የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የወልቂጤ ከተማ እግር ኳስ ክለብ ክሊፍተን ሜይሶ አይሲ የተባለ ተጫዋችን በተመለከተ የተላለፈበትን ውሳኔ ተፈጻሚ ባለማድረጉ ቅጣት አስተላልፎበታል።
ክለቡ ውሳኔውን ተግባራዊ እንዲያደርግ በተደጋጋሚ ቢገለፅም ተግባራዊ አለማድረጉን ተከትሎ የፊፋ የህግ ፖርታል የነጥብ ቅነሳ እንዲደረግበት ለኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ትዕዛዝ አስተላለፏል።
በዚህም መሰረት ወልቂጤ ከተማ እየተወዳደረበት በሚገኘው የኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ ከሰበሰበው ነጥብ ላይ የስድስት (6) ነጥብ ቅነሳ ውሳኔ ተላልፎበታል።
በያዝነው አመት ከፋይናንስ ደንብ ጥሰት ጋር በተያያዝ ከፕሪሚየር ሊግ ወደ ከፍተኛ ሊግ ውድድር የወረደው ክለቡም ሁለተኛ ቅጣቱን በያዝነው አመት ለማስተናገድ ተገዷል።
በከፍተኛ ሊጉ በምድብ ሀ እየተወዳደረ የሚገኘው ወልቂጤ ከተማ በሊጉ በ15 ነጥብ ዘጠነኛ ደረጃ ላይ ተቀምጦ ነበር።
የነጥብ ቅነሳውን ተከትሎም ክትፎዎቹ አሁን ላይ በውድድሩ 9 ነጥብ ይዘው 11ኛ ደረጃ ላይ ለመቀመጥ ተገደዋል።
#EBS
#EBSTVNEWS
#EBSTVSPORT
#_7696_WN
https://t.me/ebstvnews
ክለቡ ውሳኔውን ተግባራዊ እንዲያደርግ በተደጋጋሚ ቢገለፅም ተግባራዊ አለማድረጉን ተከትሎ የፊፋ የህግ ፖርታል የነጥብ ቅነሳ እንዲደረግበት ለኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ትዕዛዝ አስተላለፏል።
በዚህም መሰረት ወልቂጤ ከተማ እየተወዳደረበት በሚገኘው የኢትዮጵያ ከፍተኛ ሊግ ከሰበሰበው ነጥብ ላይ የስድስት (6) ነጥብ ቅነሳ ውሳኔ ተላልፎበታል።
በያዝነው አመት ከፋይናንስ ደንብ ጥሰት ጋር በተያያዝ ከፕሪሚየር ሊግ ወደ ከፍተኛ ሊግ ውድድር የወረደው ክለቡም ሁለተኛ ቅጣቱን በያዝነው አመት ለማስተናገድ ተገዷል።
በከፍተኛ ሊጉ በምድብ ሀ እየተወዳደረ የሚገኘው ወልቂጤ ከተማ በሊጉ በ15 ነጥብ ዘጠነኛ ደረጃ ላይ ተቀምጦ ነበር።
የነጥብ ቅነሳውን ተከትሎም ክትፎዎቹ አሁን ላይ በውድድሩ 9 ነጥብ ይዘው 11ኛ ደረጃ ላይ ለመቀመጥ ተገደዋል።
#EBS
#EBSTVNEWS
#EBSTVSPORT
#_7696_WN
https://t.me/ebstvnews