ብቸኝነቴ አይሰብረኝም!
ከእራስ ጋር ንግግር፦ "ብቻዬን ብሆንም ያሰብኩበት ሳልደርስ አላቆምም፤ ቢደክመኝም ከሙከራዬ አልገታም፤ ጫናዎች ቢበዙብኝም፣ ተስፋዬ ቢጨልምም፣ ደጋፊ ባጣም፣ የሚረዳኝ ባይኖርም፣ ደጋግሜ ብሰበርም፣ በሰዎች ዘንድ ዋጋ ባይኖረኝም ለእራሴ ብዬ በከባዱ መንገድ እጓዛለሁ፣ ለቤተሰቦቼ ብዬ መክፈል ያለብኝን ዋጋ እከፍላለሁ፣ ለምወዳቸውና ለሚወዱኝ ስል እስከ ጥግ እፋለማለሁ፣ በእኔ በኩል እንዲጠቀሙ የምፈልጋቸው ሰዎች እንዲጠቀሙ፣ ፈጣሪዬ በእኔ እንዲደሰት፣ ለላቀው ክብርም እንዲያጨኝ ስል እርሱ በሚወደው መንገድ እራሴን እሰራለሁ፣ ለብዙዎችም ብቁ አድርጌ እገኛለሁ። ብዙ የማይመቹ ሁኔታ ውስጥ እራሴን ባገኝም እለት እለት ሁኔታዎች ለእኔ እንዲመቹ ለማድረግ መትጋቴን እቀጥላለሁ።
አዎ! ብቸኝነቴ አይሰብረኝም፤ መገፋቴ እራሴን እንድጠላ አያደርገኝም፤ መጠላቴ ለእራሴ የምሰጠውን ቦታ አያሳንሰውም፣ መውደቅ መሰበሬ ተስፋቢስ ሰው አያደርገኝም፣ ብቻዬን መቅረቴ፣ የሚያምንብኝ ማጣቴ፣ የሚደግፈኝ፣ የሚያግዘኝ፣ የሚያበረታኝ ማጣቴ ከጉዞዬ አይገታኝም፣ ፍፁም ወደኋላ አያስቀረኝም፣ መቼም በእራሴ እንዳዝንና ተሰብሬ እንድቀር አያደርገኝም። እራሴን አውቃለሁ፣ ፍላጎቴን አውቃለሁ፣ ወዴት እንደምሔድ፣ ምን እንደማደርግ፣ በእያንዳንዱ እርምጃዬ ውስጥ ማን አብሮኝ እንዳለ ጠንቅቄ አውቃለሁ። ተፈጥሮዬን አከብራለሁ፣ ማንነቴን እወደዋለሁ፣ በእኔነቴ እኮራለሁ፣ በአምላኬ ሃይል፣ በፈጣሪዬ መንፈስ እተማመናለሁ፣ በተሰጠኝ ፀጋ፣ በታደልኩት መክሊት ከልቤ አምናለሁ። የምኖረው ለማንም ሳይሆን ለምወደው ሰውነቴ ነው፣ የምኖረው ለማንም ሳይሆን በእኔ ለሚደሰቱ፣ በእኔ ለሚያርፉና በእኔ ምክንያት ፈጣሪያቸውን ለሚያመሰግኑ ነው። እግዚአብሔር አምላኬ ያለምንም ቅድመሁኔታ እንደሚወደኝ አውቃለሁ።
አዎ! ጀግናዬ..! "ብቸኝነቴ አይሰብረኝም፤ ማጣት ዋጋዬን አያሳንስም፤ ስብራቴ ህይወቴን ጥላሸት አይቀባው፤ በሰዎች የሚሰጠኝ መጥፎ እስተያየት ከጉዞዬ አያደናቅፈኝም፤ ከእራሴ በላይ በሚያስብልኝ አምላኬ የማይሸረሸር መተማመን አለኝ።" ብለህ ለእራስህ ንገረው። ከእራስህ መምጣት ላለበት ብርታት፣ ከውስጥህ መመንጨት ላለበት በእራስመተማመን፣ በማንነት ሊገለፅ ለሚገባው ጀግንነትህ ማንንም አትጠብቅ፣ ማንም እርሱን እንዲልህ አትጠብቅ፣ ማንም የልብ ትርታህን እንዲያወራልህ አትጠባበቅ። እራስህን በማበርታት ህይወትህን በከፍታው ላይ ምራው፣ ለአንተነህ ተገን ሁን፣ ለምትፈልገው ነገር እራስህን በመስጠት፣ ለምርጫህ እስከመጨረሻው በመታገል የምትመኘውን ሰው ሁን። አስደናቂው አዕምሮህ፣ አስገራሚው የአምላክህ መንፈስህ የማይቻለውን እንዲያስችልህ ፍቀድ፣ የማይታመን የሚመስለውን አምኖና በተግባር አድርጎ በገሃድ እንዲገለፅ አድርግ።
ከእራስ ጋር ንግግር፦ "ብቻዬን ብሆንም ያሰብኩበት ሳልደርስ አላቆምም፤ ቢደክመኝም ከሙከራዬ አልገታም፤ ጫናዎች ቢበዙብኝም፣ ተስፋዬ ቢጨልምም፣ ደጋፊ ባጣም፣ የሚረዳኝ ባይኖርም፣ ደጋግሜ ብሰበርም፣ በሰዎች ዘንድ ዋጋ ባይኖረኝም ለእራሴ ብዬ በከባዱ መንገድ እጓዛለሁ፣ ለቤተሰቦቼ ብዬ መክፈል ያለብኝን ዋጋ እከፍላለሁ፣ ለምወዳቸውና ለሚወዱኝ ስል እስከ ጥግ እፋለማለሁ፣ በእኔ በኩል እንዲጠቀሙ የምፈልጋቸው ሰዎች እንዲጠቀሙ፣ ፈጣሪዬ በእኔ እንዲደሰት፣ ለላቀው ክብርም እንዲያጨኝ ስል እርሱ በሚወደው መንገድ እራሴን እሰራለሁ፣ ለብዙዎችም ብቁ አድርጌ እገኛለሁ። ብዙ የማይመቹ ሁኔታ ውስጥ እራሴን ባገኝም እለት እለት ሁኔታዎች ለእኔ እንዲመቹ ለማድረግ መትጋቴን እቀጥላለሁ።
አዎ! ብቸኝነቴ አይሰብረኝም፤ መገፋቴ እራሴን እንድጠላ አያደርገኝም፤ መጠላቴ ለእራሴ የምሰጠውን ቦታ አያሳንሰውም፣ መውደቅ መሰበሬ ተስፋቢስ ሰው አያደርገኝም፣ ብቻዬን መቅረቴ፣ የሚያምንብኝ ማጣቴ፣ የሚደግፈኝ፣ የሚያግዘኝ፣ የሚያበረታኝ ማጣቴ ከጉዞዬ አይገታኝም፣ ፍፁም ወደኋላ አያስቀረኝም፣ መቼም በእራሴ እንዳዝንና ተሰብሬ እንድቀር አያደርገኝም። እራሴን አውቃለሁ፣ ፍላጎቴን አውቃለሁ፣ ወዴት እንደምሔድ፣ ምን እንደማደርግ፣ በእያንዳንዱ እርምጃዬ ውስጥ ማን አብሮኝ እንዳለ ጠንቅቄ አውቃለሁ። ተፈጥሮዬን አከብራለሁ፣ ማንነቴን እወደዋለሁ፣ በእኔነቴ እኮራለሁ፣ በአምላኬ ሃይል፣ በፈጣሪዬ መንፈስ እተማመናለሁ፣ በተሰጠኝ ፀጋ፣ በታደልኩት መክሊት ከልቤ አምናለሁ። የምኖረው ለማንም ሳይሆን ለምወደው ሰውነቴ ነው፣ የምኖረው ለማንም ሳይሆን በእኔ ለሚደሰቱ፣ በእኔ ለሚያርፉና በእኔ ምክንያት ፈጣሪያቸውን ለሚያመሰግኑ ነው። እግዚአብሔር አምላኬ ያለምንም ቅድመሁኔታ እንደሚወደኝ አውቃለሁ።
አዎ! ጀግናዬ..! "ብቸኝነቴ አይሰብረኝም፤ ማጣት ዋጋዬን አያሳንስም፤ ስብራቴ ህይወቴን ጥላሸት አይቀባው፤ በሰዎች የሚሰጠኝ መጥፎ እስተያየት ከጉዞዬ አያደናቅፈኝም፤ ከእራሴ በላይ በሚያስብልኝ አምላኬ የማይሸረሸር መተማመን አለኝ።" ብለህ ለእራስህ ንገረው። ከእራስህ መምጣት ላለበት ብርታት፣ ከውስጥህ መመንጨት ላለበት በእራስመተማመን፣ በማንነት ሊገለፅ ለሚገባው ጀግንነትህ ማንንም አትጠብቅ፣ ማንም እርሱን እንዲልህ አትጠብቅ፣ ማንም የልብ ትርታህን እንዲያወራልህ አትጠባበቅ። እራስህን በማበርታት ህይወትህን በከፍታው ላይ ምራው፣ ለአንተነህ ተገን ሁን፣ ለምትፈልገው ነገር እራስህን በመስጠት፣ ለምርጫህ እስከመጨረሻው በመታገል የምትመኘውን ሰው ሁን። አስደናቂው አዕምሮህ፣ አስገራሚው የአምላክህ መንፈስህ የማይቻለውን እንዲያስችልህ ፍቀድ፣ የማይታመን የሚመስለውን አምኖና በተግባር አድርጎ በገሃድ እንዲገለፅ አድርግ።