በአንድ ዘገባ ያ ልጅ አድጎ ሰባት ልጆችን መውለዱንና ልጆቹ ሁሉ ቁርዓንን የሀፈዙ የሸመዱ እንደነበሩ ተጠቅሷል።
ኡሙ ሱለይምን ረድየላሁ አንሁ የተመለከተ አስደናቂ ታሪክ አለ።አንድ የሆነ ሰው ወደ ነብዩ ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም ይመጣና ድሀ እንደሆነ በመግለፅ ምግብ እንዲሰጡት ይጠይቃቸዋል።ነብዩም ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም ባለቤቶቻቸውን ለእንግዳው የሚሆን ምግብ ካላቸው ይሰጡት ዘንድ ላኩባቸው ሆኖም ግን የሁሉም መልስ እርሶን በሀቅ ላይ በላከው ጌታ ይሁንብን ከውሀ በስተቀር የሚላስ የሚቀመስ ነገር የለም።ከዚያም ነብዩ ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም
ወደ ተከታዮቻቸው ዞረው ይህን እንግዳ የሚያስተናግድልኝ ማነው አላህ ይዘንለትና በማለት በግልፅ ጠየቋቸው።አቡ ጦልሀ አል አንሷሪ ረድየላሁ አንሁ በዚህ ጊዜ ወደ ቤት ይዞት ሄደ ከዚያም ባለቤቱን ኡሙ ሱለይምን ረድየላሁ አንሃ እንግዳችንን የምናስተናግድበት አዳች ነገር ይኖራልን!? በማለት ጠየቃት።ከልጆቻችን ምግብ በስተቀር አንዳች ነገር የለም በማለት መልስ ሰጠችው።እነሱን በሆነ ዘዴ እንዲተኙ አድርጊና ምግቡን አቅርቢ ከዚያም መብራቱን በራሱ ጊዜ የጠፋ እንዲመስል አድርገሽ አጥፊው በማለት አዘዛት። በዚህ አይነት እንግዳው ሰው እነርሱም አብረውት እየተመገቡ እነደሆነ በማሰብ በጨለማ እስኪጠግብ ድረስ ምግቡን ከበላ በኋላ በሰላም ተኝቶ አደረ። እነሱም ልጆቻቸውም ግን ምንም ሳይቀምሱ አነጉ።እንደነጋም አቡ ጦልሀ ረድየላሁ አንሁ ወደ መስጂድ ሲሄድ ነብዩ ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም እንዲህ አሉት:- አላህ ባለፈ ምሽት እንግዳችሁን ለማስተናገድ የፈፀማችሁትን ድርጊት ወዶላችኋል።በማለት አሞካሹት
ኡሙ ሱለይም ረድየላሁ አንሃ እንደ ሌሎቹ ሴቶች ሁሉ በተለያዩ ጦርነቶች ተሳትፋለች በሁነይን ዘመቻ ሙስሊሞችን በማበረታታት የተጠሙትን በማጠጣት እና የቆሰሉትን በመንከባከብ ትልቅ ሚና ተጫውታለች።በዚያ ዘመቻ ኡሙ ሱለይም ረድየላሁ አንሃ ጩቤ ይዛ በመታየቷ አቡ ጦልሀ ረድየላሁ አንሁ ለነብዩ ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም ይህን በማንሳት ስሞታ አቀረበ።
በዚህም ጊዜ እርሷ የአላህ መልክተኛ ሆይ! ይህን የያዝኩት ራሴን ለመከላከል ነው። አንድ አጋሪ ወደ ቢቀርብ ሆዱን እተረትረዋለሁ አለች። ነብዩ ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም ሀሳቧን ደገፉ በዚህ ጊዜም እርሷን በአድናቆት ነበር የሚያዩዋት እቤቷ ሲገቡም እንዲህ ይላሉ ጀነት በገባሁ ጊዜ የሚንኮሻኮሾ ድምፅ ሰማሁ እኔም ማነው በማለት ጠየቅሁ ይች የአነስ ኢብን ማሊክ እናት ሩመይሳ ቢንት ሚልሀን ናት ተባልኩኝ በማለት በጀነት ያበስሯት ነበር። ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል
የእኛን እናት ድንቅ ተምሳሌት ኡሙ ሱለይም አላህ ይዘንላት
ኡሙ ሱለይምን ረድየላሁ አንሁ የተመለከተ አስደናቂ ታሪክ አለ።አንድ የሆነ ሰው ወደ ነብዩ ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም ይመጣና ድሀ እንደሆነ በመግለፅ ምግብ እንዲሰጡት ይጠይቃቸዋል።ነብዩም ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም ባለቤቶቻቸውን ለእንግዳው የሚሆን ምግብ ካላቸው ይሰጡት ዘንድ ላኩባቸው ሆኖም ግን የሁሉም መልስ እርሶን በሀቅ ላይ በላከው ጌታ ይሁንብን ከውሀ በስተቀር የሚላስ የሚቀመስ ነገር የለም።ከዚያም ነብዩ ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም
ወደ ተከታዮቻቸው ዞረው ይህን እንግዳ የሚያስተናግድልኝ ማነው አላህ ይዘንለትና በማለት በግልፅ ጠየቋቸው።አቡ ጦልሀ አል አንሷሪ ረድየላሁ አንሁ በዚህ ጊዜ ወደ ቤት ይዞት ሄደ ከዚያም ባለቤቱን ኡሙ ሱለይምን ረድየላሁ አንሃ እንግዳችንን የምናስተናግድበት አዳች ነገር ይኖራልን!? በማለት ጠየቃት።ከልጆቻችን ምግብ በስተቀር አንዳች ነገር የለም በማለት መልስ ሰጠችው።እነሱን በሆነ ዘዴ እንዲተኙ አድርጊና ምግቡን አቅርቢ ከዚያም መብራቱን በራሱ ጊዜ የጠፋ እንዲመስል አድርገሽ አጥፊው በማለት አዘዛት። በዚህ አይነት እንግዳው ሰው እነርሱም አብረውት እየተመገቡ እነደሆነ በማሰብ በጨለማ እስኪጠግብ ድረስ ምግቡን ከበላ በኋላ በሰላም ተኝቶ አደረ። እነሱም ልጆቻቸውም ግን ምንም ሳይቀምሱ አነጉ።እንደነጋም አቡ ጦልሀ ረድየላሁ አንሁ ወደ መስጂድ ሲሄድ ነብዩ ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም እንዲህ አሉት:- አላህ ባለፈ ምሽት እንግዳችሁን ለማስተናገድ የፈፀማችሁትን ድርጊት ወዶላችኋል።በማለት አሞካሹት
ኡሙ ሱለይም ረድየላሁ አንሃ እንደ ሌሎቹ ሴቶች ሁሉ በተለያዩ ጦርነቶች ተሳትፋለች በሁነይን ዘመቻ ሙስሊሞችን በማበረታታት የተጠሙትን በማጠጣት እና የቆሰሉትን በመንከባከብ ትልቅ ሚና ተጫውታለች።በዚያ ዘመቻ ኡሙ ሱለይም ረድየላሁ አንሃ ጩቤ ይዛ በመታየቷ አቡ ጦልሀ ረድየላሁ አንሁ ለነብዩ ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም ይህን በማንሳት ስሞታ አቀረበ።
በዚህም ጊዜ እርሷ የአላህ መልክተኛ ሆይ! ይህን የያዝኩት ራሴን ለመከላከል ነው። አንድ አጋሪ ወደ ቢቀርብ ሆዱን እተረትረዋለሁ አለች። ነብዩ ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም ሀሳቧን ደገፉ በዚህ ጊዜም እርሷን በአድናቆት ነበር የሚያዩዋት እቤቷ ሲገቡም እንዲህ ይላሉ ጀነት በገባሁ ጊዜ የሚንኮሻኮሾ ድምፅ ሰማሁ እኔም ማነው በማለት ጠየቅሁ ይች የአነስ ኢብን ማሊክ እናት ሩመይሳ ቢንት ሚልሀን ናት ተባልኩኝ በማለት በጀነት ያበስሯት ነበር። ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል
የእኛን እናት ድንቅ ተምሳሌት ኡሙ ሱለይም አላህ ይዘንላት