ጡወይር (617 ሂ.):—

ሌላኛው መውሊድን ከ“ፋጢሚዮች” ጋር በማያያዝ የጠቀሰው ጥንታዊ የታሪክ ፀሐፊ ኢብኑ ጡወይር ነው። ኢብኑ ጡወይር ለነዚህ “ለፋጢሚያ” መንግስት ፀሐፊ ሆኖ አገልግሏል። ኋላ በሶላሑዲን አልአዩቢ ሲደመሰሱም በአይኑ ተመልክቷል። በዚህኛው ስርኣትም ውስጥ ዳግም አገልግሏል። በ“ፋጢሚያዎች” መንግስት ስለሚዘጋጀው መውሊድና ስለተትረፈረፈ ምግቡ “ኑዝሀቱል ሙቅለተይን ፊ አኽባሪ ደውለተይን” በተባለ ኪታቡ ላይ በዝርዝር አትቷል። “ማን ያውራ የነበረ፣ ማን ያርዳ የቀበረ” ይላል ያገራችን ሰው። ለናሙና ያክል ቀንጨብ ላድርገው፡-
ذكر جلوس الخليفة في الموالد الستة في تواريخ مختلفة، وما يطلق فيها، وهي مولد النبي صلى الله عليه وسلم، ومولد أمير المؤمنين علي بن أبي طالب، ومولد فاطمة عليها السلام، ومولد الحسن، ومولد الحسين عليهما السلام، ومولد الخليفة الحاضر
“ኸሊፋው በተለያዩ ጊዜያት በስድስቱ መውሊዶች ላይ የሚያደርጋቸውን መስሰየምና ምን ተብለው እንደሚታወቁ ማውሳት፡- እነሱም የነብዩ- ﷺ - መውሊድ፣ የአሚረል ሙእሚኒን ዐሊይ ብኑ አቢ ጧሊብ መውሊድ፣ የፋጢማ ዐለይሃ ሰላም መውሊድ፣ የሐሰን መውሊድ፣ የሑሰይን - ዐለይሂመ ሰላም - መውሊድና የዘመኑ ኸሊፋ መውሊድ ናቸው፡፡ …” [ኑዝሀቱል ሙቅለተይን፡ 217-219]

3. አሕመድ ብኑ ዐሊይ አልቀልቀሸንዲ (821 ሂ.):—

ስለ “ፋጢሚያ” መሪዎች ጉባዔ ሲያወሩ “ሶስተኛው ጉባዔ በረቢዐል አወል ወር 12ኛ ቀን ላይ በነብዩ - ﷺ - መውሊድ ላይ የሚኖረው ጉባዔ ነው” ካሉ በኋላ ዝርዝር አፈፃፀሙን ይተርካሉ፡፡ [ሱብሑል አዕሻ፡ 3/576]

ስናጠቃልል የመውሊድ በዓል ጀማሪዎች “ፋጢሚያ” ሺዐዎች እንደነበሩ ለጥርጣሬ ቀዳዳ የማይሰጡ መረጃዎች አሉን ማለት ነው፡፡ ልብ በሉ! የመጨረሻው የ“ፋጢሚዮች” ንጉስ አልዓዲድ ሊዲኒላህ የሞተው በ 567 ሂጅሪያ ነው፡፡ ሱፍዮች “መውሊድ ጀመረ” የሚሉት ሙዞፈር የተሾመው ደግሞ ከ 19 ዓመታት በኋላ በ586 ሂ. ነው፡፡ ይህንን ተጨባጭ ታሪካዊ መረጃ እያየ “አይኔን ግንባር ያርገው” የሚል ካለ የለየለት ቂላቂል ነው፡፡ መውሊድ በሺዐዎች እንደተጀመረ የሚጠቁሙ ግልፅ ማስረጃዎች እየቀረቡ እያዩ “እከሌ እንዲህ ብለዋል” “እንቶኔ እንዲህ ብለዋል” እያሉ ነገር መዘብዘብ እራስን መሸወድ ብቻ ነው፡፡
“ሙዞፈር ነው የጀመረው” ያሉት እንደ ሲዩጢ ያሉ የኋለኛው ዘመን ሰዎች ከመሆናቸውም በላይ ያጣቀሱት ተጨባጭ ማስረጃ የለም፡፡ በነገራችን ላይ እነዚህ መውሊድ በሙዞፈር ነው የተጀመረው የሚሉ አካላት ኢብኑ ከሢርን ሲያጣቅሱ ማየት የተለመደ ነው፡፡ ኢብኑ ከሢር የሙዞፈርን መውሊድ ከመጥቀሳቸው ውጭ “ጀማሪ ነው” አላሉም፡፡
መቅሪዚ እንደጠቀሱት እነዚህ የሺዐዎቹ መውሊዶች ኋላ ላይ ለተወሰኑ ጊዜያት ተቋርጠው ነበር፡፡ [አልመዋዒዝ ወልኢዕቲባር፡ 1/432] ኋላ ላይ በተተካው የ“ፊጢሚዮቹ” ንጉስ አልኣሚር ቢአሕካሚላህ (524 ሂ.) ነው የተጀመሩት፡፡ ልብ በሉ! ይህ ዳግም የተጀመረው መውሊድ እራሱ ከሙዞፈር መውሊድ በዓል ብቻ ሳይሆን ከራሱ ሙዞፈር መወለድም የቀደመ ነው፡፡
በነገራችን ላይ ሱፍዮች መውሊድን ጀመረ የሚሉትን ሙዞፈርን ቅዱስ አድርገው የሚጠቅሱት ወይ ታማኞች ስላልሆኑ ነው፡፡ ወይ ደግሞ በሰውየው ላይ የቀረቡ ሂሶችን ያልተመለከቱ ናቸው፡፡ አብዛኞቹ የሚያደርጉት ለገበያቸው የሚሆናቸውን እየመረጡ ማቅረብ ነው፡፡ ንጉሱ በከፊል የታሪክ ፀሐፊዎች ከመወደሱም ጋር የሰላ ሂስ የሰነዘሩበትም አሉ፡፡ አንድ ምሳሌ ልጥቀስ፡-
ያቁት አልሐመዊ ይባላሉ፡፡ በ626 ሂ. የሞቱ ታዋቂ የታሪክ ምሁር ናቸው፡፡ ሙዞፈርን አስመልክተው እንዲህ ይላሉ፡-
“የዚህ ሰውየ ባህሪ እርስ በርሱ የሚቃረን ነው፡፡ እሱ ሲበዛ በዳይ፣ ህዝቦቹ ላይ ጨካኝ እንዲሁም አግባብ ባልሆነ መልኩ ገንዘቦችን የሚወስድ ነበር፡፡ ይህ ከመሆኑ ጋር ለድሃዎች የሚቸርና ለእንግዶች በብዛት የሚሰድቅ ነበር፡፡ እጅግ በርካታ ገንዘቦችን አፍስሶ ከከሃዲዎች እጅ ምርኮኞችን ነፃ ያወጣ ነበር፡፡ በዚህ ላይ ባለቅኔው እንዲህ ይላል፡-

‘ልክ እንደዚያች ወጥ ረገጥ
በብልቷ ነግዳ ለበጎ ስራ የምትሮጥ
መስሚያ ካለሽ ወዮ ላንቺ!
ምፅዋትሽ ይቅር ይልቅ አትዘሙቺ፡፡’ ” [ሙዕጀሙዑል ቡልዳን፡ 1/138]


«ልጄ ሆይ! ተውበትን አታዘግይ። ሞት በእርግጥም በቅፅበት ይመጣል።»
(ሉቅማን ለልጁ የመከረው ምክር)

[አ-ት'ተብሲራህ ሊብኒ-ል-ጀውዚይ: 34


“መውሊድ”፣ “ክሪስማስ”፣ አሹራ….?
***************************************
ከነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) እና ሰሃባዎቻቸው በላይ አውቀው ነው ወይ?
ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ነብይ ተደርገው በተላኩ ጊዜ ነሷራዎችም (ክርስትያኖች) ይሁዳዎችም ነበሩ፡፡ ነሷራዎች የኢሳንም ልደት ሲያከብሩ ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) የወንድማቸውን ኢሳ ልደት አንድም ቀን አክብረው አያውቁም፡፡ ምክንያቱም በአላህ አልታዘዙምና፡፡ የነብይም ይሁን የሌላ ግለሰብ የልደት በዓል ማክበር የነብያቶች እምነት እስልምና በፍፁም የሚያውቀው አይደለም፡፡ ልደት ማክበር የእስልምና አካልም አይደለም፡፡በሌላ በኩል ሌላኛው ወንድማቸው ነብየላህ ሙሳን (አለይሂ ሰላም) አስመልክቶ የሁዳዎች አሹራን ሲፆሙ አዩ፡፡ ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) የሁዳዎችን ለምን እንደሚፆሙ ጠየቁ “አላህ ሙሳን እና የእስራኢል ልጆችን ከፊርዐውን ነፃ ያወጣበት ቀን ነው” ሲሉ መለሱላቸው፡፡ ነብዩም (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) “እኛ በሙሳ ጉዳይ ከናንተ የበለጠ የተገባን ነን” ብለው አሹራን ፆሙ እንዲፆምም አዘዙ፡፡ እንዲያውም ረመዳን ከመደንገጉ በፊት አሹራ በሙስሊሞች ላይ ግዴታ ነበር፡፡ ከረመዳን በኋላ ይሀው እኛም የሳቸውን ፈለግ በመከተል እንፆመዋለን፡፡ ልክ እንደዚሁ ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) “ሰኞ ለምን እንደሚፆሙ” ሲጠየቁ “የተወለድኩበት ቀን ስለሆነ እና ቁርዐን እኔ ላይ የወረደበት ቀን ስለሆነ ነው” ብለዋል፡፡ ታድያ ግዴታ ያልሆነ የሱና ፆም አሹራን በአመት አንዴ እንድንፆመው፣ እሳቸው የተወለዱበትን ቀን እና ቁርዓን የወረደበትን ቀን ሰኞ እንዲሁ በሳምንትን አንዴ ሱና ፆም እንድንፆም ነግረውናል፡፡ የሚያሳዝነው አብዛኛው “መውሊድን” አከብራለሁ የሚል ሰው የታዘዘውን በየሳምንቱ የሚፆመውን ሱና ሲፆም አይታይም፡፡ ይልቁንስ ለምሳሌ “የኢስነይን ሰዎች ነን” እያሉ ሰኞ ሰኞ ጉንጫቸውን በአንደንዛዡ ቅጠል ጫት ወጥረው ሲቅሙ እና ሲጨፍሩ የሚውሉ ሸይጧን የተጫወተባቸው አሉ፡፡ በአመት አንዴ ግን ያልታዘዙትን “መውሊድ” ብለው በማክበር “የኢሳ ልደት” ብለው ከሚያከብሩት ሰዎች ጋር ተመሳስለዋል፡፡ የታዘዙትን ትተው ያልታዘዙትን በመስራት ወደ አላህ እዝነት ሳይሆን ቁጣውን ወደሚያከናንባቸው የሰይጣን መንገድ የሚንደረደሩ ሰዎች ምን አለ ቆም ብለው ቢያስቡ?
አላህ እኮ ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለምን) በመከተል እንጂ ውዴታውን እና ምህረቱን ቃል የገባልን ያላዘዙትን በመስራት አይደለም፡፡ ሸይጧን ደግሞ እንዲህ አሳቢ መስሎ ነው ከጥንት እስከዛሬ ሰዎችን ሲያጠም የነበረው፡፡ አላህ ከተንኮሉ ይጠብቀን፡፡
ሌላው ሰሃባዎች አላህ አማኝ፣ እውነተኞች፣ ወድጃቸዋለሁ እያለ ያወደሳቸው….. ከነሱ መንገድ ውጭ ያለን የሚከተል መንገድ የሳተ፣ ጀሀነምም እንደሚገባ አላህ እና መልክተኛው ነግረውን ሲያበቁ፡፡ ለምን ይሆን መውሊድንም ይሁን ሌሎች ተግባራትን በተመለከተ ሰሃባዎች የቆሙበት ቦታ የማንቆመው?
ሰሃባዎች ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) በህይወት በነበሩ ግዜም ይሁን ሞተው አንድም ቀን የማንንም ነብይ ይሁን የረሱልን (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ልደት አክብረው አያውቁም፡፡
ታድያ እኛ ማን ሆነን ነው ሰሃባዎች ያልሰሩትን የምንሰራው? የአላህን ዲን፣ ንፁሁን የነብዩ ሱና በቢድዐ ለማቆሸሽ፣ የሰይጣንን ተልኮ “ነብዩን መውደድ” በሚል ስም ለማሳካት ደፋ ቀና የሚባለው?
እውነት ሰሃባዎች ነብዩን (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ሳይወዱ ቀርተው ነው የነብዩን መውሊድ ያላከበሩት?
ወይንስ እነሱ ለነብያችን (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ያላቸው ውዴታ ሸሪዐ በደነገገው መልኩ በገንዘብ፣ በህይወት መስዋትነት እና በሌላም ስለገለፁ ነው?
እውነታው እነሱ ስለስርዐት አላቸው፡፡ ይህንን ከሰማይ የወረደ ዲን “እኔ እንደሚመስለኝ” እያሉ ሳይዳፈሩ ያንን ንፁህ ምንም ጭማሪ የማይፈልግ ዲን ለእኛ በሰላም አድርሰዋል፡፡ አላህም ወዷቸዋል፡፡ ዛሬ አላህ ዘንድ ገና ፍርድ ያልተሰጠባቸው ሰዎች ይህን ዲን መጥተው በፈለጉ ጊዜ በቀያየሩት ቁጥር እኛ አብረን የምንቀያየረው አላህን ነው የምናመልከው ወይንስ እነዚህ አላህ ያልደነገገውን የሚደነግጉ ዲን አፍራሾች?
መውሊድ የሸሮች ሁሉ መጠራቀሚያ፣ የሙስሊሞችን አንድነት ማፍረሻ፣ የድሆችብ ንብረት መብያ….. እርኩስ ተግባር ነው፡፡ ሙስሊሞች ሆይ! ራቁት፡፡
አይ ሸይጧን በየዘመኑ መጥፎውን ነገር ጥሩ አስመስሎ ስም እየቀያየረ የአደም ልጆችን ያጠማቸዋል፡፡ ወደ እሳትም ይመራቸዋል፡፡ ተመልከቱ አደም እና ሀዋን ያቺን ዛፍ ስሟን አሳምሮ እንዳትበሉ የተባሉትን አስበላቸው ከዛም ስህተት ውስጥ ጣላቸው፡፡ የኑሕን (አለይሂ ሰላም) ህዝቦች በሞቱት 5 ደጋግ ሰዎች ያዘነ መስሎ መቀማመጫቸው ላይ ሀውልት አሰርቶ ገደል ከተታቸው፡፡ የጠፉበትን እርኩስ ተግባር ሽርክ ውስጥ ዘፈቃቸው፡፡ አሁንም ይህን ኡመት “ለነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ያላችሁን ውዴት ልደቱን አክብሩለት” የሚመስል የሰይጣን ሹክታ እዚህ ኡማ ላይ ተሰራጭቶ የሽርክ መነሃርያ የሆነውን መውሊድ እያከበሩ ወደ እሳት ሲነዱ ይታያሉ፡፡ መውሊድ ላይ ከባባድ የሽርክ ቃላትን ከእስልምና አስፈንጥረው የሚያስወጡ የሽርክ ተግባራት ይታያሉ፡፡ ከነዚህም ውስጥ አላህን ትቶ ፍጡራንን መለመን፣ እነሱን ድረሱልን ብሎ መጣራት፣ አላህን ትቶ ለፍጡራን ስለት መግባት እና የመሳሰሉት ናቸው፡፡
አሳዛኙ ደግሞ ጥመቱን እንደሃቅ፣ ሃቁን እንደ ጥመት ቆጥረው “ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም)፣ ሰሀባዎቻቸው፣ ታቢኢኖች፣ አትባኡታቢኢን፣ 4 አኢማዎች፣ ሙሐዲሶች፣ 3 ምርጥ ክፍለ ዘመን እና ትውልድ አላከበረውም” ሲባሉ ሃቁን ከመቀበል ይልቅ ያልታዘዝነውን አንሰራም ያሉትን “ነብዩን የማይወዱ፣ የነብዩ ጠላቶች፣ ወሃብዬች እና ሌላም” ሲሉ ይደመጣሉ፡፡
ከድጡ ወደ ማጡ ይሉሃል ይህ ነው፡፡ ሸይጧን ግን ዛሬ ጥፋታቸውን እያሸበረቀላቸው ዲንን በዲን ስም እንዲንዱ እየገፋፋቸው ነው፡፡
ነሷራችን በነብየላህ ኢሳ (አለይሂ ወሰለም) ላይ ድንበር አልፈው “የአላህ ልጅ ነው” እንዲሉ ያደረጋቸው የሰው እና የጂን ሰይጣናት ናቸው፡፡ ነሷራች ኢሳን ድንበር ያለፉበት ጠልተውት ሳይሆን ወደውት ነው፡፡ ግን ድንበር አለፉ፡፡ ከልክ በላይ ከፍ ከፍ አደረጉት፣ ያላታዘዙትን ልደቱን አከበሩለት፡፡ ከዚህም ኡማ ነብዩን (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) በመውደድ ስም ሸይጧን መንገድ አስቷቸው ልክ እንደነሷራች ያልታዘዙትን ልደት ማክበር፣ ነብዩን (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) “መጣ ያለፈው ወንጀላችንን ማረ”፣ “የሁሉ ቀላቢ”፣ “ልቤ ባንቱ በእርሶ ተመካ” እና የመሳሰሉትን የብቸኛ ፈጣሪና ተመላኪ አላህ መብት አሳልፈው ለነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) በመስጠት ታላቁን ማጋራት እና ቢድዐ ሲሰሩ ይታያል፡፡
ሸይጧን መቼም ለሰው ልጎች ከባድ ጠላታቸው ነው፡፡ አላህ ድንበር ከማለፍ፣ ከሽርክ፣ ከቢድዐ እና አላህ ከጠላው ሁሉ ይጠብቀን፡፡ አላህ ወደ ተውሒድ፣ ሱና፣ የሰለፉነ ሷሊሂን አረዳድ፣ እሱ መልካም ወዳለው ሁሉ ይምራን፡፡
የአላህ ሰላት እና ሰላም በነብያት መደምደሚያ፣ በቤተሰቦቻቸው፣ በባልደረባዎቻቸው እና ሃቅ በተከተለ ላይ ሁሉ ይሁን፡፡




ነብዩን አትወዳቸውም?


ማን ነው የከፋው?
አንዳንድ ሰዎች መውሊድ በኢስላም የሌለ የፈጠራ መንገድ ነው፡፡ መውሊድ ሸር ነው፡፡ ኸይር ቢሆን ኖሮ አላህ እና መልክተኛው ይደነግጉልን ነበር፡፡ ሰሃባዎች፣ ታቢእዬች፣ አትባኡ ታቢኢን፣ አራቱ አኢማዎች ፉቀሃዎች (አቡ ሀኒፋ፣ ኢማሙ ማሊክ፣ ኢማሙ ሻፊኢይ፣ ኢማሙ አሕመድ)፣ ሙሐዲሶች (ቡኻሪ፣ ሙስሊም፣ ነሳኢ፣ አቡ ዳውድ ኢብን ማጃእ…..) ያውቁት ነበር፡፡ እነዚህ ሁሉ ምርጦች አያውቁትም ሲባሉ እሺ አናከብርም ፈጠራ ስለሆነ ከማለት ፋንታ “በሳቸው መወለድ ሰይጣን እና ወሃቢ ብቻ ነው ያለቀሱት” ሲሉ እየተደመጡ፣ ሲፅፉም እየታዩ ነው፡፡
እውነታው በነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) መወለድ የመካ ሙሽሪኮች አልተቆጡም ነበር፡፡ የመካ አጋሪያን ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለምን) ከነብይነት በፊት “ሙሐመዱል አሚን (ታማኙ ሙሐመድ)” እያሉ ነበር የሚጠሯቸው፡፡ ነብይ ሆነው “ህዝቦቼ ሆይ! ከአላህ በስተቀር በሐቅ የሚመለክ የለም በሉ ትድናላችሁ” ሲሉ የመጀመሪያው ጠላታቸው በሳቸው መወለድ አይደለም ሊቆጣ ተደስቶ የነበረው አቡ ለሃብ “እልም ያድርግህ ለዚህ ነው ወይ የሰበሰብከን” ሲል ግልፅ ጥላቻውን ይፋ አደረገ፡፡ ከዛም አጋሪያን ታማኙ ሙሐመድ እንዳላሉ “ድግምተኛ፣ እብድ፣ አባትና ልጅን የሚለያይ፣ ገጣሚ….” እያሉ ይሰድቧቸውና ስማቸውን ያጠፉ ጀመር፡፡ አለ የሚባል ሁሉ ፈተና ደረሰባቸው፡፡
ጥያቄ አለኝ ሰሃባዎች መውሊድን አላከበሩም ነበር ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለምን) ስለሚጠሉ ወይንም በሳቸው መወለድ ስለተናደዱና ስለበሸቁ ነበርን?
በፍፁም፡፡ ሰሃባዎች ማለት በጣም ስነስርኣት ያላቸው ትውልድ ነበሩ፡፡ አደለም መልክተኛው በህይወት እያሉ መልክተኛው (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ከሞቱም በኋላ የሳቸውን ትእዛዝ ታዘው ለሁለት አገር ድል በቅተዋል፡፡ ዛሬ ይህ ኡመት አላህ ካዘነለት ውጭ ሱና እንከተል እየተባለ ወደ ቢድኣ ይሮጣል፡፡ ይህም ኡማዋ ላለበት ውርደት ሰበብ ሆኗል፡፡ አላህ የሳቸውን ሱና አጥብቀው፣ የሱናን ባንዲራ ከፍ አድርጎው ለድል ከሚጎናፀፉት ያድርገን፡፡
ዛሬ ዛሬ ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) እንደገለፁት “የማይሰሩትን የሚናገሩ፣ ያልታዘዙትን የሚሰሩ” ሰዎች ማየት የተለመደ ሆኗል፡፡ እንዲህ አይነት ሰዎችን ከቻልን በእጃችን እንድናስቆም፣ ካልቻልን በምላሳችን እንናገር፣ ካልቻልን በቀልባችን እንድንጠላ ነግረውናል፡፡
አላህ ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) መወለዳቸውን ሳይሆን መላካቸውን ነው ፀጋ፣ ልገሳ ብሎ የጠራው፡፡ አላህ እንዲህ ይላል
لَقَدْ مَنَّ ٱللَّهُ عَلَى ٱلْمُؤْمِنِينَ إِذْ بَعَثَ فِيهِمْ رَسُولًا مِّنْ أَنفُسِهِمْ يَتْلُوا۟ عَلَيْهِمْ ءَايَٰتِهِۦ وَيُزَكِّيهِمْ وَيُعَلِّمُهُمُ ٱلْكِتَٰبَ وَٱلْحِكْمَةَ وَإِن كَانُوا۟ مِن قَبْلُ لَفِى ضَلَٰلٍ مُّبِينٍ
አላህ በምእምናን ላይ ከጎሳቸው የኾነን፤ በእነርሱ ላይ አንቀጾቹን የሚያነብ፣ የሚጠራቸውም፣ መጽሐፍንና ጥበብን የሚያስተምራቸውም የኾነን መልእክተኛ በውስጣቸው በላከ ጊዜ፤ በእርግጥ ለገሰላቸው፡፡ እነርሱም ከዚያ በፊት በግልጽ ስህተት ውስጥ ነበሩ፡፡
እኛ እዚህ ዲን ላይ ያለን ድርሻ መከተል ብቻ ነው፡፡ መጨመር እና መቀነስ ለእሳት ይዳርጋል፡፡ አላህ ኢድ እና አረፋን እንድናከብር እንደ ደነገገልን መውሊድን እንድናከብር ቢያዘን እንሰራ ነበር፡፡ ነገር ግን የሃይማኖቱ ባለቤት አላህ አላዘዘንም እኛም ስነስርኣት ይዘን ሰይጣን የሚያመጣልንን ወጥመድ አንቀበልም ብለን ይሀው በሱና ላይ ሰሃባዎች በነበሩበት መንገድ ላይ ፀንተናል፡፡ አልሐምዱሊላህ፡፡
ሰይጣን በነብዩ ውዴታ ስም አላህ ያላዘዘውን እንዳያሰራን ወጥመዶቹን ጠንቅቀን እንወቅ፡፡ ነሷራች ኢሳን (አለይሂ ሰላም) ያመለኩት ወደውት እንጂ ጠልተውት አይደለም፡፡ ስለዚህ የአላህ ባሪያ የሆኑትን ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ስንወድ አላህና መልክተኛው ያዘዙንን ብቻ በመታዘዝ ከከለከሉን በመራቅ ብቻና ብቻ ነው፡፡ አላህ እና መልክተኛው ያላዘዙንን ሰርተን “ለነብዩ ያለኝን ውዴታ ለመግለፅ ነው” ብንል ምክንያት አይሆነንም፡፡
አይደለም መልክተኛውን አላህን መውደዳችን እንኳን የሚረጋገጠው ነብዩ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለምን) በመከተል ነው፡፡ መከተል ሲባል የሰሩትን በመስራት የከለከሉትንና ያልሰሩትን ከመስራት በመራቅ፡፡
የአላህ ሰላትና ሰላም በመልክተኛ፣ በቤተሰቦቻቸው፣ በባልደረባዎቻቸውና ሐቅን በተከተለ ላይ ሁሉ ይሁን፡፡ አሚን፡፡


✅ የሲድቅ ( የእውነተኝነት ) ደረጃው

ሲድቅ ከላኢላሃ ኢለ ላህ ሸርጦች አንዱ ሲሆን ታላቅ የቀልብ ዒባዳ ነው ። የቀልብ ዒባዳዎች ባጠቃላይ ከሱ ነው የሚመነጩት ። የመልካም ስራ ሩሕ ነው ማለት ይቻላል ። የኢማን ባለቤቶች ከሙናፊቆች የጀነት ሰዎች ከጀሀነም ሰዎች የሚለዩት በሱ ነው ። ሲድቅ የዲን መሰረት ነው ። የእውነተኛ ሰው ደረጃ ከነብያቶች ደረጃ ቀጥሎ ነው የሚመጣው ። ይኀውም በሚቀጥለው የአላህ ቃል ማየት እንችላለን : –
" وَمَن يُطِعِ اللَّهَ وَالرَّسُولَ فَأُولَٰئِكَ مَعَ الَّذِينَ أَنْعَمَ اللَّهُ عَلَيْهِم مِّنَ النَّبِيِّينَ وَالصِّدِّيقِينَ وَالشُّهَدَاءِ وَالصَّالِحِينَ ۚ وَحَسُنَ أُولَٰئِكَ رَفِيقًا "
النساء ( 69 )
" አላህንና መልክተኛውንም የሚታዘዝ ሰው እነዚያ ከእነዚያ አላህ በእነርሱ ላይ ከለገሳቸው ከነቢያት፣ ከጻድቃንም ፣ ከሰማዕታትም፣ ከመልካሞቹ ጋር ይኾናሉ ፡፡ የእነዚያም ጓደኝነት አማረ ፡፡ "
ለዚህም ነው አላህ አማኞችን ከእውነተኞች ሁኑ ብሎ ያዘዘው ። ይህንንም በሚቀጥለው የአላህ ቃል እናገኘዋለን : –
" يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا اتَّقُوا اللَّهَ وَكُونُوا مَعَ الصَّادِقِين َ"
التوبة ( 119 )
" እናንተ ያመናችሁ ሆይ! አላህን ፍሩ ፤ ከእውነተኞቹም ጋር ኹኑ ፡፡ "
አላህ የመልካም ስራ ባልተቤቶችን ሲነግረን መልካም ስራቸውን ዘርዝሮ ካወደሳቸው በኋላ እውነተኞች መሆናቸውን መስክሮ አላህን የሚፈሩት እነርሱ ናቸው ብሎ ነው የዘጋው ። የሚቀጥለውን አንቀፅ እንመልከት : –
" لَّيْسَ الْبِرَّ أَن تُوَلُّوا وُجُوهَكُمْ قِبَلَ الْمَشْرِقِ وَالْمَغْرِبِ وَلَٰكِنَّ الْبِرَّ مَنْ آمَنَ بِاللَّهِ وَالْيَوْمِ الْآخِرِ وَالْمَلَائِكَةِ وَالْكِتَابِ وَالنَّبِيِّينَ وَآتَى الْمَالَ عَلَىٰ حُبِّهِ ذَوِي الْقُرْبَىٰ وَالْيَتَامَىٰ وَالْمَسَاكِينَ وَابْنَ السَّبِيلِ وَالسَّائِلِينَ وَفِي الرِّقَابِ وَأَقَامَ الصَّلَاةَ وَآتَى الزَّكَاةَ وَالْمُوفُونَ بِعَهْدِهِمْ إِذَا عَاهَدُوا ۖ وَالصَّابِرِينَ فِي الْبَأْسَاءِ وَالضَّرَّاءِ وَحِينَ الْبَأْسِ ۗ أُولَٰئِكَ الَّذِينَ صَدَقُوا ۖ وَأُولَٰئِكَ هُمُ الْمُتَّقُون َ"
البقرة ( 177 )
" መልካም ሥራ ፊቶቻችሁን ወደ ምሥራቅና ምዕራብ አቅጣጫ ማዞር አይደለም ፡፡ ግን መልካም ሥራ በአላህና በመጨረሻው ቀን ፣ በመላእክትም ፣ በመጻሕፍትም ፣ በነቢያትም፣ ያመነ ሰው ገንዘብንም ከመውደዱ ጋር ለዝምድና ባለቤቶችና ለየቲሞች ለምስኪኖችም ፣ ለመንገደኞችም ፣ ለለማኞችም ፣ ለጫንቃዎችም (ማስለቀቅ) የሰጠ ሰውና ሶላትንም ደንቡን ጠብቆ የሰገደ ፣ ዘካንም የሰጠ ፣ ቃል ኪዳንም በገቡ ጊዜ በኪዳናቸው የሞሉ (ሰዎች ሥራ) ነው ፡፡ በችግር በበሽታና በጦር ጊዜም ታጋሾችን (እናወድሳለን) ፡፡ እነዚህ እነዚያ እውነትን የያዙ ናቸው ፡፡ እነዚያም ተጠንቃቂዎቹ እነርሱ ናቸው ፡፡ "
ሸኹል ኢስላም – ረሒመሁላሁ – እንዲህ ይላል : –
" والصدق والإخلاص هما في الحقيقة تحقيق الإسلام والإيمان ، فإن المظهرين للإسلام ينقسمون إلى مؤمن ومنافق ، والفارق بين المؤمن والمنافق هو الصدق . فإن أساس النفاق يبنى عليه هو الكذب ، ولهذا إذا ذكر الله حقيفة الإيمان نعته بالصدق كما في قوله تعالى : –
" ሲድቅና ኢኽላስ የኢማንና የእስልምና ማረጋገጫ ናቸው ። እስልምናን የሚያሳዩ ሰዎች ወደ ሙእሚንና ሙናፊቅ ይከፈላሉ, በሙእሚንና በሙናፊቅ መካከል የሚለየው ሲድቅ ነው ። የንፍቅና መሰረቱና መገንቢያው ውሸት ነው ። ለዚህ ነው አላህ አውነተኛን ኢማን ሲገልፅ በሲድቅ የሚገልፀው በሚቀጥለው የአላህ ቃል እንደመጣው : –
" قَالَتِ الْأَعْرَابُ آمَنَّا ۖ قُل لَّمْ تُؤْمِنُوا وَلَٰكِن قُولُوا أَسْلَمْنَا وَلَمَّا يَدْخُلِ الْإِيمَانُ فِي قُلُوبِكُمْ ۖ وَإِن تُطِيعُوا اللَّهَ وَرَسُولَهُ لَا يَلِتْكُم مِّنْ أَعْمَالِكُمْ شَيْئًا ۚ إِنَّ اللَّهَ غَفُورٌ رَّحِيم ٌ"
الحجرات ( 14 )
የዐረብ ዘላኖች «አምነናል» አሉ ፡፡ «አላመናችሁም ፤ ግን ሰልመናል በሉ ፡፡ «እምነቱም በልቦቻችሁ ውስጥ ገና (ጠልቆ) አልገባም ፡፡ አላህንና መልክተኛውንም ብትታዘዙ ከሥራዎቻችሁ ምንንም አያጎድልባችሁም ፡፡ አላህ መሓሪ አዛኝ ነውና» በላቸው ፡፡
" إِنَّمَا الْمُؤْمِنُونَ الَّذِينَ آمَنُوا بِاللَّهِ وَرَسُولِهِ ثُمَّ لَمْ يَرْتَابُوا وَجَاهَدُوا بِأَمْوَالِهِمْ وَأَنفُسِهِمْ فِي سَبِيلِ اللَّهِ ۚ أُولَٰئِكَ هُمُ الصَّادِقُونَ "
الحجرات ( 15 )
(እውነተኛዎቹ) ምእምናን እነዚያ በአላህና በመልእከተኛው ያመኑት ከዚያም ያልተጠራጠሩት በገንዘቦቻቸውና በነፍሶ ቻቸውም በአላህ መንገድ የታገሉት ብቻ ናቸው ፡፡ እነዚያ እነሱ እውነተኞቹ ናቸው ፡፡
" لِلْفُقَرَاءِ الْمُهَاجِرِينَ الَّذِينَ أُخْرِجُوا مِن دِيَارِهِمْ وَأَمْوَالِهِمْ يَبْتَغُونَ فَضْلًا مِّنَ اللَّهِ وَرِضْوَانًا وَيَنصُرُونَ اللَّهَ وَرَسُولَهُ ۚ أُولَٰئِكَ هُمُ الصَّادِقُون َ"
الحشر ( 8 )
" ለእነዚያ የአላህን ችሮታና ውዴታውን የሚፈልጉ ፣ አላህንና መልክተኛውንም የሚረዱ ኾነው ከአገሮቻቸውና ከገንዘቦቻቸው ለተወጡት ስደተኞች ድኾች (ይስሰጣል) ፡፡ እነዚያ እነርሱ እውነተኞቹ ናቸው ፡፡"
فأخبر أن الصادقين في دعوى الإيمان هم المؤمنون الذين لم يتعقب إيمانهم ريبة وجاهدوا في سبيله بأموالهم وأنفسهم ."
التحفة العراقية ، ص ( 20 – 21 )
" አላህ በኢማናቸው እውነተኛ የሆኑት እነዚያ ኢማናቸው ጥርጣሬ ያልተከተለው በገንዘባቸውና በነፍሳቸው በአላህ መንገድ ላይ የታገሉት መሆናቸውን ተናገረ ። "
በመቀጠልም አንድ ባሪያ የቂያማ ቀን ከእሳት ቅጣት የሚጠብቀው ሲድ ብቻ መሆኑን አላህ ሲነግረን እንዲህ ይላል : –
" قَالَ اللَّهُ هَٰذَا يَوْمُ يَنفَعُ الصَّادِقِينَ صِدْقُهُمْ ۚ لَهُمْ جَنَّاتٌ تَجْرِي مِن تَحْتِهَا الْأَنْهَارُ خَالِدِينَ فِيهَا أَبَدًا ۚ رَّضِيَ اللَّهُ عَنْهُمْ وَرَضُوا عَنْهُ ۚ ذَٰلِكَ الْفَوْزُ الْعَظِيمُ "
المائدة ( 119 )






ኮርስ፡- በአላህና በመጨረሻው ቀን ላመኑ ሁላ፡፡

አርእስት፡- ትውልዱን ከመንዙማ ማስጠንቀቅ፡፡

ሼር በማድረግ ማህበረሰቡ ትምህርቱን እንዲሳተፍ ሰበብ ሁኑ፡፡
ለወጣቶች በክረምት 100 ሀዲስ ተማምረን መጨረሳችን ይታወቃል፡፡ በአላህ ፍቃድ መንዙማ ውስጥ ያሉትን ሺርኮች ትውልዱ ይረዳቸው ዘንድ ዛሬ ማታ ከመግሪብ እስከ ኢሻ ስንኞቹን እያነሳን ከቁርዓን እና ሀዲስ መልስ ይሰጥባቸዋል፡፡ የቴሌግራም ላይቭ ሊንክም ይለቀቃል፡፡ ልጆቾን ተሳታፊ ያድርጉ፣ እርሶም ይከታተሉ፡፡ እስልምናችንን ለማፍረስ ከውስጥ ቆርጠው የተነሱ አካላት በሰለዋት ስም ምን አይነት ከኢስላም የሚያስወጣ ንግግሮች እንዳሏቸው በማስረጃ በአላህ ፍቃድ እንማማራለን፡፡
ፓምፍሌቱን ከዚህ ሊንክ ያውርዱና ፕሪንት አድርገው ይከታተሉ፡- https://t.me/SadatKemalAbuMeryem/3512
በሞባይላችሁ ለመከታተል የምትፈልጉ ከዚህ ሊንክ አውርዱት፡- https://t.me/SadatKemalAbuMeryem/3511
በአላህ ፍቃድ ተውሒድ ከፍ ብላ ትውለበለባለች፡፡ ሺርክ ከነባለቤቶቻቸው ይከስማሉ፡፡


💢አየተል ኩርስይ ከፈርድ ሶላት በኋላ
➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖

【عن أبي أُمامةَ الباهليِّ رضيَ اللهُ عنه قال رسول الله صلى الله عليه وسلم من قرأ آية الكرسي في دبر كل صلاة مكتوبة لم يمنعه من دخول الجنة إلا أن يموت】
(رواه النسائي وصححه الألباني)

✅ አቢ ኡማመተ አልባሂልይ እንዳስተላለፈው የአላህ መልእክተኛ እንዲህ ብለዋል።
【ግድ ከተደረገበት ፈርድ ሶላት በኋላ አየተል ኩርስይ የሚቀራ ሰው፧ጀነት ለመግባት የሚከለክለው ነገር የለም ሞት ቢሆን እንጂ】
📚ነሳእይ ዘግቦታል ኢማሙ አልባንይ ሶሂህ ብለውታል።

🔺የሀዲሱ መልእክት ባጭሩ🔺
〰〰〰〰〰〰〰〰〰
👉ከፈርድ ሶላት በኋላ አየተልኩርስይ በሚቀራ ሰውና በጀነት መካከል ያለው ግርዶሽ ሞት ብቻ ነው ማለት ነው። ነገር ግን ይህ ትልቅ ምንዳ የሚረጋገጠው ተውሂድ ከተረጋገጠ በኋላ ነው። በአላህ ላይ የሚያጋራ ሰው የፈለገ መልካም ስራ ቢሰራ ተቀባይነት አያገኝምና።

🔘አየተል ኩርስይ ከአጭር ትርጉም ጋር
〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰
🔸ٱللَّهُ لَآ إِلَٰهَ إِلَّا هُوَ ٱلْحَىُّ ٱلْقَيُّومُ
🔹አላህ ከእርሱ በስተቀር በእውነት የሚመለክ አምላክ የለም፡፡ ሕያው ራሱን ቻይ ነው፡፡
🔸 لَا تَأْخُذُهُۥ سِنَةٌ وَلَا نَوْمٌ
🔹ማንገላጀትም እንቅልፍም አትይዘውም፡፡
🔸 لَّهُۥ مَا فِى ٱلسَّمَٰوَٰتِ وَمَا فِى ٱلْأَرْضِ
🔹በሰማያት ውስጥና በምድር ውስጥ ያለው ሁሉ የርሱ የአላህ ብቻ ነው፡፡
🔸 مَن ذَا ٱلَّذِى يَشْفَعُ عِندَهُۥٓ إِلَّا بِإِذْنِهِۦ
🔹ያ እርሱ ዘንድ በፈቃዱ ቢኾን እንጅ የሚያማልድ ማነው?
🔸 يَعْلَمُ مَا بَيْنَ أَيْدِيهِمْ وَمَا خَلْفَهُمْ
🔹አላህ (ከፍጡሮች) በፊታቸው ያለውንና ከኋላቸው ያለውን ሁሉ ያውቃል፡፡
🔸 وَلَا يُحِيطُونَ بِشَىْءٍ مِّنْ عِلْمِهِۦٓ إِلَّا بِمَا شَآءَ
🔹በሻውም ነገር ቢሆን እንጂ ከዕውቀቱ በምንም ነገር አያካብቡም (አያውቁም)፡፡
🔸 وَسِعَ كُرْسِيُّهُ ٱلسَّمَٰوَٰتِ وَٱلْأَرْضَ
🔹ኩርስዩን ሰማያትንና ምድርን ሰፋ፡፡
🔸 وَلَا يَـُٔودُهُۥ حِفْظُهُمَا
🔹ጥበቃቸውንም አያቅተውም፡፡
🔸 وَهُوَ ٱلْعَلِىُّ ٱلْعَظِيمُ
🔹እርሱም የሁሉ በላይ ታላቅ ነው፡፡


የምሽት ግብዣ‼
============
✍ የዚህ ወጣት ብቃት በጣም ነው ያስገረመኝ። ማሻ አላህ! አይመን ጦይብ ይባላል። ከነገ በኋላ እሁድ ከሚመረቁት የመርከዝ ኢብኑ ዐባስ ተማሪዎች መካከል አንዱ ነው።ይህን ጉሮሮ የሰጠው ጌታ አላህ ምስጋና የተገባው ነው።

①, ቃሪእ መውላና ኩርተሽ፣
②, በአስቀሪው ድምፅ፣
③, ቃሪእ አቡበክር አ-ሽ'ሻጢሪ፣
④, ቃሪእ ዐብዱ-ር'ረሕማን መስዑድ
⑤, ቃሪእ ዑመረ-ል-ሒሻሚይ (አዲስ ቃሪእ)
⑥, ቃሪእ ሰልማነ-ል-ዐቲቢይ
⑦, ቃሪእ ያሲር አል-ዱሰሪይ
⑧, ቃሪእ ሰዕደ-ል-ጛሚዲይ
⑨, ቃሪእ ኻሊደ-ል-ጀሊል
10, ቃሪእ ዐብዱ-ል-ባሲጥ ዐብዱ-ስ'ሶመድ

ገና ያላስደመጠን እስከ 5 ድምፆች አሉት!


አላህ ይባርክልህ። አምሳያህንም ያብዛልን። ጠቃሚ እውቀትም ይጨምርልህ!

(ከመርከዙ ገፅ የተገኘ!)

20 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.

863

obunachilar
Kanal statistikasi