ሳይሆን ለመመስገን፣ ለምደነቅ ወይም ለመከበር ተብሎ ስለሚሆን እና እነዚህም ጠባያት ደግሞ የሥጋ ጠባዮች ስለሆኑ እነዚህ መግቢያ አድርጎ ሰይጣን እንዳያስተውም ስለሚፈራ ነው።
ሁልጊዜም ቢሆን በቤተ ክርስቲያን ታሪክ ችግሮች የሚፈጠሩት ቲኦሎጂን ወይም ነገረ እምነትን ለአማኞች ድኅነት ቅድሚያ ሰጥቶ ማስተማር ቀርቶ የራስን ፍላጎት ለማርካት በሚደረግ አላስፈልጊ ዕውቀት መሰል ክርክር ውስጥ ነው። ይህ ጉዳይ ከዚህም አልፎ ክርክር በማያስነሡ ጉዳዮች እንኳን የሚነሣው የተለየ ነገር ተናግሮ ማስደነቅና መከበርንም ሆነ ሌላ ነገር ሲፈለግ የሚያጋጥም ስለሆነ ነው።
እንዲያውም ከዚህም አልፎ አሁንም ብዙ ገዳማዊያን ሊቃውንት አንድ መሠረታዊ ሥጋታቸውን ደጋግመው ሲያነሡ አይቻለሁ። ይህም አሁን አሁን ኦርቶዶክሳዊያን ክርስትናን ወደ ዕውቀትነት እያወረዱት ነው የሚል ሥጋት ነው። ይህ ሥጋታቸው ደግሞ ተራ ሥጋት አይደለም። በአሁኑ ጊዜ በርከት ያሉ ኦርቶዶክሳዊያን ክርስትናን ያጠኑታል፣ ለማወቅ ይጥሩለታል፣ ይወድዱታል፤ በዚያም ደስተኞች ይሆናሉ። ከዚህም የተነሣ ወደ እውነተኛው የመዳን ዕውቅት ሳይሸጋገሩ ልክ እንደ አካዳሚክ ዕውቀት በጥናት ላይ ብቻ ተመሥርተው ይቀራሉ። ይህ ባሕል እየሆነና እየተለመደ ስለሔደ ክርስቲያናዊው እውነተኛው ሕይወታዊውን ዕውቀት አካዳሚያዊ ዕውቀት እየተካው ስለሆነ ክርስትና አደጋ ላይ ነው ያለው ይላሉ። ይህን የሚሉበት ምክንያት ክርስቲያናዊ ዕውቀት ከእግዚአብሔር ጋር ኅብረት በማድረግ ከመነገር በላይ ወደ ሆነው ወደ ሚኖረው ዕውቀት ካልተሸጋገረ አካዳሚያዊ ዕውቀት ይሆናል። ከዚህም የተነሣ እንደማንኛውም አካዳሚያዊ ነገር በሰው አእምሮ መረዳት (reasoning) ላይ ይወሰንና ስፉሕ አእምሮ ያላቸው ሰዎች ሲመጡ ያንን የሚያሻሽሉት የሚያስፋፉት፣ ጠባብ አእምሮ ያላቸው ሲይዙት ደግሞ እንደዚያው የሚያጠብቡት ይሆንና በመጨረሻም በሒደት የመበረዝ ፣ የመለወጥ ፣ የመጥፋት አደጋ ይገጥመዋል የሚል ተጨባጭ ሥጋት አላቸው።
የእኛ ዘመን ተሟጋች ትውልድ ደግሞ አብዛኛው መጀመሪያ የተማረው ዘመናዊውን ወይም ምዕራባዊውን ትምህርት ነው። ይህን አስቀድሞ መማር በራሱ ችግር አይደለም፤ ( ሊሆንም አይችልም። እነ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ፣ ቅዱስ ባስልዮስ፣ ቅዱስ ጎርጎርዮ ዘእንዚናዙ እና ሊሎችም ጭምር መጀመሪያ የተማሩት የዓለሙን ፍልስፍና ነውና። የእኛ ትውልድ ግን ከመጠን በላይ ሲስተማቲክ በሆነው አካዳሚክስ ውስጥ ከማለፉ የተነሣ ነገሮችን ሳያውቀው በዚያ መጠን የመበየን፣ ጨርሶ የማወቅ እና አቋም መያዝ ድረስ መድረሱ ችግሩ ብቅ እያለ መሆኑን ያመለክታል ብዬ አስባለሁ። ምክንያቱም ክርስትናን ከትምህርት ከሚገኝ መጠነኛ ዕውቀት በሕይወት ወደሚደረስበት የመረዳት ዕውቀት ካልተሸጋገረ ችግር መግጠሙ አይቀሬ ነው። በሰሚዕ የሚገኝ ዕውቀት እና እምነት መግቢያ በር እንጂ መድረሻ አዳራሽ ወይም ቤት አይደለምና።
ይህ ጉዳይ ራሱን የቻለ ብዙ እንድንማማር የሚያደርግ ስለሆነ ጊዜውና ችሎታው ያላችሁ ሁሉ በዚህ ጉዳይ ሰፋ ያለ ዕውቀት ብታካፍሉን ብዙዎቻቸን መንገዳችንን ለማቃናት ብዙ ይጠቅመናል፤ ጉዳዮችን በአካዳሚ መንገድ እና ዓይን ከማየት፣ አለፍ ሲልም እንደ ፖለቲካ አቋምን ከመለካካት ሊያተርፉን ይችላሉ፤ ሲሆን ሲሆን ደግሞ ወደ መንፈሳዊው ዓለም እንድንገባ እና መንገዳችንን ወደዚያ እንድናደርግ ሊረዱን ይችላሉ ብዬ አስባለሁ።
ከሰሞኑ ውይይቶች በተለይ አስተያየት መስጫ ላይ የማያቸው ጥያቄዎች እና መልሶች ብዙዎቹ ትውልዱ ወደዚህ አካዳሚያዊ የነገረ መለኮት ዕውቀት ሳያውቀውም ቢሆን እያደላ መሆኑን የሚጠቁሙ ይመስለኛል። በእኔ መረዳት ኦርቶዶክሳዊ የነገረ ዕውቀት አቀራረብ ቀርቶ ምዕራባዊ የምነለውንና የራሱ ሥነ ሥርዓት ያለውንም ያንን እንኳ የማያሟሉ፣ የነገሮቹን መቅድማቸውን እንኳ በውል ሳናገኘው አንኳር ጉዳዩ ላይ ገብተን እንደዚያ ያለ አስተያየቶች መወራወራችን በእጂጉ ያስፈራል። ሕያው እግዚአብሔር ምስክሬ ነው በእጂጉ ያስፈራል። እኔን እስከገባኝ ደርሰ ከፍተኛ ድፍረት የተሞላው የአላዋቂ ክርክር ወስጥ መሆናችንን በታላቅ ትሕትና (ነገሩ እንኳ ሳስበው ድፍረትም ጭምር ነው) መጠቆም እፈልጋለሁ።
በማኅበራዊ ሚዲያ ልናደርጋቸው የሚገቡንን ውይይቶች እና ትምህርቶች በተመለከተ እኔ ከጠቆምኳቸው እና ከሌሎቹም መሠረታዊ ትውፊቶቻችን አንጻር በማየት በውስጥ መወያየት እና አቀራረቦችን ማስተካከል ይቻላል፤ ይገባለም ብዬ አምናለሁ። አበቃሁ። መልካም ጾም ይሁንልን።
©ዲ/ን ብርሃኑ አድማስ
@mezigebehayimanot
@mezigebehayimanot
@mezigebehayimanot
ሁልጊዜም ቢሆን በቤተ ክርስቲያን ታሪክ ችግሮች የሚፈጠሩት ቲኦሎጂን ወይም ነገረ እምነትን ለአማኞች ድኅነት ቅድሚያ ሰጥቶ ማስተማር ቀርቶ የራስን ፍላጎት ለማርካት በሚደረግ አላስፈልጊ ዕውቀት መሰል ክርክር ውስጥ ነው። ይህ ጉዳይ ከዚህም አልፎ ክርክር በማያስነሡ ጉዳዮች እንኳን የሚነሣው የተለየ ነገር ተናግሮ ማስደነቅና መከበርንም ሆነ ሌላ ነገር ሲፈለግ የሚያጋጥም ስለሆነ ነው።
እንዲያውም ከዚህም አልፎ አሁንም ብዙ ገዳማዊያን ሊቃውንት አንድ መሠረታዊ ሥጋታቸውን ደጋግመው ሲያነሡ አይቻለሁ። ይህም አሁን አሁን ኦርቶዶክሳዊያን ክርስትናን ወደ ዕውቀትነት እያወረዱት ነው የሚል ሥጋት ነው። ይህ ሥጋታቸው ደግሞ ተራ ሥጋት አይደለም። በአሁኑ ጊዜ በርከት ያሉ ኦርቶዶክሳዊያን ክርስትናን ያጠኑታል፣ ለማወቅ ይጥሩለታል፣ ይወድዱታል፤ በዚያም ደስተኞች ይሆናሉ። ከዚህም የተነሣ ወደ እውነተኛው የመዳን ዕውቅት ሳይሸጋገሩ ልክ እንደ አካዳሚክ ዕውቀት በጥናት ላይ ብቻ ተመሥርተው ይቀራሉ። ይህ ባሕል እየሆነና እየተለመደ ስለሔደ ክርስቲያናዊው እውነተኛው ሕይወታዊውን ዕውቀት አካዳሚያዊ ዕውቀት እየተካው ስለሆነ ክርስትና አደጋ ላይ ነው ያለው ይላሉ። ይህን የሚሉበት ምክንያት ክርስቲያናዊ ዕውቀት ከእግዚአብሔር ጋር ኅብረት በማድረግ ከመነገር በላይ ወደ ሆነው ወደ ሚኖረው ዕውቀት ካልተሸጋገረ አካዳሚያዊ ዕውቀት ይሆናል። ከዚህም የተነሣ እንደማንኛውም አካዳሚያዊ ነገር በሰው አእምሮ መረዳት (reasoning) ላይ ይወሰንና ስፉሕ አእምሮ ያላቸው ሰዎች ሲመጡ ያንን የሚያሻሽሉት የሚያስፋፉት፣ ጠባብ አእምሮ ያላቸው ሲይዙት ደግሞ እንደዚያው የሚያጠብቡት ይሆንና በመጨረሻም በሒደት የመበረዝ ፣ የመለወጥ ፣ የመጥፋት አደጋ ይገጥመዋል የሚል ተጨባጭ ሥጋት አላቸው።
የእኛ ዘመን ተሟጋች ትውልድ ደግሞ አብዛኛው መጀመሪያ የተማረው ዘመናዊውን ወይም ምዕራባዊውን ትምህርት ነው። ይህን አስቀድሞ መማር በራሱ ችግር አይደለም፤ ( ሊሆንም አይችልም። እነ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ፣ ቅዱስ ባስልዮስ፣ ቅዱስ ጎርጎርዮ ዘእንዚናዙ እና ሊሎችም ጭምር መጀመሪያ የተማሩት የዓለሙን ፍልስፍና ነውና። የእኛ ትውልድ ግን ከመጠን በላይ ሲስተማቲክ በሆነው አካዳሚክስ ውስጥ ከማለፉ የተነሣ ነገሮችን ሳያውቀው በዚያ መጠን የመበየን፣ ጨርሶ የማወቅ እና አቋም መያዝ ድረስ መድረሱ ችግሩ ብቅ እያለ መሆኑን ያመለክታል ብዬ አስባለሁ። ምክንያቱም ክርስትናን ከትምህርት ከሚገኝ መጠነኛ ዕውቀት በሕይወት ወደሚደረስበት የመረዳት ዕውቀት ካልተሸጋገረ ችግር መግጠሙ አይቀሬ ነው። በሰሚዕ የሚገኝ ዕውቀት እና እምነት መግቢያ በር እንጂ መድረሻ አዳራሽ ወይም ቤት አይደለምና።
ይህ ጉዳይ ራሱን የቻለ ብዙ እንድንማማር የሚያደርግ ስለሆነ ጊዜውና ችሎታው ያላችሁ ሁሉ በዚህ ጉዳይ ሰፋ ያለ ዕውቀት ብታካፍሉን ብዙዎቻቸን መንገዳችንን ለማቃናት ብዙ ይጠቅመናል፤ ጉዳዮችን በአካዳሚ መንገድ እና ዓይን ከማየት፣ አለፍ ሲልም እንደ ፖለቲካ አቋምን ከመለካካት ሊያተርፉን ይችላሉ፤ ሲሆን ሲሆን ደግሞ ወደ መንፈሳዊው ዓለም እንድንገባ እና መንገዳችንን ወደዚያ እንድናደርግ ሊረዱን ይችላሉ ብዬ አስባለሁ።
ከሰሞኑ ውይይቶች በተለይ አስተያየት መስጫ ላይ የማያቸው ጥያቄዎች እና መልሶች ብዙዎቹ ትውልዱ ወደዚህ አካዳሚያዊ የነገረ መለኮት ዕውቀት ሳያውቀውም ቢሆን እያደላ መሆኑን የሚጠቁሙ ይመስለኛል። በእኔ መረዳት ኦርቶዶክሳዊ የነገረ ዕውቀት አቀራረብ ቀርቶ ምዕራባዊ የምነለውንና የራሱ ሥነ ሥርዓት ያለውንም ያንን እንኳ የማያሟሉ፣ የነገሮቹን መቅድማቸውን እንኳ በውል ሳናገኘው አንኳር ጉዳዩ ላይ ገብተን እንደዚያ ያለ አስተያየቶች መወራወራችን በእጂጉ ያስፈራል። ሕያው እግዚአብሔር ምስክሬ ነው በእጂጉ ያስፈራል። እኔን እስከገባኝ ደርሰ ከፍተኛ ድፍረት የተሞላው የአላዋቂ ክርክር ወስጥ መሆናችንን በታላቅ ትሕትና (ነገሩ እንኳ ሳስበው ድፍረትም ጭምር ነው) መጠቆም እፈልጋለሁ።
በማኅበራዊ ሚዲያ ልናደርጋቸው የሚገቡንን ውይይቶች እና ትምህርቶች በተመለከተ እኔ ከጠቆምኳቸው እና ከሌሎቹም መሠረታዊ ትውፊቶቻችን አንጻር በማየት በውስጥ መወያየት እና አቀራረቦችን ማስተካከል ይቻላል፤ ይገባለም ብዬ አምናለሁ። አበቃሁ። መልካም ጾም ይሁንልን።
©ዲ/ን ብርሃኑ አድማስ
@mezigebehayimanot
@mezigebehayimanot
@mezigebehayimanot