የብሔራዊ ታክስ ሪፎርም ግብረ-ኃይል የበጀት ዓመቱን የመጀመሪያ ግማሽ ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም ገመገመ
*********
የብሔራዊ ታክስ ሪፎርም ግብረ-ኃይል የበጀት ዓመቱን የመጀመሪያ ግማሽ ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ በጉምሩክ ኮሚሽን ዋና መ/ቤት አካሂዷል።
ግብረ-ኃይሉ በታክስ አስተዳደሩ መሰረታዊ ለውጥ ለማምጣት በሚያስችሉ የታክስ ፖሊሲ፣ የሀገር ውስጥ ታክስ አስተዳደር፣ የጉምሩክ ቀረጥና ታክስ አስተዳደር ጉዳዮች ዝርዝር ዕቅድ በማዘጋጀት አፈፃፀሙን በየወሩ እየገመገመ ይገኛል።
በተያዘው በጀት ዓመት የመጀመሪያው 6 ወራት የገቢ አሰባሰብ በዕቅዱ መሰረት በተሳካ ሁኔታ የተፈፀመ መሆኑን እና በቀሪ 6 ወራት በዕቅድ የተያዘውን የገቢ ዕቅድ ለማሳካት ርብርብ ማድረግ እንደሚገባ ግብረ-ኃይሉ አቅጣጫ ማሰቀመጡን የጉምሩክ ኮሚሽን መረጃ ያመለክታል።
በተጨማሪም ለገቢ አሰባሰቡ አጋዥ የሆኑ የስጋት ስራ አመራር ሥርዓትን አጠናክሮ ማስቀጠል፣ የውዝፍ ዕዳ ክትትልን ማጠናከር፣ የጉምሩክ ዋጋን ወቅታዊ ማድረግ፣ የዘመናዊ ቴክኖሎጂ ልማት ሥራዎችን ማጠናከር፣ አዳዲስ ታክስ ከፋዮች ወደ ታክስ ሥርዓቱ እንዲገቡ ክትትል ማድረግ፣ የደረሰኝ እና የሽያጭ መመዝገቢያ መሳሪያ ቁጥጥር እና ክትትልን ማጠናከር ግብረ-ኃይሉ በውይይቱ ያስቀመጣቸው የቀጣይ ወራት አቅጣጫዎች ናቸው።
የብሔራዊ ታክስ ሪፎርም ግብረ-ኃይል ከጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት፣ ከፕላን እና ልማት ሚኒስቴር፣ ከገንዘብ ሚኒስቴር፣ ከገቢዎች ሚኒስቴር እና ከጉምሩክ ኮሚሽን በተወጣጡ ከፍተኛ አመራሮች የሚመራ ግብረ-ኃይል ነው።
*********
የብሔራዊ ታክስ ሪፎርም ግብረ-ኃይል የበጀት ዓመቱን የመጀመሪያ ግማሽ ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ በጉምሩክ ኮሚሽን ዋና መ/ቤት አካሂዷል።
ግብረ-ኃይሉ በታክስ አስተዳደሩ መሰረታዊ ለውጥ ለማምጣት በሚያስችሉ የታክስ ፖሊሲ፣ የሀገር ውስጥ ታክስ አስተዳደር፣ የጉምሩክ ቀረጥና ታክስ አስተዳደር ጉዳዮች ዝርዝር ዕቅድ በማዘጋጀት አፈፃፀሙን በየወሩ እየገመገመ ይገኛል።
በተያዘው በጀት ዓመት የመጀመሪያው 6 ወራት የገቢ አሰባሰብ በዕቅዱ መሰረት በተሳካ ሁኔታ የተፈፀመ መሆኑን እና በቀሪ 6 ወራት በዕቅድ የተያዘውን የገቢ ዕቅድ ለማሳካት ርብርብ ማድረግ እንደሚገባ ግብረ-ኃይሉ አቅጣጫ ማሰቀመጡን የጉምሩክ ኮሚሽን መረጃ ያመለክታል።
በተጨማሪም ለገቢ አሰባሰቡ አጋዥ የሆኑ የስጋት ስራ አመራር ሥርዓትን አጠናክሮ ማስቀጠል፣ የውዝፍ ዕዳ ክትትልን ማጠናከር፣ የጉምሩክ ዋጋን ወቅታዊ ማድረግ፣ የዘመናዊ ቴክኖሎጂ ልማት ሥራዎችን ማጠናከር፣ አዳዲስ ታክስ ከፋዮች ወደ ታክስ ሥርዓቱ እንዲገቡ ክትትል ማድረግ፣ የደረሰኝ እና የሽያጭ መመዝገቢያ መሳሪያ ቁጥጥር እና ክትትልን ማጠናከር ግብረ-ኃይሉ በውይይቱ ያስቀመጣቸው የቀጣይ ወራት አቅጣጫዎች ናቸው።
የብሔራዊ ታክስ ሪፎርም ግብረ-ኃይል ከጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት፣ ከፕላን እና ልማት ሚኒስቴር፣ ከገንዘብ ሚኒስቴር፣ ከገቢዎች ሚኒስቴር እና ከጉምሩክ ኮሚሽን በተወጣጡ ከፍተኛ አመራሮች የሚመራ ግብረ-ኃይል ነው።