የግለሰቦችን የቴሌግራም አድራሻ በተለያዬ ዘዴ በመጥለፍ በስማቸው ሲያጭበረብር የነበረው ግለሰብ በቁጥጥር ስር ውሏል።
በኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደር በተደጋጋሚ ከተለያዩ ግለሰቦች ገንዘብ የሚያጭበረብሩ ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር እያዋለ ለህግ እያቀረበ የሚገኘው የከተማው ፖሊስ ከሰሞኑ የግለሰቦችን የቴሌግራም አካውንትን በመጥለፍ የተቸገረ በማስመሰል ገንዘብ ጠይቆ በማስላክ ለግል ጥቅሙ ሊያውል የነበረው ተጠርጣሪ ሰፎኒያስ አደም ጥላሁ የተባለ ወጣትን በከተማ አስተዳደሩ የቢራሮ ክፍለ ከተማ ፖሊስ በቁጥጥር ስር አውሏል።
የቢራሮ ክፍለ ከተማ ፖሊስ አዛዥ ምክትል ኢንስፔክተር መሀመድ ይማም እንዳሉት ከሰሞኑ አንድ የግል ተበዳይ የቅርብ ቤተሰቡ የሆነች ልጅ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ እንዳለችና ገንዘብ እንደሚያስፈልጋት በቴሌግራም አድራሻዋ 340 ሽህ ጠየቀችው ያለውን180 ሺህ ብር ከላከ በኋላ ሲያጣራ አድራሻዋ መጠለፍ ተረጋገጠ ብለዋል። በዚህ መነሻነት ፖሊስ ተከታትሎ ተጠርጣሪውን በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ እያጣራ መሆኑን ገልፀው አሁን አሁን በቴክኖሎጂ የተደገፈ የማጭበርበር ስራዎች እየጨመሩ መሆናቸውን አንስተዋል።
ወንጀል ፈፃሚዎችን በቁጥጥር ስር በማዋል ሂደት ማህበረሰቡ ላደረገላቸው ጥቆማ ያመሰገኑት ም/ኢንስፔክር መሀመድ ይማም ወደ ፊትም ከፖሊስ ጎን እንዲቆም ጥሪ አቅርበዋል።
በኮምቦልቻ ከተማ አስተዳደር በተደጋጋሚ ከተለያዩ ግለሰቦች ገንዘብ የሚያጭበረብሩ ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር እያዋለ ለህግ እያቀረበ የሚገኘው የከተማው ፖሊስ ከሰሞኑ የግለሰቦችን የቴሌግራም አካውንትን በመጥለፍ የተቸገረ በማስመሰል ገንዘብ ጠይቆ በማስላክ ለግል ጥቅሙ ሊያውል የነበረው ተጠርጣሪ ሰፎኒያስ አደም ጥላሁ የተባለ ወጣትን በከተማ አስተዳደሩ የቢራሮ ክፍለ ከተማ ፖሊስ በቁጥጥር ስር አውሏል።
የቢራሮ ክፍለ ከተማ ፖሊስ አዛዥ ምክትል ኢንስፔክተር መሀመድ ይማም እንዳሉት ከሰሞኑ አንድ የግል ተበዳይ የቅርብ ቤተሰቡ የሆነች ልጅ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ እንዳለችና ገንዘብ እንደሚያስፈልጋት በቴሌግራም አድራሻዋ 340 ሽህ ጠየቀችው ያለውን180 ሺህ ብር ከላከ በኋላ ሲያጣራ አድራሻዋ መጠለፍ ተረጋገጠ ብለዋል። በዚህ መነሻነት ፖሊስ ተከታትሎ ተጠርጣሪውን በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ እያጣራ መሆኑን ገልፀው አሁን አሁን በቴክኖሎጂ የተደገፈ የማጭበርበር ስራዎች እየጨመሩ መሆናቸውን አንስተዋል።
ወንጀል ፈፃሚዎችን በቁጥጥር ስር በማዋል ሂደት ማህበረሰቡ ላደረገላቸው ጥቆማ ያመሰገኑት ም/ኢንስፔክር መሀመድ ይማም ወደ ፊትም ከፖሊስ ጎን እንዲቆም ጥሪ አቅርበዋል።