[ኢብን ሽፋ - Ibn Shifa]


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic
Category: not specified


እራስህን ሁል ጊዜ ለቁርኣንና ለሀዲስ ተጎታች አድርግ!
በአንድ ነገር ላይ ከቁርኣንና ከሀዲስ ማስረጃ ሳታገኝ አቋም አትያዝ!
ሁሌም ለሰዎች መልካምን ተመኝ!
ለሀቅ እንጂ ለሰዎች ወጋኝ አትሁን

Related channels  |  Similar channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Category
not specified
Statistics
Posts filter


ታላቅ ዓሊም ሸይኽ ሙሀመድ ቢን አማን አል-ጃሚ (ረሂመሁላህ) እንዲህ አሉ:-
በሰዎች ላይ መለሳለስ ማለት ትርጉሙ ሐቅን ግልፅ አለማድረግና መደበቅ ማለት አይደለም! ፣ ለሰዎች እዚህጋ ትክክለኛ ዐቂዳ አለ፣ በዚህ ደግሞ በሽተኛ የሆነ እምነት አለ፣ ጠማማ ፊርቃዎችና ጤነኛ መንገድም አለ ተብሎ ሳይገለፅ በስመ ኢስለም መሰብሰብ ብቻ አይደለም!፣ ይህን ግልፅ አድርጎ መናገር ግዴታ ነው!!።” [ሸርህ ፈታዋ አል-ሀመዊየህ…]
#join ⤵️ ቴሌግራም
https://telegram.me/IbnShifa
https://telegram.me/IbnShifa


Forward from: قناة الشيخ الدكتور حسين بن محمد
‏صورة من حسين عبد الله


የሰለፊየህ ሚንሀጅ ማለት: ትክክለኛ ትክክል ነህ የሚባልበት፣ስህተተኛ ተሳስተሀል የሚባልበት፣ለአጥፊው አጥፊ ነህ የሚባልበት፣ለጠመመው ጠመሀል የሚባልበት፣ ከትክክለኛው የእምነት ጉዳና ላፈነገጠው ከሀቅ አፈንግጠኃል የሚባልበትና ከተደነገገው ሸሪዓ መሸራረፍ፣ማንጓደድ፣ ማሻሻልና አለአግባብ ማግራራት ሚባል የሌለበት ቀጥተኛ የእምነት ጎዳና ነው፤ ምክንያቱም የነብያት ውርስ ነውና። ነብያት ደግሞ ይዘውት በመጡት የእምነት ጉዳና ላይ ዝንፍ የማይሉ ነበሩ።
📚መርሐበን ያ ጣሊበል ዒልም :59

ትርጉም:- ሰሚር ጀማል


Forward from: قناة الشيخ الدكتور حسين بن محمد
قال الإمام ربيع بن هادي المدخلي -حفظه الله- :

"المنهج السلفي الذي يقول

للمصيب: أصبت،
وللمخطئ: أخطأت،
وللمبطل: أبطلت،
وللضال: ضللت،
وللمنحرف: انحرفت،

ليس فيه مداهنة، لأنه ميراث الأنبياء الذين جاءوا بالحق وبه يعدلون"

📚 مرحباً يا طالب العلم - ص59
https://t.me/HussinAssilty


السلام عليكم ورحمة الله وبركاته

ሰበር ዜና
ለት/ት ፈላጊዎች በሙሉ
ባሁኑ ሰዓት
አልቀሲም ዩኒቨርሲቲ በዓለም አቀፍ ደረጃ  ት/ት ፈላጊዎች ካሉበት ሁነዉ የትምህርት መረጃቸዉን በማስገባት የዕድሉ ተጠቃሚ እንዲሆኑ  በዚህ ሊንክ
https://registration.qu.edu.sa/admin

**Oduu simbirtuu BARATTOOTAAF**

Yeroo Ammaa kana Al-Qasiim Universitiitti galmeen waan eegaleef namootni carraa barnootaa barbaaddatan bakkuma jiranitti karaa liinkii kanaa

https://registration.qu.edu.sa/admin

galmaahanii dokumentii isaanii galfachuu danda'u.

እንዲጠቀሙ በር ከፍቷል
መልካም እድል


Forward from: طه خضر أبوعبد الله
مصيبة هذا العصر المثقفون الجهلة المتعالمون

قال العلامة الوادعي: وترى بعض الناس يحفظ له ثلاثة أو أربعة مواضيع ويقوم بها في المساجد يركض وينطح، ثم يلقبه أصحابه بشيخ الإسلام، فهل هذا هو العلم؟ بل العلم أن تجلس على الحصير حتى تحتك ركبتك ولا بد أن تصبر على الجوع والعري، وانظر إلى حالة أصحاب رسول الله صلى الله عليه وعلى آله وسلم وما صبروا عليه.
والمصيبة التي ابتلى بها المسلمون هي جهلهم بدينهم، فمن حفظ له آيات وأحاديث وقام يتكلم بها وخصوصا إذا أعطي فصاحة، قالوا: هذا هو الشيخ.
والحمد لله تتضح الحقيقة كما قيل:
إذا حمل الفصيح فلا تهبه ... فتلك الاستعارة مستعارة
ولذ بالعلم والعرفان تلقى ... فصاحته انتهت من غير غارة
فيجب علينا أن نزن العلماء والدعاة إلى الله بالعلم والعمل

تحفة المجيب للوادعي


Forward from: Sheik Abuzar Hassen Abu tolha
مَسْأَلَة_العُذْرِ_بالجَهْلِ_في_مَسَائلِ_العَقِيدَةِ_وَالتَّوْحِيْدِ.pdf
6.3Mb

📝 አዲሱ መፅሐፍ ተለቀቀ
      ¯◉¯◈¯◉¯◈¯◉¯🔍

↙️ عنوان: ➴➴➴
  ↩️ مَسْأَلَة العُذْرِ بالجَهْلِ في مَسَائلِ العَقِيدَةِ وَالتَّوْحِيْدِ والشّرْكِ قَبْلَ بُلُوغِ الحُجَّةِ


↘️ ርዕስ፦ ➴➴➴
↪️ «መስአለቱል-ኡዝር ቢል-ጀህል ፊ መሳኢል አል-ዓቂዳህ ወተውሂድ ወሽርክ ቀብለ-ቡሉጊል ሁጃህ»

📝 إِعْدَادُ وَجَمْعُ : الشَّيْخِ أَبي طَلْحَةَ أَبِي ذَرِّ بْنِ حَسَنِ بْنِ إِمَامٍ الْإتْيُوْبِي الْوَلَّوِيّ عَفَا اللهُ عَنْهُ وَعَنْ وَالِدَيْهِ آمِيْن

📝 ዝግጅት፦ ሸይኽ አቡ ጦልሃ አቡ ዘር ብን  ሀሰን ብን ኢማም አል-ኢትዮጵይ አል-ወሎውይ አላህ እሳቸውንም ወላጆቻቸውንም ይቅር ይበል ኣሚን!

🏝 በመፅሃፉ
➩ በኡዝር ቢል ጀህል ዙሪያ ሰፊ ዳሰሳ የተደረገበት ሲሆን በተለይ በአሁኑ ሰዓት አንዳንድ ሰዎች ወጣቱን እየበረዙት ባለው ወቅታዊ መከራ ላይ ጥሩ መፍትሔ ነው።

🏝 በነጥቡ ላይ ብዥታ ወይም ግርታ ያለበት ማንኛውም ጧሊብ (ደረሳ) ወይም ቃልቻ ጠንከር ብሎ ያንብብ!

💬 ኪታቡ 360 አካባቢ ገፆችን ያካተተ ሲሆን በአላህ ፍቃድ በትዕግሥት ላነበበ ሰው ሹብሃውን ሁሉ አጥር ላይ እንደሚያንጠለጥል አያወላውልም።

✍️ ይህንን ታላቅ ስራ ያበረከቱልን ሸይኻችንን አላህ እድሜያቸውን ያርዝምልን! ከዚህም በላይ ኡማውን ለመጥቀም የሚችሉበትን ሀይል ያጎናፅፋቸው!

💬 pdፉን ለማግኘት 👇👇👇👇
https://t.me/UstazAbuzarhassenAbutolha/12772


Forward from: طه خضر أبوعبد الله
Video is unavailable for watching
Show in Telegram
❌ جماعة التبليغ
❌ والإخوان المسلمون
❌ والسّرورِيّون
❌ وحزب التَّحرير
❌ ومن يُعْطَفُ عليهم

👈 كُلًّها فتن عُرِضَت عليكم

أنتم أمام الاختبار والامتحان

🎙العلامة محمد أمان الجامي رحمه الله


الرد_على_أبي_بكر_الأحباشي_وبيان_ما_افتراه_على_من_يسميهم_بالوهابية.pdf
476.8Kb
⤵️⤵️

አዲስ PDf

الرد على أبي بكر الأحباشي وبيان ما افتراه على من يسميهم بالوهابية

አህባሹ አቢበክር ወሃቢያ ብሎ በሚጠራቸው ሰዎች ላይ በቀጠፈው ቅጥፈት የተሰጠ ምላሽ

بقلم الشيخ أ.د حسين بن محمد بن عبد الله السلطي الإثيوبي نازل مكة المكرمة حفظه الله

✍🏻አዘጋጅ:-  ሸይኽ ዶ/ር ሑሰይን ኢብኑ ሙሀመድ ኢብኑ ዐብደላህ አስ-ስልጢ (ሀፊዘሁላህ) ከሳዑዲ ዐረቢያ

(ዐረቢኛ የምትችሉ pdf ን አውርዳችሁ አንብቡት)

https://t.me/HussinAssilty
https://t.me/HussinAssilty


ትንሹ ዒድ ባህላዊ በዓል ወይስ እንደ አምልኮ ዘርፍ የተያዘ ቢድዐ?!

—————
ከዒደል ፊጥር ማግስት ጀምሮ የሚፆመውን 6ቀን የሸዋል ፆምን ተከትሎ ዒደል ፊጥር በወጣ በሳምንቱ የተወሰኑ ሙስሊሞች ዘንድ የሚከበር የሸዋል ፍቺ ወይም ትንሹ ዒድ በመባል የሚታወቅ በዓል አለ። ይህ በዓል እንደ ሸሪዓ ምንም አይነት ማስረጃ የሌለው በዋናነት ወደ ደቡብ ያሉ የተወሰኑ ብሔረሰቦች ዘንድ የሚከበር መሰረተ ቢስ የሆነ በዓል ነው። በተለይ አላህ ምንም አይነት ማስረጃን ያላወረደበት ይህ በዓል ስልጤ፣ ጉራጌና ሀረሪ ብሔረሰብ ዘንድ በልዩ ሁኔታ የሚከበር በዓል ነው። ዲናችን ሙሉ ነው። ከሁለቱ ዒድና ከሳምንታዊ ጁምዓ ውጪ ምንም ይሁን ምን አዲስ ፈጠራ (ቢድዐ) ነው። በዲናችን ላይ አዲስ ፈጠራ ሁሉ ደግሞ ጥመት ነው። የአላህ መልእክተኛ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) በየ ሳምንት ጁምዓ ኹጥባቸው ላይ እንዲህ ይሉ ነበር:-
«…የነገሮች ሁሉ ሸር ማለት (በዲን ላይ) አዲስ ፈጠራ ነው፣ አዲስ ፈጠራ (ቢድዐ) ሁሉ ጥመት ነው» ሙስሊምና ነሳኢይ የዘገቡት ሲሆን፣ ነሳኢይ «ጥመት ሁሉ የእሳት ነው» የሚል ዘገባ ጨምሯል፣ ሰነዱም ሶሂህ ነው።

ይህ በዓል ከላይ የጠቀስኩላችሁ ብሔረሰቦች ዘንድ የሚከበር መሰረቱ ገጠር የነበረ ቢሆንም ከጊዜ ወዲህ ግን በየ ከተማውም በተለየ መልኩ ሌሎች ብሔረሰቦችም ተሳትፈውበት መከበር ጀምሯል። ለበዓሉም ልክ እንደሌሎች በሸሪዓ እንደተጠቀሱ በዓሎች (እንዲያውም በበለጠ መልኩ) የተለያዩ ዝግጅቶች ሲደረጉ ይስተዋላል። ታዲያ ማስረጃ የሌለው በዓል እስከሆነ ድረስ ምንም ይሁን ምን፣ መውሊድን ጨምሮ መላው የአለማችን ህዝብ ቢያከብረው እንኳን ቢድዐ ከመሆን አይወገድም!!። ቢድዐ ደግሞ ጥመት ነው፣ ጥመት ሁሉ የእሳት ነው።

በትንሹ ዒድ ላይ አንዳንድ ስለ ዲናቸው ግንዛቤ አላቸው የሚባሉ፣ ሸሪዓው ከሚያግራራው ውጭ እያግራሩ ህዝብ ዘንድ ተደማጭነት ለማግኘት የሚዳክሩ ሰዎች የሚያነሱት ብዥታ አለ። እሱም "ምን ችግር አለው? ቢከበር ባህል ነው እንጂ ሃይማኖታዊ ይዘት የለውም" ይላሉ።

መልስ:-
1ኛ, ባህላዊ በዓል ቢሆንስ በዚህ መልኩ በየ አመቱ እየጠበቁ በድምቀጥ ማክበሩን ማን ፈቀደው?

የሙስሊሞች ሸይኽ በመባል የሚታወቁት ታላቁ ሊቅ ሸይኹል ኢስላም ኢብኑ ተይሚየህ (ረሂመሁላህ) የሸዋልን ስምንተኛውን ቀን እንደ በዓል አድርገው የሚይዙና (የደጋጎች ዒድ) ብለው የሰየሙ ሰዎችን አስመልክተው እንዲህ ይላሉ:-

(وأما ثامن شوال : فليس عيداً لا للأبرار ولا للفجار , ولا يجوز لأحد أن يعتقده عيداً, ولا يحدث فيه شيئاً من شعائر الأعياد ) ا. هـ. الاختيارات الفقهية ص/199

የሸዋል ስምንተኛው ቀንማ ለደጋጎችም ሆነ ለጠማሞች ዒድ አይደለም!። ለአንድም ሰው እለቱን ልዩ የመደሰቻ ዒድ ቀን አድርጎና አምኖ መያዝ አይፈቀድለትም!። በእለቱም ምንም አይነት ለዒድ ከሚንፀባረቁ ነገሮች ማንፀባረቅ አይፈቀድለትም!።” [አል-ኢኽትያራት አል-ፊቅሂየህ 199]

ታላቁ የኢስላም ሊቅ ኢምሙ ዐብዲልዐዚዝ ቢን ባዝ (ረሂመሁላህ) በውስጣቸው ሸሪዓን የሚፃረር ነገር ባይኖርባቸው እንኳን እንደ ባህል (ልማድ) ተደርገው የሚከበሩ በዓላትን በተመለከተ ተጠይቀው ሲመልሱ እንዲህ ይላሉ:- “ከሁለቱ ዒዶች ውጪ ማንኛውንም ዒድ አድርጎ መያዝ አይፈቀድም!። የእርዱ ቀን ዒድ (ዒደል አድሃ) እና ዒደል ፊጥር፣ እነዚህ ናቸው የሙስሊሞች ዒድ ማለት። እንዲሁም በየ ሳምንቱ የሚመጣው የሚሰገድበት እለተ ጁም ነው። በተረፈ በየ አመቱ የሚሽከረከር የሚሰባሰቡበት የሆነን ዒድ መያዝ መሰረት የሌለው ተግባር ነው። ከነቢዩ  (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) በኋላ ሶሃቦችም ይሁኑ ታቢዒዮች 3ቱ ክፍለ ዘመናት ውስጥ የነበሩ ትውልዶችም እንዲህ ያሉ በዓላትን አላከበሩም!። በኛ ላይ ግዴታው እነሱ የተጓዙበትን መከተልና በመንገዳቸው መጓዝ ብቻ ነው… ሰዎች መልካም ነው ብለው የሚያስቡት የሚደጋገም ባህል ካላቸው ሀቁን ካወቁና ከተረዱ በኋላ ያንን ባህል መተው ግዴታ ይሆንባቸዋል…” [የሸይኹ ዌብሳይት ላይ በድምፅም በፅሁፍም አለ።]

2ኛ, እንደ አምልኮ ዘርፍ ነው የሚይዙት።
2.1, ለዒደል ፊጥ ከሚያደርጉት ዝግጅት የበለጥ ለዚህ ቀን ነው  የሚዘጋጁት።
2.2, በዋናናት አባቶችና እናቶች የሸዋልን 6ቀን አከታትለው የሚፆሙት የዚህን ቀን ፍቺ ለማክበር ነው።
2.3, በተጋነነ መልኩ ለዒደል ፊጥር ሀይላቸውን ቆጠብ አድርገው ለዚህ ቀን ግን ሀይላቸውን አሟጠው ይጨርሱና ከፊታችን ለሚመጣው ዒደል አድሃ እንኳን በቂ ዝግጅት አያደርጉም። ለዚህም ነው ታላላቅ የኢስላም ሊቃውንቶች "አንድ ቢድዐ በተተካ ቁጥር ሌላ አንድ ሱንና ይሰርዛል" የሚሉት።
2.4, ዝግጅቱን በዋናነት የሚያከብሩ ሰዎች ሲጠየቁ የሸዋል 6ቀን ፆም ፍቺ (ዒድ) ነው ብለው ነው የሚናገሩት እንጂ ባህል ነው የሚል አመለካከት የላቸውም። ይህ (ባህል ነው) የሚለው አመለካከት ጠንካራ አቋም ያላቸው የሱና ሰዎች "ትንሹ ዒድ ቢድዐ ነው" ብለው ሲያስጠነቅቁ እነ ሸህ ገራገር ህዝቡ ዘንድ ተወዳጅነት ለማግኘት ሲጠየቁ የፈበረኩት አመለካከት ነው። ይህን አመለካከት ሲፈበርኩ ግን ይህን ሁሉ እውነታ ያውቁታል። እያወቁ ሀቁን ይደብቁታል፣ ያምታቱታል። ይህ ደግሞ አላህ እንዲህ በማለት አይሁዶችን የወቀሰበት አደገኛ ተግባር ነው:-

وَلَا تَلْبِسُوا الْحَقَّ بِالْبَاطِلِ وَتَكْتُمُوا الْحَقَّ وَأَنتُمْ تَعْلَمُونَ

«እውነቱንም በውሸት አትቀላቅሉ፡፡ እናንተም የምታውቁ ስትሆኑ እውነትን አትደብቁ፡፡» አል-በቀረህ 42

3ኛ, እንዲህ ያሉ በዓላት ላይ ሌላው ከባድ አደጋ!! የተለያዩ የኢስላምና የሙስሊሙ ጠላቶች እንዲህ ያሉ አዳዲስ በዓላትን ቀንና መስለው በተለየ መልኩ በየ ሚዲያዎቻቸው እያስተዋወቁ ሙስሊሙ በሀይማኖቱ ከተደነገጉ ብርቅዬ በዓላት እንዲዘናጋና ከሀይማኖቱ ተቃራኒ መንገድ እንዲጓዝ ይሰራሉ።
ወላሁ አዕለም!!
✍🏻 ኢብን ሽፋ: (t.me/ibnshifa)

የተለያዩ ት/ቶችን ለማግኘት የቴሌግራም 👇👇 ቻናላችን #join በማድረግ ይቀላቀሉ
https://telegram.me/IbnShifa
https://telegram.me/IbnShifa




Video is unavailable for watching
Show in Telegram
#join ⤵️⤵️ ቴሌግራም ቻናል
https://telegram.me/IbnShifa
https://telegram.me/IbnShifa


Video is unavailable for watching
Show in Telegram
#join ⤵️⤵️ ቴሌግራም ቻናል
https://telegram.me/IbnShifa
https://telegram.me/IbnShifa


Video is unavailable for watching
Show in Telegram
#join ⤵️⤵️ ቴሌግራም ቻናል
https://telegram.me/IbnShifa
https://telegram.me/IbnShifa


👉 ሸሪዓዊ እውቀትን በተለያዩ አገራት ርቀት ሆናችሁ በ online መቅራት (መማር) የምትፈልጉና የተለያዩ ቦታዎች የምትቀሩ ወንድም እህቶች፣ እንዲህ ባሉ በመንሀጃቸውና በመልካም ስነ-ምግባራቸው በምናውቃቸው ወንድሞ እህቶች ተማሩ!!


📲 مَرْكَزُ الْإِمَامِ ابْنِ تَيْمِيَّةَ السَّلَفِيِّ فِيْ الْبَثِّ الْمُبَاشِرِ.

↪️ ኢብን ተይሚያ on line የእውቀት ማእከል!

ታላቅ ብስራት ለእውቀት ፈላጊ ለወንድም ለሴትም ተማሪዎች እነሆ ኢብን ተይሚያህ የኦንላይን መርከዛችን ካለፈው አመት ጀምሮ ተማሪዎችን ቃዒደቱ ኑራኒየ፣ የቁርአን ንባብ፣ የቁርአን ሒፍዝ እያስተማረ ለከፍታ እያበቃ ይገኛል።

መርከዙ በ on line የሚሰጠው ትምህርት

1, ለጀማሪዎች ቃዒደቱ ኑራኒያ
2, ቁርአን ነዞር (በእይታ በተጅዊድ)
3, ቁርአን ሂፍዝ (ሽምደዳ)

📲 ትምህርቱ የሚሰጠው በ tellegram livestream ላይ ሲሆን ወንድ እና ሴቶችን ለየብቻ ነው የሚያስተምረው።

⌚️የቂርአት ግዜ በተመለከተ ደግሞ ከ 04:00 ጀምሮ እስከ 06:00 ድረስ ነው ትምህርት የሚሰጠው።

🔊 ልብ ይበሉ ማእከላችን ተማሪዎችን ኑራኒያ ወይም ቁርአን በእይታ ወይም በሒፍዝ ካስጨረሰ ቡሀላ ሰርተፍኬት (የምስክር ወረቀት) በመስጠት ያስመርቃል።

📙 "شفاء الجهل التعلم"

📙 "የአላዋቂነት መድሀኒቱ መማር ነው።"


ሴቶች ለመመዝገብ ወደዚህ ግሩፕ ግቡ
⇣⇣⇣       ⇣⇣⇣        ⇣⇣⇣
t.me/memmezgbiya
t.me/memmezgbiya

ወንዶች ለመመዝገብ ወደዚህ ግሩፕ ግቡ
⇣⇣⇣       ⇣⇣⇣        ⇣⇣⇣
t.me/memezgbiyawend
t.me/memezgbiyawend


ሶላት የማትሰግዱ ሰዎች ምን ምክንያት አላችሁ?!
…     …     …
በጠና የታመሙ ሰዎች እንኳን ሳይቀሩ ሶላት ለመተው ምንም ምክንያት የላቸውም!።

ታላቁ ዓሊም ሸይኽ ሷሊህ ቢን ፈውዛን አል-ፈውዛን (ሀፊዘሁላህ) እንዲህ አሉ:-
“አንዳንድ አላዋቂያን ሃኪም ቤት በህክምና አልጋ ላይ ሆነው መውረድ በማይችሉበት ደረጃ ላይ ይሆናሉ፣ አልያም ነጃሳ የነካባቸውን ልብስ መቀየር የማይችሉ ይሆናሉ፣ ወይም ደግሞ ተይሙም የሚያደርጉበት አፈር አይኖራቸውም፣ አልያም (ተይሙም የሚያደርጉበትን አፈር) የሚያቀብላቸው አይኖርም ይሆናል።

በነዚህ ምክንያቶች ሶላቷን ከጊዜዋ ያዘገዩዋታል። እንዲህ ያሉ ምክንያቶች ከተወገዱልኝ በኋላ እሰግዳለሁ ይላሉ።

ይህ እጅግ በጣም ትልቅ የሆነ ስህተት ነው!!። ሶላትንም ማበላሸት ነው። ለዚህ ክስተት የዳረገው አላዋቂነትና (የእውቀት ባለቤቶችን) ጠይቆ አለመረዳት ነው።

በእንዲህ ያለ ደረጃ ላይ ታሞ ያለ ሰው ግዴታ የሚሆንበት፣ በሚችለው ደረጃ ሆኖ ሶላቱን በጊዜው መስገድ ነው። በእንዲህ ያለ አስቸጋሪና ከባድ ህመም ላይ ያለ ሰው ባለበት ደረጃ መስገድ ነው ያለበት። ያለ ተይሙምና ልብሱ ነጃሳ ሆኖ ቢሰግድም እንኳ ሶላቱ ተቀባይነት አለው።
አምላካችን አላህ እንዲህ ብሏል:-

فَاتَّقُوا اللَّهَ مَا اسْتَطَعْتُمْ

«አላህንም የቻላችሁትን የክል ፍሩት!።» አት-ተጋቡን 16

ወደ ቂብላ መዞር እንኳ ሳይችል ቀርቶ ያለ ቂብላ ቢሰግድ ሶላቱ ትክክለኛና ተቀባይነት አለው።”
[አል ሙለኸስ አል-ፊቅሂያ 1/75]

ብዙ ሰዎች ባለማወቅ በእንዲህ ያለ ከፍተኛ ህመም ላይ ሲሆኑ ሶላታቸውን ይዘናጋሉ፣ በእንዲህ ያለ ጊዜ ይበልጥ ሶላታቸውን በጥንቃቄ ጊዜውን ተጠባብቀው ሊሰግዱ ይገባል።

ጭራሹኑ አላህ ሙሉ ጤና ሰጥቷችሁ ሶላታችሁን የማትሰግዱ ሰዎች ሆይ! እስኪ አንድ ኣፍታ ቆም ብላችሁ አስተውሉ!! ሶላት ማለት እንዲህ ያለ የጠና ህመም ላይ የሆኑ ሰዎች ላይ እንኳ ሳይቀር ግዴታ ናት!!።

ሶላት በእንዲህ ያለ ሁኔታ ላይ እንኳ ሳይቀር ግዴታ ከሆነ፣ ምክንያታችሁ ምንድነው?!፣ ነገ አላህ ፊት መልሳችሁ ምን ይሆናል?!። ሶላት ላለ መስገድ ለሴት ልጅ በሸሪዓው ከተጠቀሰው ምክንያት ውጪ ለሴትም ሆነ ለወንድ ምንም አይነት ምክንያት የለም!!።
✍🏻ኢብን ሽፋ (t.me/ibnshifa)

የተለያዩ ት/ቶችን ለማግኘት የቴሌግራም ቻናላችን ⤵️ #join በማድረግ ይቀላቀሉ
https://telegram.me/IbnShifa
https://telegram.me/IbnShifa




ነቢዩ አደራ ያሉትን ዊትር ሶላት በህይወት እስካለን በረመዷን ውስጥም ከረመዷን ውጭም አደራ!!
—————
ዊትር ማለት:- በቋንቋ ደረጃ ነጠላ ቁጥር ማለት ነው። ለምሳሌ:- 1:3:5:7… እንደማለት ነው። ነቢዩ () "አላህ ነጠላ (ብቸኛ) ነው፣ ነጠላ የሆነን ነገር ይወዳል" እንዳሉት ማለት ነው፣ [ነሳኢይና ትርሚዚይ ዘግበውታል።]

ዊትር ሸሪዓዊ ትርጉሙ:- ከዒሻ ሶላት በኋላ የሱብሂ ሶላት ወቅት እስኪገባ ድረስ ባለው ጊዜ ውስጥ የምትሰገድ  እጅግ በጣም ጠንካራ ሱንና የሆነች ነጠላ ቁጥር (1፣3፣5፣7፣9 ረከዓ) የሆነች ሶላት ናት።

ነቢዩን እንወዳለን ስንል በምላስ ብቻ ሳይሆን፣ ዲኑን ለማሰራጨት በነበራቸው ጉግት፣ ህዝባቸውን ከሺርክ ወደ ተውሒድ ለመጥራት በነበራቸው የማይነቃነቅ ወኔ፣ ዘውትር ከቢድዐ በማስጠንቀቅ ላይ በነበራቸው ፅኑ አቋም፣ በስነ-ምግባራቸው፣ በቸርነታቸው፣ በአዛኝነታቸው፣  በቅንነታቸው፣ ቤታቸው ሲገቡ ሲወጡ ከቤተሰባቸው በሚያደርጉት እንቅስቃሴ፣ ለሶላት በነበራቸው ልዩ ውዴታ፣ በሚያበዟዋቸው በነበሩ ጠንካራ የሱና ሶላቶች… ወዘተ፣ በሁለመናቸው ወደን ልንከተላቸው ይገባል!!።

አንዱን ጥሎ ሌላውን ማንጠልጠል ከአንድ ትክክለኛ የነቢዩ ወዳጅ ነኝ ከሚል ሰው አይጠበቅም!!። አንድ ሰው ምን ቢያቅተው  ነቢዩን ከልቡ የሚወዳቸው ከሆነ ጠንካራ ሱናዎቻቸውን ለመከተል መጣጣር አለበት።
ጠንካራ ከሆኑ የነቢዩ ሱናዎች ውስጥ ይህችን ከዒሻ ሶላት በኋላ ጀምሮ የሱብሂ ሶላት እስኪገባ ባለው ጊዜ ውስጥ የምትሰገደዋ ዊትር ሶላት ጠንካራ ሱናቸው ናት። ይህቺ ጠንካራ የሆነችው ሱንና ሶላታቸው በረመዷን ወር ብቻ የምትሰገድ ሳትሆን በህይወት እስካለን ልንሰግዳት የምትገባ ነቢዩ ይህቺን ዱኒያን ለቀዋት እስኪሄዱ አቋርጠዋት የማያውቁ ጠንካራ ሱናቸው ናት።

ይህችን ጠንካራ የሆነችዋን ሱናቸውን ነቢዩ ለአቢሁረይራ (ረዲየላሁ ዐንሁ) አደራ ብለውታል። ሶሃቦችን አደራ ያሉበት ነገር ደግሞ ለኡማው ሁሉ አደራ ነው።
①, ከአቢሁረይራ (ረዲየላሁ ዐንሁ) ተይዞ እንዲህ አለ:- «ወዳጄ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) በሶስት ነገሮች መክረውኛል:- (ከረመዷን ውጪ ካሉ) ሁሉም ወራቶች ሶስት፣ሶስት ቀን እንድፆም፣ ከአዶሃ ሶላት ሁለት ረከዓ (ቢሆን እንኳን) እንድሰግድ፣ ሶላተል ዊትርንም ከመተኛቴ በፊት (ቢሆን እንኳ) እንድሰግድ።» [ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል።] የአዶሃ ሶላት ሁለት ረከዓ ብቻ አይደለም፣ 2፣2 እያደረጉ እስከ 8ና 4 ረከዓ መስገድ ነው፣ ነገር ግን ምን ቢያቅትህ 2,ረከዓ ቢሆን እንኳን ስገድ ማለታቸው ነው።

የሶላተል ዊትርም የተሻለና በላጩ ጊዜ ከሌሊቱ የመጨረሻው ክ/ጊዜ የለይል ሶላት መስገጃ ማብቂያ ሰዓት አካባቢ ነው። አንድ ሰው ከተኛው በኋላ ላልነሳ እችላለሁ ብሎ ከፈራ ግን የዒሻ ሶላት ከተሰገድ በኋላ ባለው ጊዜ ከመተኛቱ በፊት ሰግዶ መተኛት ይችላል።
②, ከጃቢር (ረዲየላሁ ዐንሁ) ተይዞ የአላህ መልእክተኛ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) እንዲህ ብለዋል:- «ከሌሊት በመጨረሻው ክፍለ ጊዜ ላልነሳ እችላለሁ ብሎ የፈራ ሰው በመጀመሪያው ክ/ጊዜ ዊትሩን ይስገድ፣ ከሌሊቱ በመጨረሻው ክ/ጊዜ መነሳትን የከጀለ ሰው በመጨረሻው ክ/ጊዜ ይስገድ፣ የሌሊቱ የመጨረሻው ክ/ጊዜ ሶላት መላኢካዎች የሚሳተፉበት ነው። (በመሆኑም) ይህ የተሻለ (በላጭ) ነው።» [ሙስሊም ዘግበውታል።]

ዊትር ሶላት ምንም እንኳን ግዴታ ባይሆንም፣ ነቢዩ ልዩ ትኩረት ሰጥተውት የቁርኣን ባለቤት የሆነውን ሙስሊም ያዘዙበት የጠነከረ ሱና ነው።

③, ከዐሊይ ኢብን አቢ ጧሊብ (ረዲየላሁ ዐንሁ) ተይዞ፣ የአላህ መልእክተኛ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) እንዲህ ብለዋል:- «እናንተ የቁርኣን ባለቤቶች ሆይ! ዊትር ሶላትን ስገዱ፣ አላህ ነጠላ (ብቸኛ) የሆነ ጌታ ነውና ነጠላ የሆነን ነገር ይወዳል።» [አቡዳውድ፣ ነሳኢይና ትርሚዚይ የዘገቡት ሲሆን ትርሚዚይ ሀዲሱን ሀሰን ነው ብለውታል።]

ነቢዩ ለዊትር ሶላት ሚስቶቻቸውን (ቤተሰቦቻቸውን) ይቀሰቅሱ ነበር።
④, እውነተኛዋ የእውነተኛው ልጅ የሆነችው እናታችን ዓኢሻ (ረዲየላሁ ዐንሃ) እንዲህ አለች:- «የአላህ መልእክተኛ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) ከለይል ሶላት ይሰግዱ ነበር፣ ዊትርን በሰገዱ ጊዜ “ዓኢሻ ሆይ! ተነሺ ቁሚ ዊትርን ስገጂ ይሉኝ” ነበር።» [ሙስሊም ዘግበውታል።]

ለይል ሶላትን የሚሰግድ ሰው ዊትርን የሚሰግደው የለይሉን 8,ረከዓ ከሰገደ በኋላ ነው።
⑤, ከኢብኑ ዑመር (ረዲየላሁ ዐንሁ) ተይዞ፣ ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) እንዲህ ይሉ ነበር:- «በሌሊት የሶላታችሁን መጨረሻ ዊትር አድርጉት።» [ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል።]

በዊትር ሶላት ውስጥ ከፋቲሃ ቀጥሎ ሶስቱን ሱራዎች መቅራት የተወደደ (ሱንና) ነው።
⑥, ኡበይ ኢብን ከዕብ (ረዲየላሁ ዐንሁ) እንዲህ አለ:- «ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) በሰቢህ ኢስሚ ረቢከል አዕላ፣ በቁል ያ-አዩሃል ካፊሩን፣ በቁል ሁወ አላሁ አሀድ ዊትር ያደርጉ ነበር።» [ኢማሙ አህመድ፣ አቡዳውድና ነሳኢይ ዘግበውታል።]
የቁርኣን ሱራዎች ቅደም-ተከተሉን በጠበቀ መልኩ ይቀራቸዋል።

ዊትር ሶላትን ከሶስት ረከዓ በለይም መስገድ ይፈቀዳል። ዋናው ግን ከላይ በመግቢያው እንደጠቀስኩላችሁ ነጠላ የሆነ ቁጥር መሆን አለበት።
⑦, እናታችን ዓኢሻ (ረዲየላሁ ዐንሃ) እንዲህ አለች:- «ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) በዘጠኝም በአምስትም ረከዓ ዊትር ያደርጉ ነበር።» [ሙስሊም ዘግበውታል።]
✍🏻 ኢብን ሽፋ (t.me/ibnshifa)

የተለያዩ ት/ቶችን ለማግኘት የቴሌግራም 👇👇 ቻናላችን #join በማድረግ ይቀላቀሉ
https://telegram.me/IbnShifa
https://telegram.me/IbnShifa



20 last posts shown.