የሰላም ጥሪን የተቀበሉ የታጠቁ አካላት ወደ ሕዝብ እና መንግሥት ተመለሱ።
አማራ ፖሊስ: ጥር 24/2017 ዓ.ም
በደቡብ ወሎ ዞን ተሁለደሬ ወረዳ በሕዝብ እና በመንግሥት በተደጋጋሚ ይቀርብ የነበረውን የሰላም ጥሪ የተቀበሉ የታጠቁ አካላት በሰላም መግባታቸውን የወረዳው አሥተዳደር አስታውቋል።
በደቡብ ወሎ ዞን በተሁለደሬ ወረዳ 027 ሙጢበልግ እየተባለ በሚጠራው ቀበሌ በተሳሳተ መንገድ ነፍጥ አንግበው የነበሩ አካላት ናቸው የሰላምን መንገድ መርጠው ወደ ሕዝብ እና መንግሥት የተመለሱት።
የታጠቁት አካላት ወደ አካባቢያቸው ሲደርሱ በተሁለደሬ ወረዳ የሥራ ኀላፊዎች አቀባበል ተደርጎላቸዋል።
የተሁለደሬ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኀላፊ ደመቁ አበበ፣ የመከላከያ ሠራዊት መሪዎች፣ ሌሎች የወረዳው የሥራ ኀላፊዎች፣ የጸጥታ መዋቅር መሪዎች፣ የአካባቢው የሃይማኖት አባቶች እና የሀገር ሽማግሌዎች በተገኙበት አቀባበል ስለመደረጉ ከደቡብ ወሎ ዞን የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
#አሚኮ
አማራ ፖሊስ: ጥር 24/2017 ዓ.ም
በደቡብ ወሎ ዞን ተሁለደሬ ወረዳ በሕዝብ እና በመንግሥት በተደጋጋሚ ይቀርብ የነበረውን የሰላም ጥሪ የተቀበሉ የታጠቁ አካላት በሰላም መግባታቸውን የወረዳው አሥተዳደር አስታውቋል።
በደቡብ ወሎ ዞን በተሁለደሬ ወረዳ 027 ሙጢበልግ እየተባለ በሚጠራው ቀበሌ በተሳሳተ መንገድ ነፍጥ አንግበው የነበሩ አካላት ናቸው የሰላምን መንገድ መርጠው ወደ ሕዝብ እና መንግሥት የተመለሱት።
የታጠቁት አካላት ወደ አካባቢያቸው ሲደርሱ በተሁለደሬ ወረዳ የሥራ ኀላፊዎች አቀባበል ተደርጎላቸዋል።
የተሁለደሬ ወረዳ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኀላፊ ደመቁ አበበ፣ የመከላከያ ሠራዊት መሪዎች፣ ሌሎች የወረዳው የሥራ ኀላፊዎች፣ የጸጥታ መዋቅር መሪዎች፣ የአካባቢው የሃይማኖት አባቶች እና የሀገር ሽማግሌዎች በተገኙበት አቀባበል ስለመደረጉ ከደቡብ ወሎ ዞን የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
#አሚኮ