የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት " በህገ-ወጥ መንገድ ቆጣሪን እንዳይቆጥር በማድረግ ሃይል ሲጠቀሙ እንደነበር ደርሼበታለሁ " በማለት ሃይል ካቋረጠባቸው አራት ብሎኮች ውስጥ ሁለቱ ማለትም ብሎክ 550 እና 551 ሃይል ተቀጥሎላቸው አገልግሎት እያገኙ ነበር።
የእነዚህ ቆጣሪዎች እዳ ባልተከፈለበት እና ከሌሎች ብሎኮች ጋር በጋራ ሃይል በተቋረጠበት ሁኔታ ለእነርሱ በማን እና በምን ሁኔታ ተቀጠለ ? የሚል ጥያቄ ለሪጅኑ ዳይሬክተር አቶ ብርሃኑ ኦልጅራ ጥያቄ ቀርቦላቸው ነበር።
ዳይሬክተሩም ፤ የቆጣሪዎቹ እዳ ባልተከፈለበት ሁኔታ የእነሱ ሃይል መጠቀም ከእርሳቸው እውቅና ውጪ መሆኑን ገልጸዋል።
ከተቋረጠ በኃላ በራሳቸው ሃይሉን ቀጥለው ይጠቀሙ ወይስ የአገልግሎቱ ሰው ቀጠለላቸው የሚለውን ጉዳይ ማጣራት በማድረግ " አስፈላጊውን ህጋዊ እርምጃ እንወስዳለን " ብለዋል።
በመቀጠለም ምልከታ የተደረገው ብሎክ 534 እና 535 ላይ ሲሆን እነዚህ ብሎኮች " ሃይል በህገ ወጥ መንገድ ቀጥለው ሲጠቀሙ በኢንስፔክሽን ወቅት ተገኝተዋል " በሚል ሃይል ከተቋረጠባቸው ወር እንዳለፋቸው ተናግረዋል።
አገልግሎት በበኩሉ " ሃይሉን ያቋረጥኩት ከጋራ መኖሪያ መንደሩ ነዋሪዎች ለአንድ ዓመት ከአራት ወር በላይ ቀጥዬ ተጠቅሚያለው ያሉ እና የሚጠቀምም ስለመኖሩ በደረሰኝ ጥቆማ መሰረት ነው " ብሏል።
ነዋሪዎች ከእነዚህ ቆጣሪዎች ሃይል ቀጥለው አለመጠቀማቸውን ተከራክረዋል።
የኤሌክትሪክ አገልግሎት ባለሞያዎች ግን የቆጣሪውን ሃይል ባቋረጡበት ወቅት እነዚህ ብሎኮች መጨለማቸውን እንደማስረጃ በመጥቀስ ሃይል በህገወጥ መንገድ እየተጠቀሙ ስለመሆኑ አመላካች ነው ብለዋል።
" ሃይል የተቋረጠብን ለብሎካችን የገባው ስሪ ፌዝ ቆጣሪ በመቆረጡ እንጂ ከተጠቀሰው ቆጣሪ ላይ ሃይል አልቀጠልንም " ሲሉ የተከራከሩት ነዋሪዎች " ቆጣሪው መንገድ ላይ ያለ በመሆኑ ማንም ሰው እየቀጠለ ይጠቀማል ሌሎች በተጠቀሙት እኛ ልንጠየቅ አይገባም " ሲሉ መልሰዋል።
የእነዚህ ቆጣሪዎች እዳ ባልተከፈለበት እና ከሌሎች ብሎኮች ጋር በጋራ ሃይል በተቋረጠበት ሁኔታ ለእነርሱ በማን እና በምን ሁኔታ ተቀጠለ ? የሚል ጥያቄ ለሪጅኑ ዳይሬክተር አቶ ብርሃኑ ኦልጅራ ጥያቄ ቀርቦላቸው ነበር።
ዳይሬክተሩም ፤ የቆጣሪዎቹ እዳ ባልተከፈለበት ሁኔታ የእነሱ ሃይል መጠቀም ከእርሳቸው እውቅና ውጪ መሆኑን ገልጸዋል።
ከተቋረጠ በኃላ በራሳቸው ሃይሉን ቀጥለው ይጠቀሙ ወይስ የአገልግሎቱ ሰው ቀጠለላቸው የሚለውን ጉዳይ ማጣራት በማድረግ " አስፈላጊውን ህጋዊ እርምጃ እንወስዳለን " ብለዋል።
በመቀጠለም ምልከታ የተደረገው ብሎክ 534 እና 535 ላይ ሲሆን እነዚህ ብሎኮች " ሃይል በህገ ወጥ መንገድ ቀጥለው ሲጠቀሙ በኢንስፔክሽን ወቅት ተገኝተዋል " በሚል ሃይል ከተቋረጠባቸው ወር እንዳለፋቸው ተናግረዋል።
አገልግሎት በበኩሉ " ሃይሉን ያቋረጥኩት ከጋራ መኖሪያ መንደሩ ነዋሪዎች ለአንድ ዓመት ከአራት ወር በላይ ቀጥዬ ተጠቅሚያለው ያሉ እና የሚጠቀምም ስለመኖሩ በደረሰኝ ጥቆማ መሰረት ነው " ብሏል።
ነዋሪዎች ከእነዚህ ቆጣሪዎች ሃይል ቀጥለው አለመጠቀማቸውን ተከራክረዋል።
የኤሌክትሪክ አገልግሎት ባለሞያዎች ግን የቆጣሪውን ሃይል ባቋረጡበት ወቅት እነዚህ ብሎኮች መጨለማቸውን እንደማስረጃ በመጥቀስ ሃይል በህገወጥ መንገድ እየተጠቀሙ ስለመሆኑ አመላካች ነው ብለዋል።
" ሃይል የተቋረጠብን ለብሎካችን የገባው ስሪ ፌዝ ቆጣሪ በመቆረጡ እንጂ ከተጠቀሰው ቆጣሪ ላይ ሃይል አልቀጠልንም " ሲሉ የተከራከሩት ነዋሪዎች " ቆጣሪው መንገድ ላይ ያለ በመሆኑ ማንም ሰው እየቀጠለ ይጠቀማል ሌሎች በተጠቀሙት እኛ ልንጠየቅ አይገባም " ሲሉ መልሰዋል።