ቃና ዘገሊላ:-
አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ጥር ዐሥራ ሁለት በዚችም ቀን የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የገሊላ ክፍል በሆነች በቃና በሠርግ ቤት የሠራው የተአምራቱ መታሰቢያ ይደረግ ዘንድ የቤተ ክርስቲያን መምህራን ሥርዓት ሠሩ::
ቅዱስ ወንጌል እንደ ተናገረ ይህች የተአምራቱ መጀመሪያ ናት::
የእመቤታችን ድንግል ማርያም አማላጅነት የተገለጠበት ዕለት ነው:: ውኃውን ለውጦ መዓዛው የሚጥም ጣፋጭ ወይን አድርጎታልና::
በዚህም አሳዳሪው ምስክር ሆነ::
ሙሽራው በጠራው ጊዜ ሰው ሁሉ መልካሙን ጠጅ አስቀድሞ ያጠጣል ከሰከሩም በኋላ ዝቅተኛውን ያጠጣል:: አንተ ግን የተሻለውን ጠጅ ወደ ኋላ አቆይተህ አጠጣህ አለው::
ጌትነቱንም ገለጠ ደቀ መዛሙርቱም አመኑበት::
ዳግመኛም በዚህ ዕለት የከበረ መልአክ የመላእክት አለቃ የሚካኤል የበዓሉ መታሰቢያ ነው::
በዚህች ቀን እስራኤል ወደተባለ ያዕቆብ እግዚአብሔር ልኮታልና ከወንድሙ ከኤሳው ፈርቶ ሳለ አዳነው:: ዮርዳኖስንም አሻግሮ ወደ እናቱ ወንድም ወደ ላባ ሔደ::
እርሱም ሁለቱን ልጆቹን ልያንና ራኄልን አጋባው ከዚህም በኃላ ከብዙ ገንዘብና ከልጆቹ ጋር መንገዱን እየጠረገና እያቀና በሰላም በጤና ወደ አገሩ መለሰው:: ወንድሙ ኤሳውም በፍቅር በሰላም ተቀበለው::
ስለዚህም የሊቀ መላእክት ሚካኤል የበዓሉ መታሰቢያ ነው::
ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በዚህ በከበረ መልአክ አማላጅነት ይማረን::
ለርሱም ከቸር አባቱ መሐሪና ይቅር ባይ ከሆነ መንፈስ ቅዱስም ጋር ምስጋና ይሁን ለዘላለሙ አሜን::
🇪🇹@ethiopianorthodoxs⛪️⛪️
አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ጥር ዐሥራ ሁለት በዚችም ቀን የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የገሊላ ክፍል በሆነች በቃና በሠርግ ቤት የሠራው የተአምራቱ መታሰቢያ ይደረግ ዘንድ የቤተ ክርስቲያን መምህራን ሥርዓት ሠሩ::
ቅዱስ ወንጌል እንደ ተናገረ ይህች የተአምራቱ መጀመሪያ ናት::
የእመቤታችን ድንግል ማርያም አማላጅነት የተገለጠበት ዕለት ነው:: ውኃውን ለውጦ መዓዛው የሚጥም ጣፋጭ ወይን አድርጎታልና::
በዚህም አሳዳሪው ምስክር ሆነ::
ሙሽራው በጠራው ጊዜ ሰው ሁሉ መልካሙን ጠጅ አስቀድሞ ያጠጣል ከሰከሩም በኋላ ዝቅተኛውን ያጠጣል:: አንተ ግን የተሻለውን ጠጅ ወደ ኋላ አቆይተህ አጠጣህ አለው::
ጌትነቱንም ገለጠ ደቀ መዛሙርቱም አመኑበት::
ዳግመኛም በዚህ ዕለት የከበረ መልአክ የመላእክት አለቃ የሚካኤል የበዓሉ መታሰቢያ ነው::
በዚህች ቀን እስራኤል ወደተባለ ያዕቆብ እግዚአብሔር ልኮታልና ከወንድሙ ከኤሳው ፈርቶ ሳለ አዳነው:: ዮርዳኖስንም አሻግሮ ወደ እናቱ ወንድም ወደ ላባ ሔደ::
እርሱም ሁለቱን ልጆቹን ልያንና ራኄልን አጋባው ከዚህም በኃላ ከብዙ ገንዘብና ከልጆቹ ጋር መንገዱን እየጠረገና እያቀና በሰላም በጤና ወደ አገሩ መለሰው:: ወንድሙ ኤሳውም በፍቅር በሰላም ተቀበለው::
ስለዚህም የሊቀ መላእክት ሚካኤል የበዓሉ መታሰቢያ ነው::
ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በዚህ በከበረ መልአክ አማላጅነት ይማረን::
ለርሱም ከቸር አባቱ መሐሪና ይቅር ባይ ከሆነ መንፈስ ቅዱስም ጋር ምስጋና ይሁን ለዘላለሙ አሜን::
🇪🇹@ethiopianorthodoxs⛪️⛪️