ATC NEWS


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic
Category: Education


#ADDIS_ABABA : ETHIOPIA
ለመልዕክት 👇🏻
@mujaabot
For Advertisement👇🏿
@atcads

Related channels  |  Similar channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Category
Education
Statistics
Posts filter


#MoE

ከ2017 ዓ.ም ጀምሮ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተመራቂዎች የዲግሪ ሰርተፊኬት ህትመት በአንድ ማዕከል ሊከወን ነው።

የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) ለሁሉም የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች እና ለሁሉም የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በጻፉት ሰርኩላር "በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚሰጡ ዲግሪዎች ህትመት ወጥ በሆነ መልኩ ደህንነታቸው ተጠበቆ የዲግሪ ማስረጃ/ሰርተፍኬት ህትመት በማዕከል ለማሳተም መታሰቡን" ገልፀዋል።

በመሆኑም ተቋማቱ በዲግሪ የምስክር ወረቀቱ ላይ ሊካተትላችሁ የሚፈልጉትን ሎጎ እና ሌሎች መካተት አለበት የሚሉትን እንዲያካትቱ እንዲሁም በየተቋማቱ በዚህ ዓመት የመውጫ ፈተና ወስደው ያለፉና ለምርቃት የተዘጋጁ የተማሪዎች ዝርዝር እንዲልኩ ሚኒስትሩ አሳስበዋል።

የህትመት ሥራው በ2017 ዓ.ም ከሚመረቁ ተማሪዎች ጀምሮ የሚፈፀም መሆኑንም ገልፀዋል።

ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot
➡️ https://t.me/atc_news


ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ከሁለት ነጥብ አራት ሚሊየን ብር በላይ የሚያውጣ የላፕቶፕ ኮምፒውተርና የኢንተርኔት መጠቀሚያ ራውተሮችን ድጋፍ አደረገ፡፡

ድርጅቱ ከሁለት ነጥብ አራት ሚሊየን ብር በላይ ግምት ያላቸው 30 ላፕቶፕ ኮምፒውተር፣ 6 የኢንተርኔት መጠቀሚያ ራውተሮችን ከ6 ወር የነጻ ኢንተርኔት ፓኬጅ ጋር በባህር ዳር ከተማ ለሚገኙ ሶስት ትምህርት ቤቶች ድጋፍ አደርጓል፡፡

ድጋፉ የተማሪዎችን የቴክኖክሎጅ ክህሎትና ብቃት ለማሳደግና ከዘመናዊ ዓለም ጋር ተወዳዳሪ እንዲሆኑ ለማስቻል ታሳቢ ያደረገ መሆኑን የሳፋሪኮም የውጭ ግንኙነት ስራ አስፈጻሚ አቶ ጥላሁን ብርሃኑ ገልጸዋል፡፡
በድጋፍ ርክክቡ ወቅት የተገኙት የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ደግሰው መለሰ ድጋፉ ትምህርትን በቴክኖሎጅ ከዘመናዊ ዓለም ጋር አስተሳስሮ ለማስተማር እንደሚግዝ ገልጸዋል፡፡ በተለያዩ ዘርፎች መሪዎችና ተመራማሪዎች የሚፈልቁበትን የትምህርት ተቋማትን መደገፍ ሀገርን መደግፍ መሆኑን የገለጹት አቶ ደግሰው ሳፋሪኮም ላደረገው ደጋፍ አመስግነዋል፡፡

የባህርዳር ከተማ አስተዳደር ትምህርት መምሪያ ኃላፊ ሙሉዓለም አቤ /ዶክተር/ ዓለም አሁን የደረስበት ደረጃ ጋር ተወዳዳሪ መሆን የሚቻለው በቴክኖሎጅ የተደገፈ ትምህርት በማስተማር በመሆኑ ድጋፎችን በአግባቡ ለመማር ማስተማር ስራ መዋል እንደሚገባ አመላክተዋል፡፡

ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot
➡️ https://t.me/atc_news


🌟 Launch Your Tech Career with ALX! 🌍
Applications are NOW OPEN and it takes just 5 minutes to apply!

✅ Why ALX?
- Learn in-demand tech skills
- Join a global community of ambitious learners
- Get career-ready with hands-on projects and mentorship
- Flexible learning to fit your schedule

💻 Popular Programs
Front-End Web Dev: bit.ly/3Z2NS6j
Back-End Web Dev: https://bit.ly/3EXcdm7
AWS Cloud: bit.ly/3UM3ZT4
Salesforce Admin: bit.ly/40DNigr
Data Science: bit.ly/3UMM8eQ
Data Analytics: bit.ly/3Clr20F

👉 Apply NOW and gain full access to all of this for just $5 (650 ETB)!


🔥🔥🔥 ከቤት ሆነው የትም መሄድ ሳይጠበቅቦት የሚሰሩበት እና በዶላር 💵💵💵 ተከፋይ የሚሆኑበት ምርጥ የስራ እድል www.CDIWork.com ይዞሎት መጥቷል።

ይህ ዕድል እንዳያመልጦ፤

💻 💰💵💸 💥

✨ ለበለጠ መረጃ  የማህበራዊ ሚዲያችንን ይቀላቀሉ። ✨
Telegram - https://t.me/CDIWork

ጉዞውን ዛሬ ይጀምሩ።
www.CDIWork.com


የመውጫ ፈተና ወስደው ለወደቁ ተማሪዎች Special Diploma ሊሰጥ ነው።

የመውጫ ፈተና መሰጠት ከተጀመረበት ሐምሌ 2015 ዓ.ም ጀምሮ ፈተናውን ወስደው ማለፍ ላልቻሉ ተፈታኞች Special Diploma ሊሰጥ መሆኑን ቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ ሰምቷል።

ፈተናውን ለወደቁ ዕጩ ተመራቂዎች ልዩ ዲፕሎማ ሰርተፊኬት በቅርቡ መሠጠት እንደሚጀምር የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች ህብረት አረጋግጧል።

ህብረቱ ከትምህርት ሚኒስቴር አመራሮች ጋር ያደረገውን ተከታታይ ውይይት ተከትሎ ውሳኔ ላይ መደረሱን ለቲክቫህ ተናግሯል።

ተማሪዎቹ ሥራ እየሠሩ በማንኛውም ጊዜ የመውጫ ፈተናውን በድጋሜ መውሰድ የሚችሉበት ዕድል ክፍት መሆኑንም ህብረቱ ገልጿል።

ፈተናውን ወስደው የሚያልፉ ተፈታኞች በስፔሻል ዲፕሎማው ምትክ ዲግሪ ይሰጣቸዋል ተብሏል።

የስፔሻል ዲፕሎማ የደመወዝ ስኬል እንዲወጣለት ህብረቱ ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር እየተወያየ ይገኛል።


ምንጭ፡ ቲክቫህ ዩንቨርሲቲ
ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot
➡️ https://t.me/atc_news


ከአዲስ አበባ እስከ ታይዋን የተዘረጋው የሕገ-ወጥ ደላሎች ሥራ አስቸጋሪ እንደሆነበት የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ

የውጭ ጉዳይ መኒስቴር በርካታ ዜጎች በተለይም በማይናማር በስቃይ የሚገኙ ዜጎች ከአዲስ አበባ እስከ ታይዋን በተዘረጋ ሰንሰለት ሰለባ የሆኑ ናቸው ሲል አስታውቋል፡፡

በሚኒቴሩ የቆንስላ ጉዳዮች ዋና ዳይሬክተር አምበሳደር ሲራጅ ረሺድ፤ "በማይናማር በከፍተኛ ሁኔታ ስቃይ ውስጥ የነበሩ ዜጎችን ለማስመለስ ከማይናማር መንግሥት እና ሌሎች አጋሮች ጋር ሥራዎች እየተሰሩ ይገኛሉ" ብለዋል፡፡

በአሁኑ ወቅት ከ80 በላይ ዜጎችን የማስመለስ ሥራ መሰራቱን የሚናገሩት አምባሳደር ሲራጅ፤ በሁሉም አካባቢ ያሉትን ዜጎች የማስመለሱ ሥራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል፡፡

አምባሳደሩም "ሕጋዊ የመኖሪያ ፍቃድ ሳይኖራቸው ዜጎች ወደ ተለያዩ ሀገራት በሕገ-ወጥ-መንንገድ የሚሄዱበት ጉዳይ ሊቆም ይገባል" ሲሉም አሳስበዋ፡፡

ማክሰኞ ዕለት 32 እንዲሁም ረቡዕ 43 ዜጎች ከማይናማር መመለሳቸውን የገለጹት ደግሞ አምባሳደር ነብያት ጌታቸው ሲሆኑ፤ የማሰመለሱ ሥራ ከፍተኛ የሆነ የዜጋ ተኮር ዲፕሎማሲ በኃላ የተሳካ ጉዳይ መሆኑን ለአሐዱ ገልጸዋል፡፡

የማስመለሱ ሥራ ፈተኛ መሆኑን የሚያነሱት አምባሳደር ነብያት፤ "ከማይናማር ወጥተው ታይላንድ የገቡት ዜጎች በራሱ ከታይላንድ ዋና ከተማ ባንኮክ እንኳን 600 ኪሎሜትር ርቀት ላይ በሚገኝ ቦታ ላይ መሆናቸው ችግሩን ከፍተኛ አድርጎታል" ብለዋል፡፡

በማይናማር በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ያሉ ዜጎችን ሙሉ ለሙሉ ለማስወጣት ችግሮች እንዳሉበት የገለጹም ሲሆን፤ ጃፓን በሚገኘውን የኢትዮጵያ ኤምባሲ በኩል ዜጎቹን ወደ ታይላንድ በማሻገር ወደ አገራቸው ለመመለስ ከፍተኛ ጥረት እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡፡

መንግሥት ዜጎችን ከውጭ ሀገራት ከመመለስ በተጨማሪ በሕጋዊ መንገድ እንዲሄዱ ብሎም ሕጋዊ መንገድን ተከትለው እንዲሰሩ ከማድረግ አኳያ ሥራዎች እየተሰሩ መሆኑንም ጨምረው ገልጸዋል፡፡

አስቀድሞ የመከላከል ሥራዎች በተጠናከረ መንገድ እየተሰራ ቢሆንም፤ "በሕገ-ወጥ ደላሎች የተነሳ በርካታ አደጋ እየተጋለጠባቸው ይገኛል" ብለዋል፡፡

"ከአዲስ አበባ እስከ ታይዋን ከዛም አልፎ እስከ ሳኡዲ እና ሌሎች ሀገራት የተዘረጋውን የሕገ-ወጥ ደላሎች ሥራን ለማክሸፍ ከሁሉም ተባባሪ አካላት ጋር በጋራ እየተሰራ ነው" ሲሉም ገልጸዋል፡፡

በተያያዘ የኢትዮጵያ መንግሥት በሦስት ዓመት ውስጥ ብቻ በተለያዩ ችግሮች ውስጥ የነበሩ ከ450 ሺሕ በላይ ዜጎች ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ ማድረጉን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡

በዚህ ዓመትም ወደተለያዩ ሀገራት በሕገ-ወጥ መንገዶች ወጥተው በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የነበሩ፤ 27 ሺሕ ዜጎች ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ ማደረጉንም ገልጿል፡፡

#አሐዱ
ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot
➡️ https://t.me/atc_news


የትምህርት ሚኒስትሩ በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኧርቪን ማሲንጋ ጋር ተወያዩ


የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኧርቪን ማሲንጋ ጋር በትምህርት ዘርፉ በትብብር ሊሰሩ በሚችሉባቸው ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት አድርገዋል።

በዚሁ ጊዜ የትምህርት ሚኒስትሩ የኢትዮጵያ የትምህርት ሥርዓትን ለማስተካከል የቅድሚያ ትኩረት ተሰጥቷቸው እየተሰሩ ያሉ የሪፎርም ሥራዎችን ለአምባሳደሩ አብራርተውላቸዋል፡፡

በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኧርቪን ማሲንጋ በበኩላቸው በኢትዮጵያ የትምህርት ሥርዓቱን ለመቀየር እየተወሰዱ ያሉ ሪፎርሞችና የተያዙ ራዕዮችን እንገነዘባለን ያሉ ሲሆን በቀጣይ የትምህርት ዘርፉን ለመደገፍ እንደሚሰሩ ገልጸዋል፡፡

ሁለቱ አካላት በነበራቸው ውይይቶች ለትምህርት ዘርፉ የሚደረጉ ድጋፎች ለታለመላቸው አላማ ይውሉ ዘንድ ከመተግበራቸው አስቀድሞ መወያየት እንደሚያስፈልግም ተስማምተዋል፡፡


ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot
➡️ https://t.me/atc_news


የዩኒቨርሲቲ ሥራ አመራር ቦርድ አመራሮች የተሰጣቸውን ኃላፊነት በሚገባ እንዲወጡ ተጠየቀ፡፡

የዩኒቨርሲቲ ሥራ አመራር ቦርድ አባላት የምክክር መድረክ እየተካሄድ ይገኛል፡፡
-------------------------------------

በምክክር መድረኩ የተገኙት የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ እየተወሰዱ ባሉ የሪፎርም እርምጃዎች ዩኒቨርሲቲዎች ወደፊት ምን አይነት ደረጃ ላይ መድረስ እንዳለባቸው የሚያመላክቱ በመሆኑ የሥራ አመራር ቦርድ አመራሮች ዩኒቨርሲቲዎችን ለመቀየር እየተሄደበት ያለውን ሁኔታ አውቃችሁ በዛ ልክ ኃላፊነታችሁን ልትወጡ ይገባል ብለዋል፡፡

የከፍተኛ ትምህርት ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር አቶ ኮራ ጡሽኔ በበኩላቸው የዩኒቨርሲቲ ሥራ አመራር ቦርድ አመራሮ ዩኒቨርሲቲዎች ካላቸው ራዕይና ተልዕኮ አንጻር የሰሯቸውን ሥራዎች በየጊዜው እየገመገሙ የተጠያቂነት ሥርዓትን መዘርጋት ይኖርባቸዋል ብለዋል፡፡

ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot
➡️ https://t.me/atc_news


በሶስቱም ቅርንጫፎቻችን ( መገናኛ፣ ሜክሲኮና ጀሞ) እንዲሁም በኦንላይን በምንሰጣቸዉ  ስልጠናዎች በ Advanced level እና 90% practical በሆነ ካሪኩለም እንዲሁም ዘመኑ ያፈራቸዉን ሙሉ የላብራቶሪና የስቱዲዮ እቃዎችን በማሟላት ከሁሉም ስልጠናዎቻችን ላይ ታላቅ የዋጋ ቅናሽ አድርገናል! አሁኑኑ ይመዝገቡና ትልቅ ለዉጥ ወደሚያመጡበት ተቋም ይቀላቀሉ!

ከትምህርትና ስልጠና ጥራትና ቁጥጥር ባለስልጣን ሙሉ ዕዉቅና ካለዉ ሰርተፊኬት ጋር!

እኛጋ ለመሰልጠን ኮምፕዩተር መግዛት አያስፈልግዎትም!

የብዙ አመት ልምድ እና ብቃት ባላቸዉ አሰልጣኞች!

🎯 Graphics Design
🎯 Video Editing
🎯 Digital Marketing
🎯 Photography
🎯 Videography
🎯 Cinematography
🎯 Adobe photoshop
🎯 Fullstack Web app development 
🎯 Programming Language
🎯 Interior Design
🎯 English Language
🎯 Database
🎯 Basic Computer
🎯 Accounting Softwares
🎯 Engineering Softwares
🎯 SPSS & STATA
🎯 MS-Project
🎯  Foreign & Local Languages

አድራሻ:-
1. መገናኛ መተባበር ህንፃ 4ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 419 (ሊፍት ይጠቀሙ)  ☎️ 0991929303

2. ሜክሲኮ ኬኬር ህንፃ 6ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 639 (ሊፍት ይጠቀሙ ሁለተኛዉን ሊፍት) ☎️ 0991929304

 3. ጀሞ 1 አንደኛ በር ካኩ ቢዝነስ ሴንተር 3ኛ ፎቅ ☎️ 0991926707

Join telegram https://t.me/topinstitutes

tiktok https://Tiktok.com/@topinstitute

Facebook https://www.facebook.com/Topinstitutes


🌟 Launch Your Tech Career with ALX! 🌍
Applications are NOW OPEN and it takes just 5 minutes to apply!

✅ Why ALX?
- Learn in-demand tech skills
- Join a global community of ambitious learners
- Get career-ready with hands-on projects and mentorship
- Flexible learning to fit your schedule

💻 Popular Programs
Front-End Web Dev: bit.ly/3Z2NS6j
Back-End Web Dev: https://bit.ly/3EXcdm7
AWS Cloud: bit.ly/3UM3ZT4
Salesforce Admin: bit.ly/40DNigr
Data Science: bit.ly/3UMM8eQ
Data Analytics: bit.ly/3Clr20F

👉 Apply NOW and gain full access to all of this for just $5 (650 ETB)!


🔥🔥🔥 ከቤት ሆነው የትም መሄድ ሳይጠበቅቦት የሚሰሩበት እና በዶላር 💵💵💵 ተከፋይ የሚሆኑበት ምርጥ የስራ እድል www.CDIWork.com ይዞሎት መጥቷል።

ይህ ዕድል እንዳያመልጦ፤

💻 💰💵💸 💥

✨ ለበለጠ መረጃ  የማህበራዊ ሚዲያችንን ይቀላቀሉ። ✨
Telegram - https://t.me/CDIWork

ጉዞውን ዛሬ ይጀምሩ።
www.CDIWork.com


#Update


ላለፉት ደቂቃዎች ተቋርጦ የነበረው የቴሌግራም አገልግሎት ወደነበረበት ተመልሷል።

ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot
➡️ https://t.me/atc_news


ቴሌግራም ተቋርጧል።

የቴሌግራም መተግበሪያ ላለፉት ደቂቃዎች አገልግሎቱ በከፊል እየተቆራረጠ ይገኛል።

፨እስካሁን ባደረግነው ዳሰሳ በዋይፋይ ያለ ቪፒኤን አይሰራም።

ችግሩ እስኪቀረፍ አገልግሎቱን በ
#VPN መጠቀም ይቻላሉ።

ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot
➡️ https://t.me/atc_news


#COC

በዚህ ወር ለሚሰጠው የጤና ባለሙያዎች የብቃት ምዘና ፈተና የተፈታኞች ምዝገባ ከየካቲት 24/2017 ዓ.ም ጀምሮ እየተከናወነ ይገኛል፡፡ ምዝገባው እስከ መጋቢት 7/2017 ዓ.ም ለአመልካቾች ክፍት ሆኖ ይቆያል።

አመልካቾች ምዝገባ ለማድረግ "ቴምፖራሪ ዲግሪ" መያዝ እንደሚጠበቅባቸው ጤና ሚኒስቴር መግለፁ ይታወቃል፡፡

ከዚህ ጋር በተያያዘ ዘንድሮ የተመረቁ እና ቴምፖራሪ ዲግሪ ከተመረቁበት ከፍተኛ ትምህርት ተቋም ያልደረሰላቸው ተመዛኞች መቸገራቸውን የሚገልፁ ቅሬታቸውን ለቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ አድርሰዋል፡፡

በጉዳዩ ዙሪያ ጤና ሚኒስቴርን የጠየቅን ሲሆን፤ ተከታዩን ማብራሪያ አድርሶናል፦
"ጤና ሚኒስቴር የሚሰጠው Licensure Exam ትምህርታቸውን ለጨረሱ እና የሙያ ፈቃድ ለመውሰድ ለተዘጋጁ የጤና ባለሙያዎች የሚሰጥ ፈተና ነው፡፡ ጤና ሚኒስቴር ተመዛኞቹ ትምህታቸውን ማጠናቀቃቸውን የሚያረጋግጠው በሚያቀርቡት የትምህርት ማስረጃ ነው። ይህ አሰራር ላለፉት ስድስት ዓመታት ስንከተለው የቆየነው ነው፡፡ እስካሁን የብቃት ምዘና ፈተና እየሰጠን ያለነው በዚህ አግባብ ነው። በመሆኑም ቴምፖራሪ ዲግሪ መያዝ የግድ ነው፡፡"

ምንጭ፡ ቲክቫህ ዩንቨርስቲ

ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot
➡️ https://t.me/atc_news


የአስገድዶ የመድፈር ጥቃት የፈፀመው መምህር በእስራት ተቀጣ

በምዕራብ ሸዋ ዞን ኤጀሬ ለፎ ወረዳ ኦሎኮሊ 02 ቀበሌ ውስጥ በአስገድዶ መድፈር ወንጀል በተከሰሰው መምህር ላይ የኦሮሚያ ጠቅላይ ፍርድ ቤት የእስር ቅጣት ማስተላለፉ ተገለፀ::

ከምዕራብ ሸዋ ዞን ፓሊስ ዋና መምሪያ የኮሙኒኬሽን ፅህፈት ቤት የተገኘው መረጃ እንደሚያመላክተው ተከሳሽ መዝገቡ አበራ የተባለው መምህር ግንቦት 21 ቀን 2016ዓ.ም በኤጀሬ ለፋ ወረዳ ኦሎንኮሚ 02ቀበሌ ውስጥ በመምህርነት ሙያ እያገለገለ እያለ የአስራ ስድስት ዓመቷ ታዳጊ ላይ የመድፈር ጥቃት ፈፅሟል::

ተከሳሹ መምህር የአስራ ስድስት ዓመቷን ታዳጊ እናት በሰራተኝነት በማስጠጋት እናት እና ልጇን በቤቱ በማስጠጋት እያኖራቸው እያለ ግንቦት 21ቀን 2016 ዓ.ም የመምህሩ ህጋዊ ሚስት የእርግዝና ክትትል ለማድረግ ወደ ሆስፒታል በምትሄድበት ጊዜ ብቻዋን እንዳትሆን የታዳጊዋ እናት አብራት መሄዷ ተገልጿል:: 

ተከሳሹም የታዳጊዋ እናት ከባለቤቱ ጋር ተከትላ መሄዷን እንደ አጋጣሚ በመጠቀም በቤት ውስጥ ብቻዋን በማግኘቱ የመደፈር ጥቃት እንደፈፀመባት  ተረጋግጧል:: የደረሰባትን የአስገድዶ የመደፈር ጥቃት ለወላጅ እናትዋ እና ለመምህሩ ባለቤት ከሆስፒታል ሲመለሱ በማሳወቋ ወዲያውኑ ጉዳዩን ለፖሊስ ጥቆማ በመስጠታቸው በቁጥጥር ስር ውሏል።

ፖሊስም የመደፈር ጥቃት የደረሰባትን ታዳጊ ሆስፒታል በመላክ በማስመርመር እና የምርመራ ውጤቱን በመቀበል የምርመራ መዝገቡን አጠናክሮ ለአቃቢ ህግ ልኳል።አቃቢ ህግ የመሰረተውን ክስ ሲከታተል የነበረው የምዕራብ ሸዋ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት በተከሳሹ ላይ ውሳኔ ያስተላለፈ ሲሆን በውሳኔው ቅር የተሰኘው የተበዳይ ቤተሰብ እና  አቃቤ ህግ ጉዳዩን በይግባኝ ለኦሮሚያ ጠቅላይ ፍርድ ቤት በማቅረባቸው የኦሮሚያ ጠቅላይ ፍርድ ቤት  ሰበር ችሎትም የካቲት 20 ቀን 2017 ዓ.ም በዋለው ችሎት በዞኑ ከፍተኛ ፍርድ ቤት የተሰጠውን ውሳኔ በመሻር በተከሳሹ ላይ በ ዘጠኝ አመት እስራት እንዲቀጣ ውሳኔ አሳልፏል።


ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot
➡️ https://t.me/atc_news


#TVTI #ExitExam

በቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት ዋናው ግቢ የ2017 ዓ.ም ተመራቂ የኤክስቴንሽን (የማታ እና የእረፍት ቀናት) ሰልጣኞች እንዲሁም በድጋሜ የመውጫ ፈተና ለመውሰድ በኦንላይን የተመዘገባችሁ አመልካቾች የመውጫ ፈተና ከመጋቢት 18-21/2017 ዓ.ም ይሰጣል፡፡

ኢንስቲትዩቱ የተፈታኞችን ዝርዝር ያወጣ ሲሆን፤ ማንኛውም አይነት የመረጃ ስህተት እንዲሁም ስማችሁ በዝርዝሩ ውስጥ ያልተካተታችሁ እስከ ሐሙስ መጋቢት 4/2017 ዓ.ም ብቻ በየዲፓርትመንታችሁ ሪፖርት እንድታደርጉ ተቋሙ አሳስቧል፡፡ ክፍያ ያልከፈላችሁ እና የዲፓርትመንት ስህተት ያለባችሁ ተማሪዎች ለፈተናውን መቀመጥ እንደማትችሉ ተገልጿል፡፡

በሳተላይት ትምህርታቹሁን ስትከተታሉ የነበራችሁ ተመራቂ ተማሪዎች ስም ዝርዝራቹሁ በአሰተባባረያቹሁ አማካኝነት መላኩ የተገለፀ ሲሆን፤ የመፈተኛ ጣቢያ በቅርቡ ይገለጻል ተብሏል፡፡ ማንኛውም አይነት ጥያቄ ካላችሁ Block 2 Room 203 በአካል በመገኘት መጠየቅ የምትችሉ መሆኑ ተገልጿል፡፡

ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot
➡️ https://t.me/atc_news


በሶስቱም ቅርንጫፎቻችን ( መገናኛ፣ ሜክሲኮና ጀሞ) እንዲሁም በኦንላይን በምንሰጣቸዉ  ስልጠናዎች በ Advanced level እና 90% practical በሆነ ካሪኩለም እንዲሁም ዘመኑ ያፈራቸዉን ሙሉ የላብራቶሪና የስቱዲዮ እቃዎችን በማሟላት ከሁሉም ስልጠናዎቻችን ላይ ታላቅ የዋጋ ቅናሽ አድርገናል! አሁኑኑ ይመዝገቡና ትልቅ ለዉጥ ወደሚያመጡበት ተቋም ይቀላቀሉ!

ከትምህርትና ስልጠና ጥራትና ቁጥጥር ባለስልጣን ሙሉ ዕዉቅና ካለዉ ሰርተፊኬት ጋር!

እኛጋ ለመሰልጠን ኮምፕዩተር መግዛት አያስፈልግዎትም!

የብዙ አመት ልምድ እና ብቃት ባላቸዉ አሰልጣኞች!

🎯 Graphics Design
🎯 Video Editing
🎯 Digital Marketing
🎯 Photography
🎯 Videography
🎯 Cinematography
🎯 Adobe photoshop
🎯 Fullstack Web app development 
🎯 Programming Language
🎯 Interior Design
🎯 English Language
🎯 Database
🎯 Basic Computer
🎯 Accounting Softwares
🎯 Engineering Softwares
🎯 SPSS & STATA
🎯 MS-Project
🎯  Foreign & Local Languages

አድራሻ:-
1. መገናኛ መተባበር ህንፃ 4ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 419 (ሊፍት ይጠቀሙ)  ☎️ 0991929303

2. ሜክሲኮ ኬኬር ህንፃ 6ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 639 (ሊፍት ይጠቀሙ ሁለተኛዉን ሊፍት) ☎️ 0991929304

 3. ጀሞ 1 አንደኛ በር ካኩ ቢዝነስ ሴንተር 3ኛ ፎቅ ☎️ 0991926707

Join telegram https://t.me/topinstitutes

tiktok https://Tiktok.com/@topinstitute

Facebook https://www.facebook.com/Topinstitutes


#JimmaUniversity

ለተለያዩ የስፔሻሊቲ ፕሮግራሞች በጤና ሚኒስቴር ጅማ ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ ሬዚደንት ሐኪሞች የምዝገባ ጊዜ መጋቢት 8 እና 9/2017 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል፡፡

የምዝገባ ቦታ፦
ጅማ ዩኒቨርሲቲ ዋናው ግቢ

ለምዝገባ የሚያስፈልጉ፦
➫ የመጀመሪያ ዲግሪ ኦፊሽያል ትራንስክሪፕት ለጅማ ዩኒቨርሲቲ ሬጅስትራር ጽ/ቤት በፖ.ሳ.ቁ. 378 ማስላክ
➫ የመጀመሪያ ዲግሪ ዋናውና ሁለት ኮፒ
➫ የስፖንሰርሺፕ ደብዳቤ ከጤና ሚኒስቴር ወይም ከሚሰሩበት ዩኒቨርሲቲ

ለጥቆማ 👉 @atc_newsbot
➡️ https://t.me/atc_news


🌟 Launch Your Tech Career with ALX! 🌍
Applications are NOW OPEN and it takes just 5 minutes to apply!

✅ Why ALX?
- Learn in-demand tech skills
- Join a global community of ambitious learners
- Get career-ready with hands-on projects and mentorship
- Flexible learning to fit your schedule

💻 Popular Programs
Front-End Web Dev: bit.ly/3Z2NS6j
Back-End Web Dev: https://bit.ly/3EXcdm7
AWS Cloud: bit.ly/3UM3ZT4
Salesforce Admin: bit.ly/40DNigr
Data Science: bit.ly/3UMM8eQ
Data Analytics: bit.ly/3Clr20F

👉 Apply NOW and gain full access to all of this for just $5 (650 ETB)!


🔥🔥🔥 ከቤት ሆነው የትም መሄድ ሳይጠበቅቦት የሚሰሩበት እና በዶላር 💵💵💵 ተከፋይ የሚሆኑበት ምርጥ የስራ እድል www.CDIWork.com ይዞሎት መጥቷል።

ይህ ዕድል እንዳያመልጦ፤

💻 💰💵💸 💥

✨ ለበለጠ መረጃ  የማህበራዊ ሚዲያችንን ይቀላቀሉ። ✨
Telegram - https://t.me/CDIWork

ጉዞውን ዛሬ ይጀምሩ።
www.CDIWork.com

20 last posts shown.