አምስቱ አዕማደ ምሥጢራት
ቅድስት ቤተክርስቲያናችን እምነቷን የምትገልጽበት ለሰዎችም የምታስተምርበትና የምትመስከርበት አምስት እዕማደ ምሥጢራት አሏት።
"ናሁ ኅቡዓ ነገረ እነግረከሙ” እነሆ ኅቡዕ (ምሥጢር) እነግራችኋለሁ ፩ ቆሮ: ፲፭: ፶፩ (15፡51) እንዳለ እነዚህ አምስቱ ምሥጢራት አምስቱ ኅቡዓት ተብለውም ይነገራሉ፡፡ አምሰቱም ነገረ መለኮት ናቸው።
#አምስት፡- ቁጥራቸውን ይገልፃል
#አዕማድ፡- ማለት ምስሶዎች ማለት ነው። አንድ ቤት ሲሠራ ሊቆምና ጠንካራ ሊሆን የሚችለው በአዕማድ (ምሰሶዎች) ነውና። ለሃይማኖታችንም መሠረታዊ ምስሶዎች አሏት።
#ምሥጢር፡- ለወዳጅ የሚገለጽ ነገር ሲሆን ለሚያምኑ ሁሉ የሚገለጽና በእምነት ብቻ የሚረዱት በመሆኑ ምሥጢር ይባላል።
አምስቱ አዕማደ ምሥጢራት የሚባሉትም፡-
1.ምሥጢረ ሥላሴ
2.ምሥጢረ ሥጋዌ
3.ምሥጢረ ጥምቀት
4.ምሥጢረ ቊርባን
5.ምሥጢረ ትንሣኤ ሙታን ናቸው።
አንድ ክርስቲያን እነዚህን ጠንቅቆ ከተረዳ መሠረቱ ጠንካራ ዐለት ይሆናል። ለዚህም ነው ቅዱስ ጳውሎስ በ1ኛ ቆሮ.፲፬:፲፱ (14፥19) ላይ "ወባሕቱ በቤተ ከርስቲያን እፈቅድ ኀምስቲ ቃላተ እንግር በልብየ ከመ ለባዕዳንሂ እምሃር እስመ ይኄይስ እምእእላፍ ቃል በነገረ በሐውርት” “አምስት ቃላት በእእምሮዬ ልናገር እወዳለሁ"ብሎ የአምስቱን አዕማደ ምሥጢር በአውነት ለምአመናን ያስተምር የነበረው።
#በቀጣይ ግልጽ በሆነ መንገድ አጠር አጠር አድርገን ምሥጢረ ሥላሴን እናያለን
ቅድስት ቤተክርስቲያናችን እምነቷን የምትገልጽበት ለሰዎችም የምታስተምርበትና የምትመስከርበት አምስት እዕማደ ምሥጢራት አሏት።
"ናሁ ኅቡዓ ነገረ እነግረከሙ” እነሆ ኅቡዕ (ምሥጢር) እነግራችኋለሁ ፩ ቆሮ: ፲፭: ፶፩ (15፡51) እንዳለ እነዚህ አምስቱ ምሥጢራት አምስቱ ኅቡዓት ተብለውም ይነገራሉ፡፡ አምሰቱም ነገረ መለኮት ናቸው።
#አምስት፡- ቁጥራቸውን ይገልፃል
#አዕማድ፡- ማለት ምስሶዎች ማለት ነው። አንድ ቤት ሲሠራ ሊቆምና ጠንካራ ሊሆን የሚችለው በአዕማድ (ምሰሶዎች) ነውና። ለሃይማኖታችንም መሠረታዊ ምስሶዎች አሏት።
#ምሥጢር፡- ለወዳጅ የሚገለጽ ነገር ሲሆን ለሚያምኑ ሁሉ የሚገለጽና በእምነት ብቻ የሚረዱት በመሆኑ ምሥጢር ይባላል።
አምስቱ አዕማደ ምሥጢራት የሚባሉትም፡-
1.ምሥጢረ ሥላሴ
2.ምሥጢረ ሥጋዌ
3.ምሥጢረ ጥምቀት
4.ምሥጢረ ቊርባን
5.ምሥጢረ ትንሣኤ ሙታን ናቸው።
አንድ ክርስቲያን እነዚህን ጠንቅቆ ከተረዳ መሠረቱ ጠንካራ ዐለት ይሆናል። ለዚህም ነው ቅዱስ ጳውሎስ በ1ኛ ቆሮ.፲፬:፲፱ (14፥19) ላይ "ወባሕቱ በቤተ ከርስቲያን እፈቅድ ኀምስቲ ቃላተ እንግር በልብየ ከመ ለባዕዳንሂ እምሃር እስመ ይኄይስ እምእእላፍ ቃል በነገረ በሐውርት” “አምስት ቃላት በእእምሮዬ ልናገር እወዳለሁ"ብሎ የአምስቱን አዕማደ ምሥጢር በአውነት ለምአመናን ያስተምር የነበረው።
#በቀጣይ ግልጽ በሆነ መንገድ አጠር አጠር አድርገን ምሥጢረ ሥላሴን እናያለን