የወሎ ማህበረሰብ ድንቅ እሴት፡- "ፋጡማ ቆሪ"
****************
"ፋጡማ ቆሪ" በወሎ አካባቢ ለነፍሰጡር ሴቶች የሚዘጋጅ ባህላዊ በገንፎ የታጀበ የምርቃት ሥነ-ሥርዓት ነው፡፡
በትውልድ ቅብብሎሽ ዛሬ ላይ የደረሰው ስርዓቱ የወሎ ነፍሰጡር ሴቶች እርግዝናቸው 9 ወር ሲደርስ እናቶች የገንፎ እህል አዘጋጅተው በባህላቸው መሰረት ደግሰው አብረው እየበሉ የሚመራረቁበት ነው፡፡
የኢቢሲ ሪፖርተር መታሰቢያ ደረጀ ወደ ወሎ ደጋን አካባቢ ባቀናችበት ወቅት አንድ ለመውለድ የተቃረበች ነፍሰጡር ሴት ከመውለድዋ በፊት በባህሉ መሰረት ምን ዓይነት ቅድመ ዝግጅት ይደረግላታል የሚለውን ቅኝት አድርጋለች፡፡
ድሪያ የለበሱ እናቶች ቀድሞ ከተዘጋጀው ዱቄት ላይ እየወሰዱ ለብዙኃኑ እንዲበቃ አድርገው በትልቅ ድስት ገንፎ ሰርተው ያቀርባሉ፡፡ ሰብሰብ ብለውም ለነፍሰጡሩዋ ሴት በሰላም ተገላገይ፣ ልጅሽን ወልደሽ እቀፊ እያሉ ይመርቃሉ፡፡
https://web.facebook.com/EBCzena/posts/pfbid02YhQGUQM2xr9Tm9jMeEJFv2WWXHKRcj7eZqAm14RwdNm3NHoSVNXFLjgHBEPyJYXjl
****************
"ፋጡማ ቆሪ" በወሎ አካባቢ ለነፍሰጡር ሴቶች የሚዘጋጅ ባህላዊ በገንፎ የታጀበ የምርቃት ሥነ-ሥርዓት ነው፡፡
በትውልድ ቅብብሎሽ ዛሬ ላይ የደረሰው ስርዓቱ የወሎ ነፍሰጡር ሴቶች እርግዝናቸው 9 ወር ሲደርስ እናቶች የገንፎ እህል አዘጋጅተው በባህላቸው መሰረት ደግሰው አብረው እየበሉ የሚመራረቁበት ነው፡፡
የኢቢሲ ሪፖርተር መታሰቢያ ደረጀ ወደ ወሎ ደጋን አካባቢ ባቀናችበት ወቅት አንድ ለመውለድ የተቃረበች ነፍሰጡር ሴት ከመውለድዋ በፊት በባህሉ መሰረት ምን ዓይነት ቅድመ ዝግጅት ይደረግላታል የሚለውን ቅኝት አድርጋለች፡፡
ድሪያ የለበሱ እናቶች ቀድሞ ከተዘጋጀው ዱቄት ላይ እየወሰዱ ለብዙኃኑ እንዲበቃ አድርገው በትልቅ ድስት ገንፎ ሰርተው ያቀርባሉ፡፡ ሰብሰብ ብለውም ለነፍሰጡሩዋ ሴት በሰላም ተገላገይ፣ ልጅሽን ወልደሽ እቀፊ እያሉ ይመርቃሉ፡፡
https://web.facebook.com/EBCzena/posts/pfbid02YhQGUQM2xr9Tm9jMeEJFv2WWXHKRcj7eZqAm14RwdNm3NHoSVNXFLjgHBEPyJYXjl