Ethiopian Orthodoxs Daily


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic
Category: not specified


በቤተ ክርስቲያናችን በየቀኑ የሚታሰብ ቅዱሳን፤ የመፅሐፍ ቅዱስ ምንባባት ፤ ብሂለ አበው እና አስተማሪ የሆኑ መንፈሳዊ ፅሁፎች ያገኙበታል::Share https://t.me/ethiopianorthodoxs //like page on facebook fb.me/ethiopianorthodxs ለሀሳብ አስተያየትዎ
@Yakob520

Related channels  |  Similar channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Category
not specified
Statistics
Posts filter




++ አበው ስለ እመቤታችን ዕረፍት እንዲህ አሉ ++

‹ሌሎች በድንግልና የኖሩ ሴቶች 'ለሞት የሚሆኑ ልጆችን አንሰጥህም" በማለት ሞትን ተቃወሙት፡፡ ድንግል ማርያም ግን አንድ ልጅ በመውለድ በልጅዋ ሞት ራሱ እንዲሞት አደረገችው፡፡ ከዐለት ጋር እንደተጋጨ የተፈረካከሰው በማሕፀንዋ ፍሬ ነውና ሞት ወደ እርስዋ ሲቀርብ ተብረከረከ›› ቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘኑሲስ

‹‹ልጃቸው ተሰብስበው ወዳሉበት መጥታለችና አዳምና ሔዋን ዛሬ ደስ አላቸው … በዚህች ቀን ታላቁ ዳዊት በራሱ ላይ የተዋበ አክሊል የደፋችለትን ሴት ልጁን አይቶ ደስ አለው … በዚህች ቀን ነቢዩ ኢሳይያስ ትንቢት የተናገረላት ድንግል ወደ ሙታን ሥፍራ ልትጎበኘው መጥታለችና ደስ አለው … በዚህች ቀን ብርሃን ሲበራባቸው አይተዋልና ነቢያት ሁሉ ከመቃብራቸው ራሳቸውን ቀና አደረጉ … አርያም በጣፋጭ የመላእክት ዝማሬ ተሞላ ፣ ምድር ደግሞ ኀዘንን በተሞሉ በሐዋርያት ለቅሶ ተሞላች፡፡ ሙታንም ሕያዋንም ትርጉሙን ሊገልጹት በማይችሉት [የተለያየ] ዜማ ሰውና መላእክት በዚያች ዕለት አብረው ጮኹ›› ቅዱስ ያዕቆብ ዘሥሩግ (Homily on the Dormition)

‹‹የቃሉ አገልጋዮችና ምስክሮች የነበሩት ሐዋርያት በሥጋ የወለደችውን የእናቱን ዕረፍትና እርስዋን የሚመለከቱ የመጨረሻዎቹን ምሥጢራትም ማየት ነበረባቸው፡፡ ይህም የሆነው የክርስቶስ የዕርገቱ የዓይን ምስክሮች እንደሆኑ ሁሉ የወለደችውም እናቱ ወደዚያኛው ዓለም ለመሸጋገርዋ ምስክሮች መሆን ስላለባቸው ነው›› ቅዱስ ዮሐንስ ዘደማስቆ  (aka Doctor of Dormition)

ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
አስተ ርእዮ ማርያም


Forward from: ቤተ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
“ማግባት ለሚሹ”
የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ምክር

ከምንም በፊት የጋብቻ ዓላማን ማወቅ አለባችሁ፡፡ በሕይወታችን ለምን ጋብቻ እንደሚያስፈልገን መረዳት አለባችሁ፡፡ ከዚህ ውጪ ሌላ ነገርን አትጠይቁ፡፡ እናስ የጋብቻ ዓላማው ምንድነው? ለምንድነው እግዚአብሔር ጋብቻን የሰጠን? ብጹዕ ጳውሎስን እናድምጠው፤ እንዲህ ያለውን፦ "ስለ ዝሙት ጠንቅ ለእያንዳንዱ ለራሱ ሚስት ትኑሮው፤ ለእያንዳንዲቱ ደግሞ ለራሷ ባል ይኑራት" (1ኛ ቆሮ.7፥2)። "ከድህነት ይወጣ (ትወጣ) ዘንድ" ነው የሚለውን? ወይስ "ሀብት ለማግኘት ሲባል" ነው የሚለውን? አይደለም፡፡ ታዲያ ምንድነው የሚለው? ከዝሙት እንጠበቅ ዘንድ፤ ራሳችንን መቆጣጠር እንችል ዘንድ፤ ንጽህናን ገንዘብ እናደርግ ዘንድ፤ በትዳር አጋራችን ደስ ተሰኝተን እግዚአብሔርን እናመሰግን ዘንድ፡፡ አያችሁ ይኼ ነው የጋብቻ ስጦታው ይኼ ነው የጋብቻ ፍሬው፤ ይኼ ነው የጋብቻ ጥቅሙ፡፡

ስለዚህ ልጆቼ! እማልዳችኋለሁ ትልቁን ጥቅም ዘንግታችሁት ዓይናችሁን በትንሹ ላይ አታሳርፉ፡፡ የትዳር አጋርን ስትመርጡ የሀብት ጉዳይ የእናንተ ትልቅ አጀንዳ ሊኾን አይገባም፡፡ ስለ ሀብት ብሎ የትዳር አጋርን መምረጥ ድንቁርና ነው፤ ሀብት ነገ ሊጠፋ ይችላልና፡፡ ስለዚህ ለትዳር የምትመርጡት ሰው ከምንም በላይ መንፈሳዊ ሀብቱን ተመልከቱ፡፡ በዚህም ዓለም በወዲያኛውም ዓለም ይበልጥ የሚጠቅማችሁ ይኼ ነውና፡፡

አባቶች ሆይ! አብርሃምን ምሰሉት፡፡ አብርሃም ለልጁ ለይስሐቅ ሚስትን ሲፈልግለት፦ ሀብትን አላየም፤ የንጉሣውያን ቤተሰብን አልተመለከተም፤ አፍአዊ ውበትን መመዘኛ አላደረገም፤ ወይም ይህን የመሰለ ሌላ መስፈርትን አልደረደረም፡፡ የነፍስ ንጽህናን እንጂ፡፡

እናቶች ሆይ! ሴት ልጆቻችሁን እንደ ርብቃ አሳድግዋቸው፡፡

እናንተ ማግባትን የምትሹ ወጣቶች ሆይ! ይስሐቅን ምሰሉት፦ ዘፈንን፣ ዳንኪራን፣ ሳቅና ስላቅን፣ የከበሮንና የዋሽንት ጫጫታን፣ ሌላውንም የዲያብሎስ ትርኢት በሰርጋችሁ ቀን አታስቡ፡፡ ከዚህ ይልቅ በምታደርጉት ኹሉም ላይ እግዚአብሔር እንዲቀድማችሁ ለምኑት፡፡ ይህን ያደረጋችሁ እንደኾነ ትዳራችሁ ፍቺ፣ ዝሙት፣ ቅናት፣ ጭቅጭቅ፣ ንትርክ የሌለበት ኾኖ ይፀናላችኋል፡፡ ይህን ያደረጋችሁ እንደኾነ፥ ሌላው በረከትም ተትረፍርፎ ይመጣላችኋል፡፡ የአውሎ ነፋስ ዓይነት በዙሪያችሁ ቢነፍስም፥ አትነዋወፁም፡፡

እናንተ ልጃገረዶች ሆይ! ርብቃን ምሰሏት፡፡ የትዳር አጋራችሁን ፍጹም ለማፍቀር የተዘጋጃችሁ ኹኑ፡፡ ይህን ያደረጋችሁ እንደኾነ ቤታችሁ ፍጹም ሰላማዊ ባሎቻችሁ የምትልዋቸውን የሚያደርጉና በፍቅራችሁ የሚንበረከኩ ይኾናሉ፡፡ ትዳር እንዲህ ኾኖ ሲጀመር፥ እግዚአብሔርንና ወላጆቹን ደስ የሚያሰኝ ልጅ ይገኝበታል፡፡

የቤት ዕቃዎችን መግዛት ስንፈልግ፥ በጣም እንጠነቀቃለን፡፡ የሻጮቹን ማንነት አይተን፣ የዕቃዉንም ጥንካሬ አገላብጠን ተመልክተን ነው የምንሸምተው፡፡ ሚስት ስናገባም ከዚህ የበለጠ ልንጠነቀቅ ይገባናል፡፡ የገዛነው ዕቃ ችግር ቢኖርበት ለሸጠልን ሰው መመለስ እንችላለን፡፡ ሚስት ስናገባ ግን ወደ ቤተሰቦቿ መመለስ አንችልም፤ እስከ ዕድሜአችን ፍጻሜ ድረስ ከእኛ ጋር ነው የምትኾነው፡፡ ክፉ ናት ብለን ብንመልሳት፥ በሕገ እግዚአብሔር መሠረት አመንዝራ እንኾናለን፡፡ ስለዚህ፥ ሚስት ስትመርጡ የሀገራችሁን ሕገ መንግሥትን ብቻ አታንብቡ፤ ከኹሉም በፊት ሕገ ቤተ ክርስቲያንን አንብቡ እንጂ፡፡


Forward from: የደ/መ/ቅዱስ ሚካኤል ካቴድራል ፈለገ ዮርዳኖስ ሰ/ት/ቤት መ/መ ክፍል
✝️ የድጋፍ ጥሪ✝️

እህታችን ኖላዊት መለሰ ባጋጠማት የልብ ሕመም ምክንያት ዶክተሮች ቀዶ ጥገና እንድታደርግ አዘዋታል፡፡ ለዚህም ከፍተኛ ወጪ ተጠይቃለች ይህም በሷ አቅም ሊደረግ ስለማይችል ስለዚህ ሁላችንም ተረባርበን እናድትድንና አብራን በሙሉ ጤንነት እንድታገለግል እንድናግዛት በመልአኩ ቅዱስ ሚካኤል ስም በትህትና እንጠይቃለን፡፡

▶️ መደገፍ ለምትፈልጉ
- አቢሲኒያ ባንክ - 143265048
- ቴ-ሌ ብር - 0991667840
- ንግድ ባንክ - 1000450190792

‹‹ እውነት እላችኋለሁ ከሁሉ ከሚያንሱ ከነዚህ ወንድሞቼ ለአንዱ ስላደረጋችሁት ለእኔ አደረጋችሁት ይላቸዋል፡፡›› ማቴ.25፡40


ቃና ዘገሊላ:-
አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ጥር ዐሥራ ሁለት በዚችም ቀን የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የገሊላ ክፍል በሆነች በቃና በሠርግ ቤት የሠራው የተአምራቱ መታሰቢያ ይደረግ ዘንድ የቤተ ክርስቲያን መምህራን ሥርዓት ሠሩ::

ቅዱስ ወንጌል እንደ ተናገረ ይህች የተአምራቱ መጀመሪያ ናት::

የእመቤታችን ድንግል ማርያም አማላጅነት የተገለጠበት ዕለት ነው:: ውኃውን ለውጦ መዓዛው የሚጥም ጣፋጭ ወይን አድርጎታልና::

በዚህም አሳዳሪው ምስክር ሆነ::

ሙሽራው በጠራው ጊዜ ሰው ሁሉ መልካሙን ጠጅ አስቀድሞ ያጠጣል ከሰከሩም በኋላ ዝቅተኛውን ያጠጣል:: አንተ ግን የተሻለውን ጠጅ ወደ ኋላ አቆይተህ አጠጣህ አለው::

ጌትነቱንም ገለጠ ደቀ መዛሙርቱም አመኑበት::

ዳግመኛም በዚህ ዕለት የከበረ መልአክ የመላእክት አለቃ የሚካኤል የበዓሉ መታሰቢያ ነው::

በዚህች ቀን እስራኤል ወደተባለ ያዕቆብ እግዚአብሔር ልኮታልና ከወንድሙ ከኤሳው ፈርቶ ሳለ አዳነው:: ዮርዳኖስንም አሻግሮ ወደ እናቱ ወንድም ወደ ላባ ሔደ::

እርሱም ሁለቱን ልጆቹን ልያንና ራኄልን አጋባው ከዚህም በኃላ ከብዙ ገንዘብና ከልጆቹ ጋር መንገዱን እየጠረገና እያቀና በሰላም በጤና ወደ አገሩ መለሰው:: ወንድሙ ኤሳውም በፍቅር በሰላም ተቀበለው::

ስለዚህም የሊቀ መላእክት ሚካኤል የበዓሉ መታሰቢያ ነው::

ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በዚህ በከበረ መልአክ አማላጅነት ይማረን::

ለርሱም ከቸር አባቱ መሐሪና ይቅር ባይ ከሆነ መንፈስ ቅዱስም ጋር ምስጋና ይሁን ለዘላለሙ አሜን::
🇪🇹@ethiopianorthodoxs⛪️⛪️


"ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመጠመቁ ምክንያት ከብሉይ ወደ ሐዲስ፥ ከኦሪት ወደ ወንጌል አሻገረን፤ የመንግሥተ ሰማያትን ደጅ ከፈተልን፤ ወደ ሀገራችን (ወደ ሰማይ) ይጠራን ዘንድ ብቻ ሳይኾን ሊነገር በማይችል ክብር ያከብረን ዘንድም ቅዱስ መንፈሱን ላከልን፡፡"
                       ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
Share https://t.me/ethiopianorthodoxs /


🍡🍡🍡🍡🍡🍡🍡🍡🍡🍡🍡🍡
              የከተራ በዓል

ኢየሱስ ክርስቶስ አምላከ አማልክት የጌቶች ጌታ የነገሥታት ንጉሥ ሲሆን ወደ ዮርዳኖስ ወርዶ በዮሐንስ እጅ ተጠምቋል::

የሁሉ አስገኝ ፈጣሪያችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ዮሐንስ ሔዶ መጠመቁን ለማዘከር ማደሪያው የሆኑት ታቦታት ወደ ጥምቀተ ባህር ይሔዳሉ::

ጌታችን በዮርዳኖስ ወንዝ በመጠመቁ ዮርዳኖስን እንደ ቀደሰ ሁሉ ታቦታቱም ባህረ  ጥምቀቱን ሊቀድሱ ይወጣሉ::

በዚህ በከተራ ዕለት ምእመናን ሁሉ ታቦታትን አጅበው ነጭ ለብሰው እያሸበሸቡና እየዘመሩ ፍጹም መንፈሳዊ በሆነ ሥርዓት ያከብራሉ::

ታቦታቱ ከመንበራቸው ተነስተው ወደ ጥምቀተ ባህሩ ሲሔዱም ሆነ ሲመለሱ በሙሉ ኃይሉ ሕዝቡ ሁሉ እየተከተለ ይዘምራል:: ልክ እንደ ዳዊት "ዳዊት በሙሉ ኃይሉ በእግዚአብሔር ፊት ይዘምር ነበር::" እንዳለ:: መጽ. ሳሙኤል ካልዕ ም.5 -:-15::

በቃል ኪዳኑ ታቦት ፊት የምንፈጽማቸው ማንኛውም መልካምም ሆነ ክፉ ነገር በእግዚአብሔር ፊት እንደፈጸምነው ነው:: መጽሐፍ እንደሚለን::

ዳዊትም ሆነ ሕዝቡ የእግዚአብሔር ታቦት ወደ ከተማቸው ስትገባ በቅኔ በበገና በከበሮ በመስንቆ በነጋሪትh በጸናጽል ሆ እያሉ እየዘመሩ ይሔዱ ነበር ነው የሚለን:: ልብ እንበል በእግዚአብሔር ፊት ነው የሚለው መጽሐፍ:: በታቦታቱ ፊት የምንፈጽመው ዝማሬ በእግዚአብሔር ፊት ነው የምናደርገው:: መጽ. ሳሙኤል ም.5 በሙሉ እንመልከት::

ሁላችን የቤተ ክርስቲያን ልጆች በዚህ ቀን ደምቀን ነጭ ለብሰን የቃል ኪዳኑ ታቦት በሚያልፍበት አካባቢ ሙሉ ኃይላችን ተጠቅመን ልንዘምር ይገባል:: አካባቢውን ሙሉ ኃይላችን ተጠቅመን በጥቅስ በቅዱሳን ሥዕላት በምንጣፍ በቀጤማ በሽቶ በሰረገላ ልናከብረው ይገባል::

የእግዚአብሔር ቸርነት የድንግል ማርያም አማላጅነት የሁሉ ቅዱሳን በረከትና ረድሄት ከሁላችን ላይ ይኑር ለዘላለሙ አሜን::
መልካም የከተራ በዓል!!!
🇪🇹@ethiopianorthodoxs⛪️


🌼🌺🌼🌺🌼🌺🌼🌺🌼🌺🌼
"ሥላሴን" "ቅድስት ሥላሴ" እያልን የመጠራታችን ምስጢር፡-

አንድም ሴት ወይም እናት ልጆቿን አልወለደችም ተብላ አትጠረጠርም ሥላሴም ይህንን ዓለም ፈጥረዋል እናም አልፈጠሩም ተብሎ አይጠረጠሩም፡፡

አንድም ሴት በባህሪዋ ልጅን ታስገኛለች፣ሥላሴም ይህንን ዓለም ካለመኖር ወደ መኖር አምጥተው ስለፈጠሩት በሴት አንጻር ቅድስት ተብለው ይጠራሉ፡፡

አንድም ሴት አዛኝ ናት፣ለታናሹም ሆነ ለታላቁ ትራራለች ሥላሴም እንደዚሁ ለፍጥረት ሁሉ ያዝናሉ፣ ይራራሉ፣ ምህረትን ይሰጣሉ፡፡ ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ እንዲህ ይላል ”ምህረታችሁ ከልክም በላይ የበዛ በሴት አንፃር ቅድስት ተብላችሁ የተጠራችሁ የምህረት ወንዶች ሥላሴ" በማለት ያመሰጥራል፡፡ ስለእዚህ ቅድስት ለምን ተባሉ ቢባል በረከታቸው፣ ርህራሄያቸውና፣ ይቅር ባይነታቸው መሆኑን ማወቅ አለብን፡፡

አንድም ሴት ልጇ ቢታመምባት አትወድም፣ ሥላሴም አንድም ልጅ በዲያቢሎስ እጅ ተይዞ በሐጥያት እንዲታመሙ አይወዱም፣ አይፈቅዱም በመሆኑም “ቅድስት” ይባላሉ፡፡

አንድም ሴት የልጇን ነውር አትፀየፍም ልጄ ቆሽሿል፣ ተበላሽቷል ብላ ፊቷን አታዞርም፣ ሥላሴም የሰውን በሐጥያት መቆሸሽ ሳይፀየፉ በቸርነታቸው ጎብኝተው ለንስሐ ያደርሱታል ይህንን የፅድቅ አየር የምንምገው ያማረውንም ብርሃን የለበስነው ስለ ፅድቃችን ሳይሆን በሥላሴ ቸርነት ነውና ስለዚህም ሥላሴን በሴት አንጻር ቅድስት እንላቸዋለን፡፡

አንድም ሴት ልጆቿን ፈጭታና ጋግራ ትመግባቸዋለች ሥላሴም እነደዛው ናቸው በዝናብ አብቅለው በፀሐይ አብስለው ፍጥረታትን ሁሉ ይመግባሉ፡፡ ስለእዚህ ሥላሴ እንደ እናት ሁሉንም ይመግባሉና በሴት አንፃር ቅድስት ይባላሉ፡፡

በዚህ ምክንያት ሥላሴን ቅድስት ሥላሴ እያልን በፍቅር እንጠራለን፡፡

የቅድስት ሥላሴ ረድኤት በረከት አይለየን፡፡
🇪🇹@ethiopianorthodoxs⛪️


ሐዋርያው ቅዱስ ዮሐንስ:-
አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ጥር አራት በዚች ቀን የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የሚወደው የከበረና የተመሰገነ ወንጌልን የጻፈ የሐዋርያው ዮሐንስ የፍልሰቱ መታሰቢያ ነው::

አባቶቻችን ይህን ቅዱስ ዮሐንስን በተለያዩ ስሞች እንዲህ በማለት በዜማ ይጠሩታል። ዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ፤ ዮሐንስ ሐዋርያ፤ ዮሐንስ ወንጌላዊ፤ ዮሐንስ ወልደ ዘብዴዎስ፤ ዮሐንስ ፍቁረ እግዚእ፤ ዮሐንስ አቡቀለምሲስ፤ ሰአል ለነ ከመ ንስማዕ ወንግበር ቃለ ወንጌሉ ለወልደ ማርያም ድንግል። ይላሉ ዘወትር በሰዓታቱ።

ለዚህም ቅዱስ ወደ እስያ ሀገር ይሔድ ዘንድ ዕጣው በወጣ ጊዜ እጅግ አዝኖ አለቀሰ:: እነርሱ ክፉዎች ከሀዲዎች ልባቸው የደነደነ መሆናቸውን አውቋልና:: ግን ከጌታችን ኃይልን መጽናናትን አግኝቶ ከደቀ መዝሙሩ ከአብሮኮሮስ ጋር ወጥቶ ወደ ክፍሉ ሔደ::

ወደ ኤፌሶንም ሊሔድ ወዶ በመርከብ ላይ ተሳፈረ:: መርከቡም ተሰበረ:: እየአንዳንዱ በመርከብ ስባሪ ሠሌዳ ላይ ተንጠለጠለ:: ደቀ መዝሙሩን አብሮኮሮስንም የባሕሩ ማዕበል ወደ አንዲት ደሴት አደረሰው:: ቅዱስ ዮሐንስ ግን በባሕሩ ማዕበል መካከል አርባ መዓልት አርባ ሌሊት ኖረ::

ከዚህም በኋላ ደቀ መዝሙሩ አብሮኮሮስ ወዳለበት ወደ የብስ ባሕሩ ተፋው:: ስለ መገናኘታቸውም እግዚአብሔርን አመሰገኑት:: በዚያም ጊዜ ተነስተው ወደ ኤፌሶን ከተማ ገቡ:: ግን በክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስም ይሰብኩ ዘንድ አልተቻላቸውም እነዚያ ያገር ሰዎች እጅግ የከፉ ናቸውና::

ስለዚህ ምክንያት ፈጥረው ዮሐንስ ሮምና ለምትባል ሴት የውሽባ ቤት እሳት የሚያነድ ሆነ:: ረድኡ አብሮኮሮስም አጣቢ ሆነ:: ያቺ ሴትም እጅግ ታሰቃያቸው ነበር:: መጻተኞችም ስለሆኑ ታጎሳቁላቸዋለች:: ትደበድባቸዋለች:: ትረግማቸዋለች:: ባሮቿም እንደሆኑ ጽፈውላታልና ለእርሷ ባሮች አደረገቻቸው በዚህም በታላቅ ጉስቁልና ውስጥ ኖሩ::

ከዚህም በኋላ በአንዲት ዕለት ይታጠብ ዘንድ የአገር ገዥው ልጅ ገባ:: በዚያም የውሽባ ቤት ከተሠራ ጀመሮ የሰይጣን ኃይል አለ:: የመኰንኑንም ልጅ አንቆ ገደለው:: በዚያንም ጊዜ የአገር ሰዎች ለዚያ ለሞተው ሊያለቅሱለት ተሰበሰቡ:: የከበረ ዮሐንስም ከእርሳቸው ጋር መጥቶ እንደ ሰው ሁሉ ሊያይ በዛው ቆመ::

ሮምናም በአየችው ጊዜ ረገመችው አንተስ በጌታዬ ልጅ ሞት ደስ ብሎህ ልትዝትብኝ መጣህ አለችው:: ቅዱሱ ግን በቅንነት አይዞሽ አትዘኝ አላት:: ይህንንም ብሎ ወደ ሞተው ቀረብ ብሎ  በመስቀል ምልክት አማተበበት:: በፊቱም ላይ እፍ አለበት:: በዚያንም ጊዜ ያ የሞተው ድኖ ተነሣ:: የአገር ሰዎችም ደነገጡ::

ሮምናም ወዮልኝ  እግዚአብሔር የሚሉት አምላክ አንተ ነህን አለች:: እርሱም አይደለሁም እኔ አገልጋይ ሐዋርያው ነኝ እንጂ አላት:: በእነርሱ ላይ የሠራችውን በደል ሁሉ ይቅር ይሏት ዘንድ መሪር ለቅሶ በማልቀስ ሐዋርያትን ለመነቻቸው:: እነርሱም አረጋጓት አጽናኗትም::

ከሀገሩም ሰዎች ብዙዎቹ በክብር ባለቤት በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ አመኑ:: የክርስትና ጥምቀትንም አጠመቃቸው::

በፊታቸውም ብዙዎች የሆኑ ድንቆች ተአምራትን አደረጉ:: ይህንንም አይተው የሀገሩ ሰዎች ሁሉም በጌታችን አመኑ::

ከጣዖታቱ አገልጋዮች በቀር እነርሱም ሰይጣን በእርሱ ላይ ስለሚያነሣሣቸው ሊገድሉት ይሹ ነበር:: ነገር ግን ምርጦቹን እግዚአብሔር ጠበቃቸው::

የከበረ ዮሐንስም ሁሉንም እግዚአብሔርን ወደ ማወቅ እስከመለሳቸው ድረስ ታላቅ ድካምና ጭንቅ የሆነ መከራ ደረሰበት:: የከበረ ሐዋርያ ጳውሎስም ስለ ልቡናቸው ደንዳናነት ጣዖታትን ስለመውደዳቸው ስለ እነርሱ መስክሮአል::

እርሱም ዮሐንስ በታላቅ ድካም ወደ ቀናች ሃይማኖት መለሳቸው:: ከዚህም በኋላ ኤጴስ ቆጶሳትን ቀሳውስትን ዲያቆናትን ሾመላቸው::

ከዚህም በኋላ ከእስያ በዙሪያዋ ወዳሉ አገሮች ሁሉ ወጥቶ አስተማረ እግዚአብሔርንም ወደ ማወቅ መለሳቸው::

ይህም የከበረና የተመሰገነ ዮሐንስ በዚህ ዓለም ዘጠና ዓመት ኖረ:: እጅግም ሸመገለ:: ግን እንደ ባልንጀሮቹ ሐዋርያት በመሰየፍ ሞትን አልቀመሰም::

ስለ ድንግልናውን ስለ ንጽሕናው ይህ ሆነ:: ሁሉም በክብር ይስተካከሉ ዘንድ እርሱም ወንጌልን ቀለምሲስ የሚባለውን ራእይ ሦስት መልአክታትን የጻፈ ነው::

ራት ሲበሉ በጌታ ኢየሱስ አጠገብ የተቀመጠውና አቤቱ የሚያሲዝህ ማን ነው ያለው እርሱ ነው::

ጌታችንም በተሰቀለ ጊዜ ከእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ጋር በመስቀሉ አጠገብ የቆመ እናቱንም እንሆ ልጅሽ ያላት እርሱን ደቀ መዝሙሩን እንኋት እናትህ ያለው ነው::

ጴጥሮስም እርሱን ሲከተለው በአየው ጊዜ ስለርሱ ጌታ ኢየሱስን አቤቱ ይህስ እንዴት ነው ብሎ የተናገረ:: ጌታ ኢየሱስም እስክመጣ ድረስ ይኖር ዘንድ ከወደድኩ አንተ ምን አለህ አንተ ግን ተከተለኝ ያሉት ይህ ነው::

የተመሰገነ ዮሐንስም ከዚህ ዓለም የሚወጣበት ሰዓት እንደ ቀረበ በአወቀ ጊዜ ሕዝቡን ጠራቸው:: ጸሎትንም ጸለየና ኅብስቱን ባርኮ ቆረሰ ይህም የጌታችን ሥጋውንና ደሙን ሰጣቸው በቀናች ሃይማኖትም እንዲጸኑ አዘዛቸው:: ባረካቸው:: አጽናናቸውም::

ከዚህም በኋላ ደቀ መዝሙሩ አብሮኮስን ከወንድማቸው ሌሎች ሁለቱን መቆፈሪያ ይዘው ይከተሉት ዘንድ አዘዘ::

ከኤፌሶንም ከተማ ውጪ ወጣ ጉድጓድ እንዲቆፍሩም አዘዘ:: ከውስጥዎም ገብቶ ቆመ::  ልብሱንም አስወገደ:: ከአንድ የበፍታ ቀሚስ በቀር አላስቀረም እጆቹንም አንሥቶ ጸለየና ወደ ከተማ ይመለሱ ዘንድ አሰናበታቸው::

በክርስቶስም ሃይማኖት ይጸኑ ዘንድ ለሕዝቡ ይነግሩአቸው ዘንድ አዘዛቸው:: በጎ ሥራዎችንም ይሠሩ ዘንድ ጌታችን ለሁሉም እንደ ሥራው ይከፍለው ዘንድ አለውና::

ሁለተኛም እንዲህ አላቸው:: እኔ ከሁላችሁ ደም ንጹሕ ነኝ ከእግዚአብሔር ትእዛዝና ሕግ ሳልነግራችሁ የተውኩት ምንም ምን የለምና እናንተም ከእንግዲህ ከቶ ፊቴን አታዩኝም::

ይህንንም በተናገረ ጊዜ አለቀሱ እጆቹንና እግሮቹን ስመው በጕድጓድ ውስጥ ትተዉት ወደ መንደር ተመለሱና የሆነውን ሁሉ ለሰዎች ነገሩዋቸው:: ሁሉም ደንግጠው መጡ:: ግን ልብስና መጫሚያ እንጂ መቃብሩን አላገኙም:: እጅግም አደነቁ ደቀ መዝሙሩ ዮሐንስን በዚህ በጎ ዕረፍት ያሳረፈው እግዚአብሔርንም አመሰገኑት::

ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በዚህ በከበረ አባት በሐዋርያ ዮሐንስ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን::
🇪🇹@ethiopianorthodoxs⛪️⛪️




“ስለተገለጠልን ምስጢር ምስጋና አቅርቡ ሰው የማይሆን ሰው ሆኗልና ቃል ተዋህዷልና ቅድምና የሌለው ሥጋ ጥንታዊ ቀዳማዊ ሆነ፣ ዘመን የማይቆጠርለት መለኮት ዘመን ተቆጠረለት” ቅዱስ ኤፍሬም
መልካም የልደት በዓል


"የጌታ ልደት በቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ"
ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ የከበረ የክርስቶስን ልደት ነገር በተናገረበት አንቀፅ እንዲህ አለ ቀዳማዊ አምላክ ዛሬ ተወለደ ፤ ጥንቱን ገንዘቡ ባይደለ ባህርይ ተገኝ ፤ እርሱ ቀዳማዊ አምላክ ነው ፤ ሰው በመሆኑም ከባህርይው አልተለወጠም፡፡ የመለኮቱ መገኝትም ከእመቤታችን ከተወለደ ወዲህ አይደለም ፤ ከአብ ከመንፈስ ቅዱስ ጋር ዓለም ሳይፈጠር የነበረ ጥበብ ነውንጂ ፤ የማይታመም እርሱ ከባህርይ መለኮቱ ሳይለወጥ ሕማም የሚስማማውን ስጋን ተዋሃደ፡፡ ዳግመኛም በልዑል ዙፋን ላይ ተቀምጦ ያለ እርሱ በበረት ተጣለ ስጋ ሳይሆን የነበረ የማይዳሰስ ወልድ ዋህድ ዛሬ ስጋን በመዋሃድ ተዳሰሰ ፤ ሃጢአትን የሚያስተሰርይ እርሱ በጨርቅ ተጠቀለለ፡፡
መፅሃፍ እንዲህ አለ ፦ ብልህ ሽክላ ሰሪ የሚሰራውን የለዘበ ጭቃ በአገኝ ጊዜ ከእርሱ መልካም እቃ እንዲሰራ እንደዚሁ ጌታችን የዚህችን ድንግል ንፁህ ስጋዋን ንፅህት ነፍሷን ባገኘ ጊዜ ነፍስ ያለችውን ስጋ ሊዋሃደው ፈጠረ፡፡ እንደወደደ ከድንግል ነፍስን ስጋን ፈጥሮ ለበሰ እርሱንም ተዋህዶ ዛሬ ተወለደ ሕፀፅ ያለበት ነው ብሎ ባህርያችንን አልተወውም ፤ ስጋን በተዋህዶ ጊዜ ቃል ከምላቱ አልተወሰነም ፤ ስጋ የፈጣሪ አካል ባህርይ በሆነ ጊዜ ፍፁም አምላክነትን አገኝ እንጂ፡፡ ምን እላለሁ? ምንስ እናገራለሁ? ከዘመን አስቀድሞ የነበረ እርሱ ትንሽ ህፃን ሆኗልና፡፡
እኔ ፈፅሜ አደንቃለሁ ፤ ከሰማየ ሰማያት በላይ የሚሆን ፡ በዘላለማዊ ዙፋን የሚኖር እርሱ በበረት ተጣለ ፡ ከስጋዌ አስቀድሞ አይዳሰስ የነበረ አንዱ እርሱ በምድራውያን እጅ ተዳሰሰ ፡ ሃጢአትን የሚያስተሰርይ እርሱን በጨርቅ ጠቀለሉት ፤ ይህን ወዷልና፡፡ ክብሩ ተለይቶት የነበረ ስጋን ክቡር አምላክ ሊያደርገው ፤ የፀጋ ገዥነትን አጥቶ የነበረ ስጋንም የባህርይ ገዥ ሊያደርገው ወደደ ፤ አዳም ከእኛ እንዳንዱ ሆነ ያለውንም ሰው በመሆን ሊገልጠው ወደደ፡፡ ስለዚህ ስጋየን ተዋሃደ ፡ ወንጌልን ሲያስተምር እሰማው ዘንድ ስጋየን በተዋህዶ ገንዘብ አደረገ ፤ መንፈስ ቅዱስን ሰጠኝ ፡ ተቀበልኩ ፡ ለእኔም ፍፁም ህይወትን ገንዘብ አደረግሁ ፡ እርሱ ያከብረው ዘንድ ስጋየን ተዋሃደው ፡ የሚያድነኝ መንፈስ ቅዱስን ሰጠኝ፡፡ በቅዳሴውም እንዲህ አለ፡- ዳግመኛም የወልድ አነዋወሩ እንደምን እንደሆነ መውረዱም እንዴት እንደሆነ እንናገራለን፡፡ ከአባቱ ሳይወጣ መጣ ከአነዋወሩ ሳይለይ ወረደ ከሶስትነቱ ሳይለይ መጣ ከአንድነቱም ሳይለይ ወረደ ከዙፋኑም ሳይለይ በስጋ ልጅ አደረ ከምላቱ ሳይወሰን በማህጸን ተጸነሰ በላይ ሳይጐድል በማህፀን ተወሰነ በታችም ሳይጨመርበት ተወለደ ከኃጢአት በቀር ፈፅሞ ሰው ሆነ እንደ እግዚአብሔር እየሰራ እንደ ባርያ ታየ፡፡ ዳግመኛም እንዲህ አለ ፍቅር ሰሃቦ ለወልድ ኃያል እም መንበሩ ወአብጽሖ እስከለሞት /ፍቅር ኃያል ወልድን ከዙፋኑ አወረደው እስከ ሞትም አደረሰው።/
እንግዲህ እኛ ግን ከጨለማ ወደሚደነቅ ብርሃኑ የጠራን የእርሱን በጎነት እንድንነግር የተመረጥን ቅዱስ ሕዝብ ለርስቱ የተለየን ወገን መሆናችን አውቀን በብርሃን እንኑር ጨለማውም ያልፋልና እውነተኛውም ብርሃን ይበራል በቀን እንደሚሆን በጽድቅና በቅንነት ሆነን (1ጴጥ 2፡9 ፣ 1ዮሐ 2፡8) የጌታችንን የመድኃኒታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ልደት እናክብር።
🇪🇹@ethiopianorthodoxs⛪️⛪️




Video is unavailable for watching
Show in Telegram


አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ታኅሣሥ ዐሥራ ዘጠኝ በዚች ቀን የመላእክት አለቃ የመላኩ የቅዱስ ገብርኤል የበዓሉ መታሰቢያ ነው::

በዛሬው ቀን በያለንበት ቤተ ክርስቲያን አምላከ ቅዱስ ገብርኤል ማረን ይቅር በለን ከተቃጣብን ከመጣብን እሳት አድነን የምንልበት ቀን ነው።

እርሱም በባቢሎን አገር ከነደደ እሳት ውስጥ በጨመሩአቸው ጊዜ አናንያ አዛርያ ሚሳኤልን ያዳናቸው ተራዳኤ መልአክ ነው::

"ለገብርኤል መልአክኪ ዘፍሡሕ ገፁ" ፊቱን ደስ ያለው የተላላከልሽ የገብርኤል ድምፁን በመስማት ያለ አባት ፀነስሽው። በዚህም አብሳሬ ትብስኅት የተባለው ቅዱስ ገብርኤል ነው።

ከሰባቱ ሊቃነ መላእክት አንዱና በእግዚአብሔር ፊት የሚቆመው ታማኝ መልአክ ቅዱስ ገብርኤል ነው፡፡

በተረዳኢነቱና በአማላጅነቱ በክርስቲያኖች ዘንድ ይወደዳል፡፡ ምክንያቱም ያዘኑትን ለማፅናናት የምስራች ለመንገር ከእግዚአብሔር ወደ ምእመናን ይላካልና፡፡

ገብርኤል ማለት የእግዚአብሔርን ልጅ የሚመስል ጌታና አገልጋይ ማለት ነው፡፡

ብርሃናዊ መልአክ ቅዱስ ገብርኤል ቅዱሳን ሰማዕታት ገድላቸውን እንዲፈፅሙ እሳቱንና ስለቱን ተሳቀው ወደ ኋላ እንዳይመለሱ ይረዳቸዋል፡፡

ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያናችን የቅዱሳን መላዕክትን ወርሃዊና ዓመታዊ በዓላቸውን በፀሎትና በምስጋና ታከብራለች፤ በተለይ ታኅሣሥ ዐሥራ ዘጠኝ ቀን የሚከበርበት ምክንያት ብርሃናዊ መልአክ ቅዱስ ገብርኤል ሠለስቱ ደቂቅን ከዕቶን እሳት ያዳነበት ዕለት በመሆኑ ነው፡፡

በጣዖት ፍቅር እጅግ ያለመጠን ልቡ ተቃጥሎ የነበረው የባቢሎን መሪ ናቡከደነፆር ቁመቱ ስድሳ ወርዱ ስድስት ክንድ የሆነውን የወርቅ ምስል አሰርቶ መኳንንቱን ሰብስቦ ሕዝቡ በሙሉ ለጣዖቱ እንዲሰግድ አዋጅ አወጀ፡፡

ያ ዘመን ለእግዚአብሔር ወዳጆች የፈተና ዘመን ነበር፡፡ አስመሳዮች ለጣዖት ሰገዱ፤ ተረበረቡ፡፡ እውነተኛ አማኞች ግን በእግዚአብሔር ላይ ያላቸውን እምነት ‹‹ ንጉስ የወደደው፣ ጊዜ የወለደው›› በሚል አስተሳስብ አይለወጥም፡፡ በዚያ ፈታኝ ዘመን ነበር ሶስት ታማኝ የእግዚአብሔር ባለሟሎች የተገኙት፡፡

ንጉሱ ላቆመው ጣኦት ያልሰገደ ወደ እቶን እሳት ተጥሎ እንደሚሞት ቁርጥ ውሳኔው መሆኑን ወጣቶቹ በሚገባ ያውቁታል ግን ይህንን አልፈሩም፡፡

ንጉስ ሆይ አምላካችንን ክደን አንተ ላቆምከው ጣዖት አንሰግድም አሉት፡፡

ሶስቱ ወጣቶች የወሰዱት ይህ አቋም ለንጉሱ ታላቅ ራስ ምታትን  ፈጠረ፤ ንጉሱም አገልጋዮቹን ጠርቶ እሳቱ ሰባት እጥፍ እንዲነድ ትዕዛዝ ሰጠ፡፡

እሳቱም ሰባት እጥፍ ነደደ፡፡ ወዲያውኑ የንጉሱ አገልጋዮች አናንያ ፣ አዛርያን እና ሚሳኤልን እያንከበከቡ አንጠልጥለው ወደ ዕቶን እሳቱ ወረወሯቸው፡፡

በእሳቱ ኃይል የተነሳ አገልጋዮቹም በእሳቱ እየተጠለፉ እንደ ማገዶ ነደዱ፡፡ ሠልስቱ ደቂቅ ግን ከየት እንደመጣ ከማይታወቅ  እንግዳ ጋር በመሆን በዕቶን እሳት ውስት ይንሸራሸሩ ጀመር፡፡ ይህ ተዓማራት ንጉሡንና መኳንንቱን አስገረመ፡፡  ንጉሡም በዚህ ወቅት፦

‹‹ እነሆ እኔ በእሳቱ መካከል የሚመላለሱ አራት ሰዎች አያለሁ እሳቱ ምንም አላቆሰላቸውም አራተኛውም የአማልክትን ልጅ ይመስላል ፡፡ ››  አለ፡፡

ንጉሥ ናብከደነፆር በግልፅ ተመልክቶ እንደመሰከረው የነደደውን እሳት በማብረድ ለሠልስቱ ደቂቅ ቤዛ የሆናቸው ቅዱስ ገብርኤል ነው፡፡ 

በግዕዙ ‹‹ ወገፁ ለራብዓይ ወልደ እግዚአብኤር ይመስል›› አራተኛውም ፊቱ የእግዚአብሔርን ልጅ ይመስላል ይላል፡፡

አዎን፤ ከዚህ በላይ እንደተገለፀው ሊቀ መላዕክት ቅዱስ ገብርኤል ስለ ሃይማኖታቸው መከራ የተቀበሉትን ወጣቶች የነደደውን እሳት አብርዶ በሃይማኖታቸው እንደ አፀናቸው ተመልክተናል፡፡

የቅዱስ ገብርኤል አማላጅነት እኮ ጥንት የነበረ ብቻ ሳይሆን እስከ አለንብት ዘመን ደርሶ የመልአኩን አማላጅነት በዓይን የተመለከትነው ተጨባጭ ድርጊት ነው፡፡

የነደደ እሳት ውስጥ ገብቶ ከመውጣት ባልተናነሰ መከራ ውስጥ ገብተው በቅዱስ ገብርኤል አማላጅነት ከሞተ ስጋ እና ነፍስ ድነው እውነተኛ  ምስክርነታቸውን የሚሰጡ ብዙዎች ናቸው፡፡

በመልአኩ ስም በፈለቀው ፀበል ተጠምቀው ደዌ የራቀላቸው በምልጃው የተቋረጠው ሕይወታቸው የተቀጠለላቸው እጅግ በርካታ ናቸው፡፡

በየዓመቱ በተለያዩ በቅዱስ ገብርኤል ስም በታነፁ አብያተ ክርስቲያናት የሚሰባሰበው ምዕመን ስዕለቱ የሰመረለት ልመናው የተሰማለት ተምኔቱ የተፈፀመለት ብዙ እንደሆነ ግልፅ ነው፡፡

ስለዚህ ለመላዕክት አለቃ ለቅዱስ ገብርኤል የተሰጠውን ፀጋ ተረድተን መልአኩን ልናከብረውና ልናመሰግነው ይገባል፡፡

ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም መላኩ ቅዱስ ገብርኤል በአማላጅነቱ በፊታችን ቆሞ ይጠብቀን ያድነን ለዘላለሙ አሜን::
🇪🇹@ethiopianorthodoxs⛪️⛪️


አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ታኅሣሥ ዐሥራ አንድ በዚህች ቀን የኤጲስ ቆጶሱ በርተሎሜዎስና የሰማዕቱ በጥላን መታሰቢያቸው ነው::

የአባቶቻችን በረከታቸው ድል የማትነሳ በክርስቶስ ደም የታነፀች ተዋሕዶ ሐይማኖታቸው ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ በእውነት አሜን::
🏝🏝🏝🏝🏝🏝🏝🏝🏝🏝🏝🏝
#የሰው_ልጅ_ከሞት_በኋላ_ይህ_የምንመካበት #ሰውነት ,,,
በ3ኛው ቀን ጥፍሮቻችን ተነቅለው መውደቅ ይጀምራሉ,,,
በ 4ኛው ቀን ፀጉራችን መበስበስ ይጀምራል
በ 5ኛው ቀን አእምሮአችን በከፍተኛ ሁኔታ መበላሸት
ይጀምራል
በ 6ኛው ቀን የሆድ እቃችን በመቅለጥ በአፋችንና በተለያዩ
የሰውነታችን ቀዳዳዎች መፍሰስ ይጀምራል
በ 60ኛው ቀን ከአጥንታችን ውጪ አንዳችም ቀሪ አካል አይኖርም,,,,
ታዲያ ለዚህ ከንቱ አካል መጨካከን ፣ መጠላላት፣ መጎዳዳትና
ስስት ምን ይሰራል?
ዝናም ሀብትም እውቀትም ሁሉ ይህን የተፈጥሮ ህግ ሽሮ
አያቆመንም ቆመን ስንሄድ የማናልፍ ብርቱዎች ብንመስለም
ተሸክመን የምንዞረው በቀናት ውስጥ አፈር የሚበላውን ስጋ ነው።
ይልቅስ እንዋደድ፣ እንፋቀር ፣ በጎ ነገር እንስራ፣ ህሊናችንን የሚያስደስት ምግባር እንፈፅም።
ደስ ብሎን ውለን ደስ ብሎን እናድራለን።

🇪🇹@ethiopianorthodoxs⛪️




አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ኅዳር ሃያ አንድ የጽዮን የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በዓሏ ነው::

"ትውልድ ሁሉ ያመሰግኑኛል" እንዳለች እርሷ እመቤታችን በዛሬው ዕለት እስትንፋስ ያለው ፍጥረት ሁሉ ጽዮንን ከበው ያመሰግኗታል::

በእውነት ጽዮን እናታችን ናት፣ እርሷ መመኪያችን ናት፣ እሷን ከብን እናመሰግናታለን፣ ለጽዮን የጸጋ  ስግደት እንሰግድላታለን።

አባቶቻችን እንዳስተማሩን ቅዱሳን መጻሕፍት እንደመሰከሩልን ሰው እናታችን ጽዮን ይላል በውስጧም ሰው ተወለደ።

ጌታ ከእመቤታችን በስጋ ተወለደ ።
እርሱ እራሱ ልዑል መሰረታት ማለት እግዚአብሔር እመቤታችንን በንፅህና አጸናት በእመቤታችን ያመኑ ሁሉ ደስ ብሏቸው እንዲኖሩ ይናገራቸዋል ።
( መዝ 130÷131--18)

ጽዮን የሚላት በወርቁ እመቤታችንን ነው ይህም ይታወቅ ዘንድ ይህቺ ለዘለአለም ማረፊያዬ ናት ብሎ ለምድራዊቷ ጽዮን (ለምድሪቱ )አለመሆኑን ያረጋግጥልናል ።

ምክንያቱም ሰማይና ምድር ያልፋሉ ብሎ ራሱ ጌታ በማይታበል ቃል ተናግሯል ።

ስለሆነም ምድሪቱ የዘለዓለም ማረፊያ ልትሆነው አትችልም ለእመቤታችን ግን ይስማማል ይህቺ ለዘለአለም ማረፊያዬ ናት ሲል ለዘለአለም ወላዲተ አምላክ ስትባል የምትኖር ስለሆነ ነው።

ከእርሷ የነሳው (የወሰደው )ስጋ ለዘለዓለም መለኮትን ተዋሕዶ የሚኖር ስለሆነ መርጫታለሁና አድሬባታለሁ አለ
( ትቢ ኢሳ 60÷4) ።

የአስጨናቂዎችሽ ልጆች አንገታቸውን ደፍተው ወደ አንቺ ይመጣሉ የናቁሽም ሁሉ ወደ እግርሽ ጫማ ይሰግዳሉ የእግዚአብሔር ከተማ (ዘጠኝ ወር ከ 5 ቀን ማሕጸኗን አለም አድርጎ ተመስግኖባታል እና ከተማ አለው )የእስራኤል ቅዱስ የሆንሽ ጽዮን ይሉሻል ። ሲል ነው

ምስጋና በዛሬው ዕለት ማኅሌቱ ቅኔው ይፈሳል:: ዕንባዎች በተማፅኖ በደስታ ይፈሳሉ::

የፃድቃን እጆች ለምጽዋት ይፈተሉ:: ድሆች ይጠግባሉ የታረዙ ይለብሳሉ::

በዛሬው ዕለት አብያተ ክርስቲያናት በማኅሌት በሠዓታት በእግዚኦታ በኪዳን በቅዳሴ በትምህርተ ወንጌል ደምቀው አድረው ይውላሉ::

አባ ጊዮርጊስ በመጽሐፈ ሰዓታቱ ላይ:-
ጸጋን የተመላሽ ሆይ በምን ስም እንጥራሽ?
  የመድኃኒት በር ነሽ፤ የብርሃን መስኮት ነሽ፤ የመንግሥት ልጅ ነሽ:: ሰማይ እንበልሽ ይሆን!

✝ልጅሽ የእውነት ፀሐይ ነው፤ ሐዋርያት ኮከቦችሽ ናቸው፤ (እነዚያ) የልጆችሽ መቅረዞች::
የአትክልት ቦታ እንበልሽ ይሆን!

✝ልጅሽ የወይን ተክል ነው፤ ሐዋርያቱ ሐረጎችሽ ናቸው (እነዚያ) የበኵርሽ  ቅርንጫፎች::

✝መርከብ እንበልሽ ይሆን! ቀዛፊው ልጅሽ ነው፤ሐዋርያቱ መርከበኞችሽ ናቸው (እነዚያ) የበኵርሽ ምርጦች::

✝የግንብ ቤት እንበልሽ ይሆን ገንቢው ልጅሽ ነው ሐዋርያቱ ቤተሰቦችሽ ናቸው (እነዚያ) የበኵርሽ ምእመናን::

✝መሠዊያ (መንበር) እንበልሽ ይሆን! ልጅሽ ሊቀ ካህናት ነው፤ ሐዋርያት ተላላኪዎችሽ ናቸው::
(እነዚያ) የበኵርሽ ደቀ መዛሙርት::

✝መሶበ ወርቅ እንበልሽ ይሆን! ልጅሽ የሕይወት እንጀራ ነው ሐዋርያቱ አሳላፊዎችሽ ናቸው (እነዚያ) የበኵርሽ ሥጋ የሚሠዉ::

✝ጽዋ እንበልሽ ይሆን! ልጅሽ የመለኮት ወይን ነው
ዠሐዋርያቱ ካህናትሽ ናቸው (እነዚያ) የበኵርሽ ደም የሚቀዱ ይሏታል:: በማድነቅና በተመስጦም!

"የእግዚአብሔር ጥበብ እንዴት ድንቅ ነው የሥራው ኃይል ትልቅ ነው ፍርዱ ሁሉ ትክክል ነው የስሙ ምስጋና የተባረከ ነው በዕብራይስጢ ማሪሃም የተባለውን ይህችን ቅድስት በሁሉት በኩል ድንግል የሆነች ማርያምን የመረጣትና የወደዳት-:- ከፍ ከፍ ያደረጋት ያከበራት ነውና::

እንግዲህ ምን እንላለን! በእውነት ቅድስት ሆይ ለምኝልን ብቻ እንበላት እንጂ:: ለእርሷ ምስጋና ለማቅረብ የጸዳ ልቡናና አንደበት ያላቸው እንደምን ያሉ ናቸው!

የእግዚአብሔር ቸርነት የድንግል ማርያም አማላጅነት አይለየን ለዘላለሙ አሜን።

@ethiopianorthodoxs


ጾመ ነቢያት:-
አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ሰም ኅዳር ዐሥራ አምስት በዚህች ቀን የስብከተ ገና ጾም መጀመሪያ ነው::

ይህም ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለተወለደበት በግብጽ የሚኖሩ ያዕቆባውያን ክርስቲያኖች የሠሩት ነው::

በሐዋርያት ቤተ ክርስቲያን ባሕልና ትውፊት መሠረት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከመጀመሪያዎቹ አብያተ ክርስቲያናት አንዷ ስለሆነች የጾም ሥርዓት አላት::

እነዚህም ሰባቱ የጾም ወራት ናቸው::

1ኛ. ዓቢይ ጾም
2ኛ. የሐዋርያት ጾም
3ኛ. የፍልሰታ ጾም
4ኛ. ጾመ ነቢያት
5ኛ. ጾመ ገሀድ
6ኛ. ጾመ ነነዌ
7ኛ. ረቡዕና ዓርብ የተባሉት ናቸው::

እነዚህንም አጽዋማት ሀብተ ወልድና ሥመ ክርስትና በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ያገኘ ምእመን ዕድሜው ከሰባት ዓመት በላይ የሆነ ክርስቲያን መምህረ ንስሐው በበሽታ ምክንያት ካልከለከላቸው በስተቀር ሰባቱንም አጽዋማት  እንዲጾም ሥርዓት ተሠርቶልናል::

  ከነዚህ አጽዋማት መካከል ዛሬ የምንጀምረው ጾም በ4ኛ. ደረጃ ላይ ያስቀመጥነውን ነው:: ይህም ጾም:- ጾመ ነቢያት ይባላል::

ከኅዳር 15 እስከ ታኅሣሥ 28 ቀን ያለው ነው:: ይህን ጾም የምንጾመው ነቢያት በየዘመናቸው ስለመሲህ መምጣት በናፍቆት በመጠባበቅ ይጾሙ ይጸልዩ ስለነበር የእነርሱን አርአያ ተከትለን ከዛሬ ከኅዳር 15 ጀምሮ የክርስቶስን ልደት ከማክበራችን ቀደም ብለን ይህን ጾም እንድንጾም በሐዋርያት ቤተ ክርስቲያን ሥርዓት ተሠርቷል:: በዚህም ምክንያት እንጾማለን::

ጾም ማለት ሰውነት ከሚፈልጋቸው ነገሮች ሁሉ መከልከል ማለት ነው:: ወይም ለሰውነት የሚያምረውን የሚያስጎመዥውን ነገር መተው ማለት ነው::

ሃይማኖት ባለበት ቦታ ሁሉ ጾም አለ:: ጾም ከሃይማኖት ጋር ዘላለማዊ ዝምድና አለው:: ይልቁንም በብሉይ ኪዳን ጾም ከፍተኛ ቦታ አለው::

የብሉይ ኪዳን ነቢያት ከእግዚአብሔር ጋር በሚገናኙበት ወራት እህል ውኃ ባፋቸው አይገባም ነበር:: ዘጸ. 34 -:- 28:: በኃጢአት ብዛት የታዘዘው የእግዚአብሔር መዓት የሚመለሰው ቁጣው የሚበርደው ሕዝቡ በጾም ሲለምኑትና ሲማልዱት ነበር::  ዮና.3-:-5-10::

በአዲስ ኪዳንም ጾም ሰው ሠራሽ ሕግ ሳይሆን ራሱ መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመዋዕለ ሥጋዌው የሥራ መጀመሪያ አድርጎ የሠራው ሕግ ነው:: ማቴ.4-:-2:: ሉቃ.4-:-2::

ስለዚህ ቤተ ክርስቲያናችን በሠራችልን ሥርዓት መሠረት መጾም አለብን:: የምንጾመውም ከመብል ከመጠጥ ብቻ ሳይሆን አባቶቻች "ከመብልና ከመጠጥ ብቻ እንጾማለን አትበሉ ከክፉ ነገር ጭምር ራቁ" እንዳሉን መራቅ ይገባናል::

ስለዚህ በረከት ረድሄት የምናገኝበት ከኃጢአት ከበደል የምንርቅበት ጾም ያድርግልን::

ይቅርታው ቸርነቱ በሁላችን ክርስቲያኖች ላይ ይኑር በአገራችን ኢትዮጵጰያ ላይ ሰላም ያምጣልን ለዘላለሙ አሜን::
🇪🇹@ethiopianorthodoxs⛪️⛪️


Forward from: የደ/መ/ቅዱስ ሚካኤል ካቴድራል ፈለገ ዮርዳኖስ ሰ/ት/ቤት መ/መ ክፍል
የቅዱስ ሚካኤል ዓመታዊ ንግስ ከዋዜማ እስከ ሰርክ ጉባኤ በፈለገ ዮርዳኖስ ሚዲያ በቀጥታ ስስጭት ይጠብቁ።
⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺⁺
ይህ ፈለገ ዮርዳኖስ ሚዲያ ነው Like Shear Follow Subscribe ያድርጉ


Telegram

Facebook

YouTube

Tiktok

Instagram

20 last posts shown.