የትምህርት ሚኒስትሩ በነገሶ ጊዳዳ ልዩ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተገኝተው ተማሪዎችን አበረታቱ።
--------------------------------------------------------
የትምህርት ሚኒሰቴርና የኦሮሚያ ክልል ትምህርት ቢሮ አመራሮች በኦሮሚያ ክልል ቄለም ወለጋ ዞን ደምቢዶሎ ከተማ የሚገኘውን የነጋሶ ጊዳዳ ልዩ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤትን በመጎብኘት ተማሪዎችን አበረታተዋል።
በዚሁ ጊዜ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ተማሪዎች ኩረጃና ስርቆት የሚጠየፉ፣ በራሳቸው የሚሰሩና ጊዜያቸውን በአግባቡ የሚጠቀሙ ጠንካራ ተማሪዎች እንዲሆኑ አሳስበዋል።
ትምህርት ሰውን ሰው ያደረገ ነው ያሉት ሚኒስትሩ ተማሪዎች ወደፊት የሚገጥማችሁ አለም ትልቅ እውቀት የሚፈልግ መሆኑን አውቃችሁ ለዛ መዘጋጀት ይጠበቅባችኃል ብለዋል።
እንደ ሀገር ሁሉም የኢትዮጵያ ልጆች ጥራት ያለው ትምህርት እንዲማሩ ሀገራቸውን ከሌላው አለም ማወዳደር የሚችሉ ብቃት ያላቸው ተማሪዎችን ለማፍራት በትምህርት ሚኒስቴር ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች እየተገነቡ እንደሚገኝም አንስተዋል።
ተማሪዎች ጠንክረው በመማር ወደፊት ሀገራቸው ራሷን የቻለች፤ ለሌላ ሀገር የምትተርፍ እንድትሆን እንደሚያደርጓት እምነት እንዳላቸው በመግለፅ ይህን እንዲወጡ አደራ በማለት መልዕክታቸው አስተላልፈዋል። ሙሉ መረጃውን ይህንን ሊንክ በመጫን ማግኘት ይችላሉ፤
https://www.facebook.com/share/p/163sKpcEtq/
--------------------------------------------------------
የትምህርት ሚኒሰቴርና የኦሮሚያ ክልል ትምህርት ቢሮ አመራሮች በኦሮሚያ ክልል ቄለም ወለጋ ዞን ደምቢዶሎ ከተማ የሚገኘውን የነጋሶ ጊዳዳ ልዩ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤትን በመጎብኘት ተማሪዎችን አበረታተዋል።
በዚሁ ጊዜ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ተማሪዎች ኩረጃና ስርቆት የሚጠየፉ፣ በራሳቸው የሚሰሩና ጊዜያቸውን በአግባቡ የሚጠቀሙ ጠንካራ ተማሪዎች እንዲሆኑ አሳስበዋል።
ትምህርት ሰውን ሰው ያደረገ ነው ያሉት ሚኒስትሩ ተማሪዎች ወደፊት የሚገጥማችሁ አለም ትልቅ እውቀት የሚፈልግ መሆኑን አውቃችሁ ለዛ መዘጋጀት ይጠበቅባችኃል ብለዋል።
እንደ ሀገር ሁሉም የኢትዮጵያ ልጆች ጥራት ያለው ትምህርት እንዲማሩ ሀገራቸውን ከሌላው አለም ማወዳደር የሚችሉ ብቃት ያላቸው ተማሪዎችን ለማፍራት በትምህርት ሚኒስቴር ልዩ አዳሪ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች እየተገነቡ እንደሚገኝም አንስተዋል።
ተማሪዎች ጠንክረው በመማር ወደፊት ሀገራቸው ራሷን የቻለች፤ ለሌላ ሀገር የምትተርፍ እንድትሆን እንደሚያደርጓት እምነት እንዳላቸው በመግለፅ ይህን እንዲወጡ አደራ በማለት መልዕክታቸው አስተላልፈዋል። ሙሉ መረጃውን ይህንን ሊንክ በመጫን ማግኘት ይችላሉ፤
https://www.facebook.com/share/p/163sKpcEtq/