Good Morning #Ethiopiaዬ : ኢትዮጵያ እና ሱማሊያ አንካራ ውስጥ ያካሄዱትን የመጀመሪያ ዙር የቴክኒክ ድርድር ትናንት አጠናቀዋል።
ኹለቱ ወገኖች፣ ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይና ፕሬዝዳንት ሐሰን ሞሐመድ በአንካራው ስምምነት ያስቀመጡትን ራዕይ ወደ ተግባር ለመለወጥ ቁርጠኛ መኾናቸውንና ኹለቱን አገራት ተጠቃሚ ለሚያደርግ ዘላቂ ልማት መሠረት መጣላቸውን በጋራ ባወጡት መግለጫ ገልጸዋል።
ኹለቱ ወገኖች ለኹለተኛው ዙር የቴክኒክ ድርድር በመጋቢት ወር ለመገናኘት ከስምምነት ላይ መድረሳቸውንም ጠቅሰዋል።
በቴክኒክ ድርድሩ የኢትዮጵያን ልዑካን ቡድን የመሩት ውጭ ጉዳይ ሚንስትር ጌዲዮን ጢሞቲዮስ ሲኾኑ፣ የሱማሊያን ልዑካን ቡድን የመሩት ደሞ የውጭ ጉዳይ ሚንስትር ደኤታ ዓሊ ኦማር ናቸው።
ኹለቱ ወገኖች፣ ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይና ፕሬዝዳንት ሐሰን ሞሐመድ በአንካራው ስምምነት ያስቀመጡትን ራዕይ ወደ ተግባር ለመለወጥ ቁርጠኛ መኾናቸውንና ኹለቱን አገራት ተጠቃሚ ለሚያደርግ ዘላቂ ልማት መሠረት መጣላቸውን በጋራ ባወጡት መግለጫ ገልጸዋል።
ኹለቱ ወገኖች ለኹለተኛው ዙር የቴክኒክ ድርድር በመጋቢት ወር ለመገናኘት ከስምምነት ላይ መድረሳቸውንም ጠቅሰዋል።
በቴክኒክ ድርድሩ የኢትዮጵያን ልዑካን ቡድን የመሩት ውጭ ጉዳይ ሚንስትር ጌዲዮን ጢሞቲዮስ ሲኾኑ፣ የሱማሊያን ልዑካን ቡድን የመሩት ደሞ የውጭ ጉዳይ ሚንስትር ደኤታ ዓሊ ኦማር ናቸው።