"የጌታ ልደት በቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ"
ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ የከበረ የክርስቶስን ልደት ነገር በተናገረበት አንቀፅ እንዲህ አለ ቀዳማዊ አምላክ ዛሬ ተወለደ ፤ ጥንቱን ገንዘቡ ባይደለ ባህርይ ተገኝ ፤ እርሱ ቀዳማዊ አምላክ ነው ፤ ሰው በመሆኑም ከባህርይው አልተለወጠም፡፡ የመለኮቱ መገኝትም ከእመቤታችን ከተወለደ ወዲህ አይደለም ፤ ከአብ ከመንፈስ ቅዱስ ጋር ዓለም ሳይፈጠር የነበረ ጥበብ ነውንጂ ፤ የማይታመም እርሱ ከባህርይ መለኮቱ ሳይለወጥ ሕማም የሚስማማውን ስጋን ተዋሃደ፡፡ ዳግመኛም በልዑል ዙፋን ላይ ተቀምጦ ያለ እርሱ በበረት ተጣለ ስጋ ሳይሆን የነበረ የማይዳሰስ ወልድ ዋህድ ዛሬ ስጋን በመዋሃድ ተዳሰሰ ፤ ሃጢአትን የሚያስተሰርይ እርሱ በጨርቅ ተጠቀለለ፡፡
መፅሃፍ እንዲህ አለ ፦ ብልህ ሽክላ ሰሪ የሚሰራውን የለዘበ ጭቃ በአገኝ ጊዜ ከእርሱ መልካም እቃ እንዲሰራ እንደዚሁ ጌታችን የዚህችን ድንግል ንፁህ ስጋዋን ንፅህት ነፍሷን ባገኘ ጊዜ ነፍስ ያለችውን ስጋ ሊዋሃደው ፈጠረ፡፡ እንደወደደ ከድንግል ነፍስን ስጋን ፈጥሮ ለበሰ እርሱንም ተዋህዶ ዛሬ ተወለደ ሕፀፅ ያለበት ነው ብሎ ባህርያችንን አልተወውም ፤ ስጋን በተዋህዶ ጊዜ ቃል ከምላቱ አልተወሰነም ፤ ስጋ የፈጣሪ አካል ባህርይ በሆነ ጊዜ ፍፁም አምላክነትን አገኝ እንጂ፡፡ ምን እላለሁ? ምንስ እናገራለሁ? ከዘመን አስቀድሞ የነበረ እርሱ ትንሽ ህፃን ሆኗልና፡፡
እኔ ፈፅሜ አደንቃለሁ ፤ ከሰማየ ሰማያት በላይ የሚሆን ፡ በዘላለማዊ ዙፋን የሚኖር እርሱ በበረት ተጣለ ፡ ከስጋዌ አስቀድሞ አይዳሰስ የነበረ አንዱ እርሱ በምድራውያን እጅ ተዳሰሰ ፡ ሃጢአትን የሚያስተሰርይ እርሱን በጨርቅ ጠቀለሉት ፤ ይህን ወዷልና፡፡ ክብሩ ተለይቶት የነበረ ስጋን ክቡር አምላክ ሊያደርገው ፤ የፀጋ ገዥነትን አጥቶ የነበረ ስጋንም የባህርይ ገዥ ሊያደርገው ወደደ ፤ አዳም ከእኛ እንዳንዱ ሆነ ያለውንም ሰው በመሆን ሊገልጠው ወደደ፡፡ ስለዚህ ስጋየን ተዋሃደ ፡ ወንጌልን ሲያስተምር እሰማው ዘንድ ስጋየን በተዋህዶ ገንዘብ አደረገ ፤ መንፈስ ቅዱስን ሰጠኝ ፡ ተቀበልኩ ፡ ለእኔም ፍፁም ህይወትን ገንዘብ አደረግሁ ፡ እርሱ ያከብረው ዘንድ ስጋየን ተዋሃደው ፡ የሚያድነኝ መንፈስ ቅዱስን ሰጠኝ፡፡ በቅዳሴውም እንዲህ አለ፡- ዳግመኛም የወልድ አነዋወሩ እንደምን እንደሆነ መውረዱም እንዴት እንደሆነ እንናገራለን፡፡ ከአባቱ ሳይወጣ መጣ ከአነዋወሩ ሳይለይ ወረደ ከሶስትነቱ ሳይለይ መጣ ከአንድነቱም ሳይለይ ወረደ ከዙፋኑም ሳይለይ በስጋ ልጅ አደረ ከምላቱ ሳይወሰን በማህጸን ተጸነሰ በላይ ሳይጐድል በማህፀን ተወሰነ በታችም ሳይጨመርበት ተወለደ ከኃጢአት በቀር ፈፅሞ ሰው ሆነ እንደ እግዚአብሔር እየሰራ እንደ ባርያ ታየ፡፡ ዳግመኛም እንዲህ አለ ፍቅር ሰሃቦ ለወልድ ኃያል እም መንበሩ ወአብጽሖ እስከለሞት /ፍቅር ኃያል ወልድን ከዙፋኑ አወረደው እስከ ሞትም አደረሰው።/
እንግዲህ እኛ ግን ከጨለማ ወደሚደነቅ ብርሃኑ የጠራን የእርሱን በጎነት እንድንነግር የተመረጥን ቅዱስ ሕዝብ ለርስቱ የተለየን ወገን መሆናችን አውቀን በብርሃን እንኑር ጨለማውም ያልፋልና እውነተኛውም ብርሃን ይበራል በቀን እንደሚሆን በጽድቅና በቅንነት ሆነን (1ጴጥ 2፡9 ፣ 1ዮሐ 2፡8) የጌታችንን የመድኃኒታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ልደት እናክብር።
🇪🇹@ethiopianorthodoxs⛪️⛪️
ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ የከበረ የክርስቶስን ልደት ነገር በተናገረበት አንቀፅ እንዲህ አለ ቀዳማዊ አምላክ ዛሬ ተወለደ ፤ ጥንቱን ገንዘቡ ባይደለ ባህርይ ተገኝ ፤ እርሱ ቀዳማዊ አምላክ ነው ፤ ሰው በመሆኑም ከባህርይው አልተለወጠም፡፡ የመለኮቱ መገኝትም ከእመቤታችን ከተወለደ ወዲህ አይደለም ፤ ከአብ ከመንፈስ ቅዱስ ጋር ዓለም ሳይፈጠር የነበረ ጥበብ ነውንጂ ፤ የማይታመም እርሱ ከባህርይ መለኮቱ ሳይለወጥ ሕማም የሚስማማውን ስጋን ተዋሃደ፡፡ ዳግመኛም በልዑል ዙፋን ላይ ተቀምጦ ያለ እርሱ በበረት ተጣለ ስጋ ሳይሆን የነበረ የማይዳሰስ ወልድ ዋህድ ዛሬ ስጋን በመዋሃድ ተዳሰሰ ፤ ሃጢአትን የሚያስተሰርይ እርሱ በጨርቅ ተጠቀለለ፡፡
መፅሃፍ እንዲህ አለ ፦ ብልህ ሽክላ ሰሪ የሚሰራውን የለዘበ ጭቃ በአገኝ ጊዜ ከእርሱ መልካም እቃ እንዲሰራ እንደዚሁ ጌታችን የዚህችን ድንግል ንፁህ ስጋዋን ንፅህት ነፍሷን ባገኘ ጊዜ ነፍስ ያለችውን ስጋ ሊዋሃደው ፈጠረ፡፡ እንደወደደ ከድንግል ነፍስን ስጋን ፈጥሮ ለበሰ እርሱንም ተዋህዶ ዛሬ ተወለደ ሕፀፅ ያለበት ነው ብሎ ባህርያችንን አልተወውም ፤ ስጋን በተዋህዶ ጊዜ ቃል ከምላቱ አልተወሰነም ፤ ስጋ የፈጣሪ አካል ባህርይ በሆነ ጊዜ ፍፁም አምላክነትን አገኝ እንጂ፡፡ ምን እላለሁ? ምንስ እናገራለሁ? ከዘመን አስቀድሞ የነበረ እርሱ ትንሽ ህፃን ሆኗልና፡፡
እኔ ፈፅሜ አደንቃለሁ ፤ ከሰማየ ሰማያት በላይ የሚሆን ፡ በዘላለማዊ ዙፋን የሚኖር እርሱ በበረት ተጣለ ፡ ከስጋዌ አስቀድሞ አይዳሰስ የነበረ አንዱ እርሱ በምድራውያን እጅ ተዳሰሰ ፡ ሃጢአትን የሚያስተሰርይ እርሱን በጨርቅ ጠቀለሉት ፤ ይህን ወዷልና፡፡ ክብሩ ተለይቶት የነበረ ስጋን ክቡር አምላክ ሊያደርገው ፤ የፀጋ ገዥነትን አጥቶ የነበረ ስጋንም የባህርይ ገዥ ሊያደርገው ወደደ ፤ አዳም ከእኛ እንዳንዱ ሆነ ያለውንም ሰው በመሆን ሊገልጠው ወደደ፡፡ ስለዚህ ስጋየን ተዋሃደ ፡ ወንጌልን ሲያስተምር እሰማው ዘንድ ስጋየን በተዋህዶ ገንዘብ አደረገ ፤ መንፈስ ቅዱስን ሰጠኝ ፡ ተቀበልኩ ፡ ለእኔም ፍፁም ህይወትን ገንዘብ አደረግሁ ፡ እርሱ ያከብረው ዘንድ ስጋየን ተዋሃደው ፡ የሚያድነኝ መንፈስ ቅዱስን ሰጠኝ፡፡ በቅዳሴውም እንዲህ አለ፡- ዳግመኛም የወልድ አነዋወሩ እንደምን እንደሆነ መውረዱም እንዴት እንደሆነ እንናገራለን፡፡ ከአባቱ ሳይወጣ መጣ ከአነዋወሩ ሳይለይ ወረደ ከሶስትነቱ ሳይለይ መጣ ከአንድነቱም ሳይለይ ወረደ ከዙፋኑም ሳይለይ በስጋ ልጅ አደረ ከምላቱ ሳይወሰን በማህጸን ተጸነሰ በላይ ሳይጐድል በማህፀን ተወሰነ በታችም ሳይጨመርበት ተወለደ ከኃጢአት በቀር ፈፅሞ ሰው ሆነ እንደ እግዚአብሔር እየሰራ እንደ ባርያ ታየ፡፡ ዳግመኛም እንዲህ አለ ፍቅር ሰሃቦ ለወልድ ኃያል እም መንበሩ ወአብጽሖ እስከለሞት /ፍቅር ኃያል ወልድን ከዙፋኑ አወረደው እስከ ሞትም አደረሰው።/
እንግዲህ እኛ ግን ከጨለማ ወደሚደነቅ ብርሃኑ የጠራን የእርሱን በጎነት እንድንነግር የተመረጥን ቅዱስ ሕዝብ ለርስቱ የተለየን ወገን መሆናችን አውቀን በብርሃን እንኑር ጨለማውም ያልፋልና እውነተኛውም ብርሃን ይበራል በቀን እንደሚሆን በጽድቅና በቅንነት ሆነን (1ጴጥ 2፡9 ፣ 1ዮሐ 2፡8) የጌታችንን የመድኃኒታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ልደት እናክብር።
🇪🇹@ethiopianorthodoxs⛪️⛪️