አሬሮ የካቲት 30/2017 ዓ.ም (ቡሌ ሆራ ዩኒቨርስቲ)
ከቡሌ ሆራ ዩኒሸርሲቲ የተወጣጡ የልኳን ቡድን በ72ተኛው የቦረና ባሊ ስልጣን ሽግግር ላይ ተገኙ።
********
በገዳ እና ባህል ጥናት ኢንስቲትዩት የሚመራዉ የልኳን ቡድን ከስረዓቱ አንድ ቀን በፊት በአሬሮ ወረዳ አረዳ ጅላ በዳሳ በመገኘት በ72ተኛዉ የቦረና ባሊ ርክክብ ላይ ታድመዋል።
የስልጣን ርክክቡ ከፋላሳ ጎጌሳ አባ ገዳ ኩራ ጃርሶ ኩራ ወደ መርዲዳ ጎጌሳ አባ ገዳ ጉዮ ቦሩ ጉዮ ሰላማዊ በሆነ መንገድ የስልጣን ርክክቡ ተከናዉነዋል። በስርዓቱ ላይ ከሀገር ውስጥ እና ከዉጭ ሀገር ትላልቅ የመንግስት ባለስልጣናት ፣የኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት ፕረዘዳንት አቶ ሽመልስ አብዲሳ ፣ ታዋቂ ሙዚቀኞች ፣ አባ ገዳዎች እና ሌሎች ታዳሚዎች የተሳተፋ ሲሆን ፣ ስረዓቱ በደማቅ ሁኔታ ተከናዉነዋል።
በስረዓቱ ላይም የገዳ የእርከን ደረጃ የሚያሳዩ ደበሌዎች፣ ትንሹ ጋሜ፣ ትልቁ ጋሜ፣ ኩሳ፣ ራባ ፣ዶሪ ፣ገዳ ፣ዩባ1ኛ እስከ ዩባ 3ተኛ እንዲሁም ገደሞጂ ጭምር ተገኘተዋል።በተጨማሪም የተለያዩ የባህላዊ መገልገያ መሳሪያዎች፣ የባህላዊ አለባበስ እና ባህላዊ ገልማዎች በመዘጋጀት ለእይታ ለታዳሚዎች ቀርበዋል።
የቡሌ ሆራ ዩኒሸርሲቲ
ከቡሌ ሆራ ዩኒሸርሲቲ የተወጣጡ የልኳን ቡድን በ72ተኛው የቦረና ባሊ ስልጣን ሽግግር ላይ ተገኙ።
********
በገዳ እና ባህል ጥናት ኢንስቲትዩት የሚመራዉ የልኳን ቡድን ከስረዓቱ አንድ ቀን በፊት በአሬሮ ወረዳ አረዳ ጅላ በዳሳ በመገኘት በ72ተኛዉ የቦረና ባሊ ርክክብ ላይ ታድመዋል።
የስልጣን ርክክቡ ከፋላሳ ጎጌሳ አባ ገዳ ኩራ ጃርሶ ኩራ ወደ መርዲዳ ጎጌሳ አባ ገዳ ጉዮ ቦሩ ጉዮ ሰላማዊ በሆነ መንገድ የስልጣን ርክክቡ ተከናዉነዋል። በስርዓቱ ላይ ከሀገር ውስጥ እና ከዉጭ ሀገር ትላልቅ የመንግስት ባለስልጣናት ፣የኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት ፕረዘዳንት አቶ ሽመልስ አብዲሳ ፣ ታዋቂ ሙዚቀኞች ፣ አባ ገዳዎች እና ሌሎች ታዳሚዎች የተሳተፋ ሲሆን ፣ ስረዓቱ በደማቅ ሁኔታ ተከናዉነዋል።
በስረዓቱ ላይም የገዳ የእርከን ደረጃ የሚያሳዩ ደበሌዎች፣ ትንሹ ጋሜ፣ ትልቁ ጋሜ፣ ኩሳ፣ ራባ ፣ዶሪ ፣ገዳ ፣ዩባ1ኛ እስከ ዩባ 3ተኛ እንዲሁም ገደሞጂ ጭምር ተገኘተዋል።በተጨማሪም የተለያዩ የባህላዊ መገልገያ መሳሪያዎች፣ የባህላዊ አለባበስ እና ባህላዊ ገልማዎች በመዘጋጀት ለእይታ ለታዳሚዎች ቀርበዋል።
የቡሌ ሆራ ዩኒሸርሲቲ