TGStat
TGStat
Type to search
Advanced channel search
English
Site language
Russian
English
Uzbek
Sign In
Catalog
Channels and groups catalog
Search for channels
Add a channel/group
Ratings
Rating of channels
Rating of groups
Posts rating
Ratings of brands and people
Analytics
Search by posts
Telegram monitoring
TGStat Bot
Bot to get channel statistics without leaving Telegram
Start bot
ad
Telegram Analytics
Subscribe to stay informed about TGStat news.
Read channel
ad
TGAlertsBot
Monitoring of keywords in channels and chats
Subscribe
ad
SearcheeBot
Your guide in the world of telegram channels
Start bot
ad
Statistics
Favorites
Natinael Mekonnen
@NatinaelMekonnen21
Channel's geo and language:
Ethiopia, Amharic
Category:
Shock content
ይህ ቻናል ቴሌግራሜ hacked በተደረገበት ሳት ለግዝያዊነት የከፈትኩት ቻናል ነው ለችግር ጊዜ ይጠቅማል ተቀላቀሉ
በቀጥታ መረጃዎችን ለመስጠት ከፈለጉ
@NatnaelMekonnen7
በማለት መረጃዎችን ይላኩልን
I blog about marketing and sales
Buy ads: https://telega.io/c/NatinaelMekonnen21
Related channels
|
Similar channels
Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Category
Shock content
Statistics
Favorites
Is this your channel?
Confirm
Канал в реестре блогеров РКН?
Confirm
Channel history
Posts filter
Select month
April 2025
March 2025
February 2025
January 2025
December 2024
November 2024
October 2024
September 2024
August 2024
July 2024
June 2024
May 2024
April 2024
March 2024
February 2024
January 2024
December 2023
November 2023
October 2023
September 2023
August 2023
July 2023
June 2023
May 2023
April 2023
March 2023
February 2023
January 2023
December 2022
November 2022
October 2022
September 2022
August 2022
July 2022
June 2022
May 2022
Hide deleted
Hide forwards
Natinael Mekonnen
19 Apr, 11:02
Open in Telegram
Share
Report
በትግራይ በባህላዊ የማዕድን ሥራ ላይ የተሰማሩ እስከ 10 ሚሊዮን ብር እንደሚቀጡ ተገለፀ!
በትግራይ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት በቅርቡ በወጣው የተሻሻለ የማዕድን አስተዳደር ደንብ መሠረት በባህላዊ የማዕድን ማምረት ሥራ ላይ የተሰማሩ ግለሰቦች እስከ 10 ሚሊዮን ብር እንደሚቀጡ ተገለጸ።
ረቡዕ ሚያዚያ 8 ቀን 2017 ዓ.ም. ተግባራዊ እንዲደረግ በክልሉ ለሚገኙ ለመሬትና ማዕድን እንዲሁም ለሚመለከታቸዉ የመንግስት መ/ቤቶች በተላከዉ ደብዳቤ ይህኑን ደንብ እንዲያስፈፅሙ መጠየቁን ካፒታል ተመልክቷል።
ደንቡ በባህላዊ እና አነስተኛ ደረጃ የማዕድን ሥራዎች ላይ እንደ ሜርኩሪ እና ሳይናይድ ያሉ ጎጂ ኬሚካሎችን መጠቀም እንዲሁም ብረትና ብረት ነክ ማዕድናትን ያለዕሴት መጨመር መላክ ወይም መሸጥን በግልጽ ይከለክላል።
ይህን ጣሰ ማንኛውም ሰው ከ15 እስከ 20 ዓመት በሚደርስ ጽኑ እስራት ሊቀጣ የሚችል ሲሆን በተጨማሪም እስከ 10 ሚሊዮን ብር የሚደርስ የገንዘብ መቀጮ ሊጣልበት ይችላል።
ከዚህም በላይ ጥፋተኛው ከማዕድን ሥራው ጋር የተያያዙ ማሽነሪዎችና ሌሎች መሣሪያዎች እንዲሁም ያመረተው ማዕድን ይወረሳል፤ ድርጅቱም ዝግ የሚሆን ከመሆኑም በላይ ለወደፊቱ በማንኛውም የማዕድን ሥራ እንዳይሳተፍ ይታገዳል።
የክልሉ መንግሥት ይህንን ደንብ ያወጣው በፌዴራል መንግሥት በተሰጠው ሥልጣን መሠረት መሆኑ የተጠቆመ ሲሆን ዓላማውም የአካባቢን ደህንነት መጠበቅ፣ የሰዎችንና የእንስሳትን ጤና መከላከል እንዲሁም ማዕድናት በአግባቡ ተጨምሮባቸው ለሀገር ጥቅም እንዲውሉ ማድረግ ነው ተብሏል።
924
0
0
6
Natinael Mekonnen
18 Apr, 13:04
Open in Telegram
Share
Report
ሰበር ዜናው ቀጥሏል
የጎጃሙ ጽንፈኛ ቡድን እያለቀ ነው። ከውስጥ ለፀጥታ ኃይል እየተሰጡ ያሉ መረጃዎች ኦፕሬሽኑን እያሳኩት ይገኛሉ።
ትናት በገደብ ስልጠና እና ስብሰባ ላይ የነበሩት 126 ታጣቂዎች የተደመሰሱ ሲሆን ዛሬም በአደባባይ ስብሰባ ላይ የነበሩት 135 ስብሰባ ላይ እያሉ አንድም ሳይቀር ተደምስሰዋል። ከተደመሰሱት ውስጥ የትኞቹ አመራሮች እንዳሉ እየጣራ ነው::
1.4k
0
0
19
Natinael Mekonnen
18 Apr, 13:04
Open in Telegram
Share
Report
breaking news loading… ጎጃም/ፋኖ
1.4k
0
0
1
Natinael Mekonnen
18 Apr, 13:04
Open in Telegram
Share
Report
ሰበር
መንበሩ ጌታዬ ከጠባቂዎቹ ጋር ተደመሰሰ
በምስራቅ ጎጃም ዞን ሞጣ ሰዴ አካባቢ በሚንቀሳቀሰው የጽንፈኛው ፋኖ ቡድን ላይ የፀጥታ ኃይል በወሰደው እርምጃ መንበሩ ጌታዬ የተባለ የአማራ ፋኖ በጎጃም 2ኛ ተፈራ ዳምጤ ክ/ጦር መሪ የሆነውን ጨምሮ ጠባቂዎቹ እና ሌሎች አመራሮች ተደምስሰዋል። በዚሁ አካባቢ የነበሩ ቁጥራቸው ከ100 በላይ ታጣቂዎችም ተደምስሰዋል
1.4k
0
0
6
Natinael Mekonnen
18 Apr, 13:04
Open in Telegram
Share
Report
Prev
Next
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የፋሲካ በዓልን ምክንያት በማድረግ ማዕድ አጋሩ
*********
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ፣ መጪውን የፋሲካ በዓል ምክንያት በማድረግ፣ ዝቅተኛ ገቢ ላላቸው የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ሠራተኞች እና ጽሕፈት ቤቱ ለሚያሳድጋቸው ሕጻናት ማዕድ አጋርተዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ የማዕድ ማጋራት መርሐ ግብሩን ዛሬ ጠዋት ማከናወናቸውን የጽሕፈት ቤቱ መረጃ ያመላክታል።
1.2k
0
0
2
Natinael Mekonnen
18 Apr, 13:04
Open in Telegram
Share
Report
Prev
Next
ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው በሃኖይ የሚገኝ የአይነስውራን ትምህርት ቤትን ጎበኙ
ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው በሃኖይ የሚገኘውን የአንደኛና ሁለተኛ ደረጃ የአይነስውራን ት/ቤት ጎብኝተዋል፡፡
ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው፤ ዛሬ የቬትናም ሶሻሊስት ሪፐብሊክ ቀዳማዊት እመቤት ማዳም ነኹ በሃኖይ የሚገኘውን የአንደኛና ሁለተኛ ደረጃ የአይነስውራን ት/ቤት አስጎብኝተውኛል ብለዋል፡፡
ባደረጉት ጉብኝት በቅርቡ ተመርቆ አገልግሎት በመስጠት ላይ ለሚገኘው እና በተለያዩ ክልሎች እየተሰሩ ላሉት አዳዲስ የአይነስውራን አዳሪ ት/ቤቶች የሚሆኑ ተሞክሮዎችን ማግኘታቸውን ጠቅሰዋል፡፡
1.2k
0
0
3
Natinael Mekonnen
17 Apr, 21:49
Open in Telegram
Share
Report
የመከላከያ ሰራዊት በጽንፈኛው ቡድን የስልጠና ማዕከል ላይ በወሰደው እርምጃ አንድ የሻለቃ አመራርን ጨምሮ በርካታ ታጣቂዎች ተደምስሰዋል!
ጀግናው የመከላከያ ሰራዊት ለሰላም ጀርባውን በመስጠት ህዝብን እያሰቃየ በሚገኘው ጥገኛ እና ጽንፈኛ ቡድን ላይ የማያዳግም እርምጃ መውሰዱን ቀጥሏል። በዚህም መሰረት ሰራዊቱ ዛሬ ሚያዚያ 09/2017 ዓ.ም በምስራቅ ጎጃም ዞን እናርጅና እናውጋ ወረዳ ገደብ አካባቢ በስልጠና ላይ በነበሩ የፀረ-ሰላም ቡድኑ አባላት ላይ በወሰደው እርምጃ አንድ የሻለቃ አመራርን ጨምሮ ከአርባ በላይ የቡድኑ አባላት የተደመሰሱ መሆናቸው ታውቋል። በተጨማሪም በእርምጃው አሁንም ብዛት ያለው ታጣቂ የቆሰለ መሆኑና የሟቾች ቁጥር ሊያሻቅብ እንደሚችል ተገልጿል። የጽንፈኛው ቡድን አመራሮች የጓደኞቻቸውን አስ*ከሬን ለማንሳት እንኳን በማይችሉበት ደረጃ እርምጃው ጠንካራ እንደሆነ እየገለጹ ይገኛሉ። ለሰላም አሻፈረኝ ያለውን ይህንን ከሃዲ እና ጸረ ህዝብ የሆነ ቡድን ጀግናው ሰራዊት በሚገባው ቋንቋ እያናገረው ይገኛል። የጽንፈኛው አባላት አሁንም ያላቸው ምርጫ ሁለት ነው እጅ ሰጥቶ ወደ ሰላማዊ ህይወት መመለስ አሊያም የማይቀረውን የሞት ጽዋ መጎንጨት! ይኸው ነው!
1.3k
0
0
10
Natinael Mekonnen
17 Apr, 19:15
Open in Telegram
Share
Report
ትላንት የመከላከያ ፔጅ የፕ/ት መንግስት ኃ/ማርያም መገልገያ አውሮፕላን ከ37 ዓመት በኋላ upgrade እና overhaul ተደርጋ ዳግም መብረር ጀመረች የሚል የምስራች ዜና አወጣ።
ይህን መልካም ዜና አድርገው ከኛ ውጭ “ fact check “ አድራጊ የለም ብሎ በማለት ዜናውን አጣራሁ ብሎ ሀሰት አለ።
ይሄው ዛሬ “የኮሎኔል መንግስቱ ትዝታዎች” የሚል መፅሀፍ የፃፈቺው እና ለቀድሞ ፕሬዚደንቱ ቅርበት ያላት ጋዜጠኛ እና ፀኃፊ ገነት አየለ ዜናው እውነት መሆኑን ከእራሳቸው ፕ/ት መንግስቱን አፍ ጠይቃ አረጋግጣለች።
ጋዜጠኛ ገነትን እያመሠገንን fact check መልሰን fact check የማድረግ ስራችንን እንቀጥላለን። በግሌ እኔ አየር ሃይ ግቢውስጥ ይህን አውሮፕላን ቆሞ አይቼዋለሁ በሰአቱ እየታደሰ ስለነበር አንድ ኮሎኔል የመንግስቱ ሃይለማሪያም እንደበር ነግሮኝ በግዜው ከተወሰነ ጉዞ በላይ መንግስቱ ሃይለማሪያም እንዳልተጏዙበት ነግሮኛል ምክንያቱንም ነዳጅ በጣም ይበላ ስለነበር መንግስቱ ሃይለማሪያም በራሳቸው ትዕዛዝ እንዲቆም አድርገውታል ነበር ያለኝ::
1.4k
0
1
2
Natinael Mekonnen
17 Apr, 19:15
Open in Telegram
Share
Report
#KeneniAdugna
የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች የድምጻዊ አንዱዓለም ጎሳ የችሎት ሂደትን እንዳይታደሙ በፍርድ ቤት ታገዱ።
ዛሬ የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ችሎት በፍቅረኛው ወጣት ሞዴል ቀነኒ አዱኛ ህልፈት ተጠርጥሮ በምርመራ ሂደት ላይ የሚገኘው የአርቲስት አንዱዓለም ጎሳ ጉዳይ በታየበት ችሎት ነው ፍርድ ቤቱ መገናኛ ብዙሃን ችሎቱን እንዳይታደሙ ያገደው፡፡
በዛሬው ችሎት ፖሊስ የመገናኛ ብዙሃን በተለያዩ ጊዜያት “ የችሎቱን ውሎ በተደጋጋሚ አዛብተው ዘግበውታል ” በሚል የምርመራ ሂደቱ ላይ እክል በመፍጠራቸው በችሎቱ እንዳይታደሙ ጠይቋል፡፡
በጉዳዩ ላይ አስተያየት እንዲሰጡ በችሎቱ የተጠየቁት የተከሳሽ ጠበቃ በፊናቸው ፖሊስ ያቀረበውን አቤቱታ እንደሚደግፉ ገልጸዋል፡፡
ችሎቱም ግራ ቀኙን ካደመጠ በኋላ “ መገናኛ ብዙሃን ካሁን በፊት አንድ ጊዜ ተከሳሽ ለፋሲካ በዓል ወጥቶ ኮንሰርት ለማዘጋጀት ጠይቋል፤ ሌላ ጊዜ ደግሞ የሟች የግል ማህደር (ዳይሪ) በተከሳሽ ጠበቃ እጅ ነው የሚገኘው የሚሉ የተዛቡና ሀሰተኛ ዘገባዎች ማቅረባቸው በችሎቱና በምርመራ ሂደቱ ላይ እክል እንደሚፈጥር በመታመኑ የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች (ጋዜጠኞች) ችሎቱን እንዳይታደሙ “ በሚል ብይን ሰጥቷል።
በዛሬው ችሎት የታደሙትን ጋዜጠኞችን በዳኛ ትዕዛዝ እንዲወጡ ተደርገዋል።
መጋቢት 01 ቀን ሌሊት ለመጋቢት 02 ቀን 2017 ዓ.ም. አጥቢያ የመኖሪያ ቤቷ ከሚገኝበት ህንጻ ወድቃ ህይወቷ ማለፉ በተሰማው በወጣት ቀነኒ አዱኛ ህልፈት በፖሊስ የተጠረጠረው ፍቅረኛዋ ድምጻሚ አንዱዓለም ጎሳ በቁጥጥር ስር ውሎ ምርመራ እየተጣራበት ይገኛል።
1.3k
0
0
1
Natinael Mekonnen
17 Apr, 19:15
Open in Telegram
Share
Report
Prev
Next
በርካታ ገንዘብ የያዙ በማስመሰል ከፊትና ከኋላ ሁለት ሁለት መቶ ብሮች በማድረግና ባለ አስር ብሮችን በመጠቅለል የማጭበርበር ወንጀል ሊፈጽሙ የነበሩ ተጠርጣሪዎችን በግል ተበዳይ ጠቋሚነት በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ እያጣራ መሆኑን የየካ ክ/ከተማ ፖሊስ መምሪያ ገለጸ።
ግለሰቦቹ ሆን ብለው በመዘጋጀት በርከት ያለ ገንዘብ የያዙ ለማስመሰል በሁለት መቶ ብሮች የተጠቀለሉ ባለ አስር ብር ኖቶችን በመያዝ የተለያዩ የማታለያ ዘዴዎችን በመጠቀም ሰዎች ላይ የሚያዩትን ጌጣ ጌጥ አታለው በገንዘቡ ለመቀየር ካልሆነም የበለጠ ገንዘብ የሚያገኙበትን ዘዴ ይፈጥራሉ፤ ተጠርጣሪዎቹ በተለያዩ ቦታዎች ላይ እየተንቀሳቀሱ የሚፈፀሙት የወንጀል ድርጊት መሆኑን ፖሊስ በምርመራው አረጋግጧል፡፡
ሚያዚያ 8 ቀን 2017 ዓ/ም በተመሳሳይ የወንጀል አፈጻፀም ሙከራ በየካ ክ/ከተማ ወረዳ 4 ልዩ ቦታው ዳግማዊ ሚኒሊክ ሆስፒታል በፖሊስ ቁጥጥር ስር ውለዋል።
ዳንኤል ታደሰና ታዬ ዋቅጅራ የተባሉ ተጠርጣሪዎች ከላይና ከታች በባለ 200 ብር ኖት የተሸፈነና መሀሉ በባለ 10 የብር ኖት ጥቅልል የተዘጋጀ ገንዘብ በመያዝ በሆስፒታሉ እናቷን እያስታመመች የነበረችና መድኃኒት ለመግዛት የወጣችን ግለሰብ በማግባባት የታወቁ ስፔሻሊስት ዶክተሮች መሆናቸውን በመግለፅ ለማጭበርበሪያነት የያዙትን ጥቅልል ብር ካሳዩኋት በኋላ በ10 ብር እንዲቀይሯት ይጠይቋታል ።
ሁኔታቸው ያላማራት የግል ተበዳይም የግለሰቦቹን ሁኔታ በመጠራጠር ጩኸት ታሰማለች ግለሰቦቹም ወዲያውኑ በአካባቢው ማህበረሰብ ትብብር በፖሊስ ቁጥጥር ስር ይውላሉ፡፡
በምርመራው ለማረጋገጥ እንደተቻለው የግል ተበዳይ በፍጥነት ነቅታባቸው ባይያዙ ወደ ባንክ ወይም ወደ ኤ.ቲ.ኤም ይዘዋት በመሄድ ከዚህ በፊት እንደሚያደርጉት ገንዘብ ሊያስወጧት እንደነበርም ፖሊስ ገልጿል።
የግል ተበዳይ ለፖሊስ በሠጠችው ጥቆማ መነሻነት ምርመራው የቀጠለ ሲሆን ከሳምንት በፊት በተመሳሳይ የወንጀል አፈፃፀም የጣት ቀለበት የተወሰደባት ሌላ ግለሰብ መረጃ ለመስጠት ወደ ወደ ፖሊስ ጣቢያ እንደመጣች ታውቋል፡፡ ሌሎች ተመሣሣይ ወንጀል ተፈፀሞብናል የሚሉ ለየካ ክ/ከተማ ፖሊስ መምሪያ መረጃ መስጠት እንደሚችሉ ፖሊስ አስታውቋል።
ወንጀል ፈጻሚዎች የተለያዩ የማጭበርበሪያ ዘዴዎችን በመጠቀም ወንጀል ሊፈጽሙ እንደሚችሉ ታሳቢ በማድረግ በማንኛውም እንቅስቃሴያችን ትኩረት ሊለየን አይገባም ሲል የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ መልዕክቱን ያስተላልፋል።
*
1.1k
0
0
1
Natinael Mekonnen
16 Apr, 23:10
Open in Telegram
Share
Report
Prev
Next
ከአገልግሎት ውጪ የነበረውን የፕሬዝዳንት መንግሥቱ ሃይለ ማርያም አውሮፕላን ጠግኖ ጥቅም ላይ ማዋል መቻሉ ተገለፀ።
የቀድሞውን የኢትዮጵያ ፕሬዝዳንት መንግሥቱ ሃይለ ማርያም አውሮፕላን ከተጣለበት ጥሻ በማንሳት አፕግሬድና ኦቨር ሆል በማድረግ ከ37 ዓመት በኋላ የበረራ አገልግሎት እንዲሠጥ ማድረጋችን በተቋሙ በሁሉም መስክ ውጤታማ ሥራ እየተሠራ ሥለመሆኑ ማሳያ ነው ሲሉ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ገልፀዋል።
አውሮፕላኑ አሥፈላጊውን ጥገና አግኝቶ መብረር እና ወደ ኃይል መመለስ እንዲችል በሰጠነው መመሪያ መሠረት ለተሳተፋችሁ የአየር ሃይል አመራሮች ቴክኒሺያኖች የመከላከያ ድጋፍ ሰጪ ሁሉ አመሠግናለሁ ሲሉ ፊልድ ማርሻል ብርሀኑ ጁላ ምስጋና አቅርበዋል።
የኢፌዴሪ አየር ሃይል ዋና አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ይልማ መርዳሳ በበኩላቸው አየር ሃይል በሰው ሃይል ግንባታ ፣ትጥቆችን ማሣደግና ከዘመኑ አቅም ላይ ማድረስ፣ መሠረተ ልማቶችን ተቋሙን በሚመጥን ልክ ማሥፋፋት ትኩረት የተሠጠባቸው መሠረታዊ ነጥቦች መሆናቸውን ገልፀው አውሮፕላኑን ጠግኖ ወደ ኃይል መመለስ የዚሁ አንድ አካል ነው ብለዋል።
ዳሽ ፋይፍ ወይም ቡፋሎ በሚል መጠሪያ የሚታወቀውና ለቀድሞው የኢትዮጵያ ፕሬዝዳንት መንግስቱ ኃይለማርያም አገልግሎት ይሠጥ የነበረውን አውሮፕላን ከአንድ ዓመት ጊዜ በላይ አሥፈላጊውን ጥገና በአየር ሃይል ቴክኒሺያኖች በመሥጠት ከሰላሣ ሰባት ዓመት በኋላ ለበረራ ማብቃት እንደተቻለ ተናግረዋል።
ለትራንስፖርት ፣ለፓራሹት ዝላይ፣ የካርጎ አገልግሎት መሥጠት የሚችለው አውሮፕላን ተጠግኖ ወደ ኃይል እንዲመለስ የተቋሙ ከፍተኛ አመራሮች ለሠጡት ድጋፍ ሙያተኞች ላደረጉት ሙያዊ አበርክቶ ሌተናል ጄኔራል ይልማ መርዳሳ ምስጋና አቅርበዋል።
1.3k
0
1
1
10
Natinael Mekonnen
16 Apr, 14:34
Open in Telegram
Share
Report
አብይን በታገልንበት በዚያው ሊንክ ህውሀትን መታገል ጀምረናል እያሉ ነው 😂
ህወሓትን ይዞ ወደ አዲስ አበባ መምጣት አይቻልም። በሌላዉ የኢትዮጵያ ማሕበረሰብ የተጠላ ነዉ። የዓለም አቀፍ ማሕበረሰብም ከአማራጭ ዉጪ ያደረገዉ ድርጅት ነዉ። (አሉላ ሰለሞን)
1.5k
0
0
1
12
last posts shown.
Show more
7 507
subscribers
Channel statistics
Popular in the channel
ምዕ/ሸዋ እና ደ/ምዕ/ሸዋ አዋሳኝ አካባቢ ሲንቀሳቀስ የነበረው የኦነግ/ሸኔ ታጣቂ በሰላም ከነ ትጥቁ ለመከላከያ ሰራዊት እጁን ሰጥቷል:: ሰላም ለኢትዮጵ...
የአሜሪካ መንግስት ፊቱን ያዞረበት ህወሃት ! The Economist እንደዘገበው የአሜሪካ መንግስት ለቀጠናው ጸጥታ ስጋት ናቸው ባላቸው የህወሃት ሹማም...
የሁርሶ ኮንቲጀንት ማሰልጠኛ ትምህርት ቤት መሰረታዊ ወታደሮችን አስመረቀ ። በምረቃ ስነ-ስርዓቱ በክብር እንግድነት የተገኙት የመከላከያ ዘመቻ ዋና መም...
🇪🇹ወደ ኢትዮጵያ የሚገቡ የውጪ ባንኮች አምስት ቢሊዮን ብር ዝቅተኛ ካፒታል ሟሟላት እንደሚኖርባቸው ተገለፀ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ያወጣው አዲስ መመሪ...
የኢ ቢ ኤስ (EBS) ቴሌቪዥን “የአዲስ ምዕራፍ” ፕሮግራም ከስርጭት ታግዶ እንዲቆይ ተወሰነ! በኢ ቢ ኤስ ቴሌቪዥን ጣቢያ የሚተላለፈውና “አዲስ ምዕራ...