ሸይኹል ኢስላም ኢብኑ ተይሚያ [ረሂመሁሏህ] እንደሚሉት ሙእሚን በርሱና በአሏህ መካከል የሚቀር ወንጀል፣ ሃጢያት ከፈጸመ በአስር ምክንያቶች ከቅጣት ሊድን እንደሚችል ይናገራሉ። ከአስሮቹ ምክንያቶች አንዱ ሰውየው በህይወት እያለም ሆነ ከሞተ በኋላ ኢስቲግፋር የሚያደርጉለት፣ ምህረት የሚጠይቅሉት፣ የመልካም ስራቸውን ምንዳ በስጦታ የሚያበረክቱለት ወንድሞች ያሉት እንደሆነ ወንጀለኛ ቢሆን እንኳ አሏህ ይቅር ብሎት፣ ከጀሃነም ነጃ ይለዋል። ሷሊሆችን፣ ደጋጎችን መጎዳኘት፤ እነርሱን መወዳጀት ብዙ ጥቅሞች አሉት። ዱንያ ላይ ወደ መልካም ይጎትቱናል፣ ከመጥፎ ይከለክሉናል። ቀድመናቸው ብንሻገር ጨርሶ አይረሱንም፣ ምህረት ይጠይቁልናል፣ በዱዓቸው ያስታውሱናል። ይሄ መታደል ነው። ተስካር ወይም ሰደቃ በልቶ የሚበተን ወዳጅ አይጠቅመንም፤ ስለዚህ ደጋጎችን ለራሳችን ስንል እንጎዳኝ፣ ሷሊሆችን እንወዳጅ።
•┈┈•◈◉✹❒🔸❒✹◉◈•┈┈•
©ሱቡሉ ሰላም-سبل السلام
https://t.me/AbubilalIbnuseid
•┈┈•◈◉✹❒🔸❒✹◉◈•┈┈•
©ሱቡሉ ሰላም-سبل السلام
https://t.me/AbubilalIbnuseid