ጊዜው የሚጠይቀው አርበኝነት ለሙያ እና ሙያተኛ ክብር መስጠት መሆኑን የስራና ክህሎት ሚኒስትር ገለጹ
- የትርክት መዛባት የቴክኒክና ሙያ ዘርፉን ጎድቶታትል ብለዋል
****
(ኢፕድ)
ጊዜው የሚጠይቀው አርበኝነት ለሙያ እና ሙያተኛ ክብር መስጠት መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ወይዘሮ ሙፈሪሃት ካሚል ገለጹ። የትርክት መዛባት የቴክኒክና ሙያ ዘርፉን እንደጎዳውም ተናግረዋል።
የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ባደረጉት የማጠቃለያ ንግግር እንደገለጹት፤ ክህሎት በህብረት እና በአንድነት ሆነን ሀገር የምንሰራበት መንገድ ነው፡፡
ጊዜው የሚጠይቀው አርበኝነት ለሙያ እና ሙያተኛ ክብር መስጠት መሆኑን ገልጸው፤ ዜጎች ወርቃማ እጃቸውን ብሩህ አዕምሯቸውን ተጠቅመው የሚያደርጉት የችግር ፈቺነት ተግባር አርበኝነት ነው ብለዋል።
አሁን ያለንበት ወቅት የተዛቡ ትርክቶችን የምንጋፈጥበት ሲሆን፤ ከተዘቡ ትርክቶች አንዱ በሙያ እና ሙያተኞች ያለው ግንዛቤ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
የተዘባ ትርክትን ለማስተካከል በኮሚኒኬሽንና በተግባር አሰናስሎ በማስኬድ ተቀራርቦ መስራት እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥተዋል፡፡
አይቻልም፣ አይሆንም አትንካ የሚሉት ጉዳዮች የፈጠራን በር የሚዘጉ በመሆናቸው፤ ልጆችን ከልጅነታቸው ጀምሮ ለፈጠራ ያላቸውን ሀሳብ በመደገፍና በማበረታት ማሳደግ እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡
ምርታማነት ለማሳደግ እና ዘላቂነት ያለው ኢኮኖሚ ለመገንባት ክህሎት መግቢያ በር መሆኑን አመላክተዋል፡፡
ክህሎት ችግር ፈቺና መፍትሄ አመንጪ ነው ያሉት ሚኒስትሯ፤ እያንዳንዱ አምራች ኢንዱስትሪ የሚፈልገውን ብቁ የሰው ኃይል ለመገንባት በትብብር መስራት ይገባል ነው ያሉት፡፡
ኢንዱስትሪዎች የሚፈልጓቸው አዳዲስ የስልጠና መስኮች እንዳሉ ገልጸው፤ ትብብርን በማጠናከር ፍላጎት መር የሰው ሃይል ለማቅረብ ይሰራል ብለዋል፡፡
በልምድ እውቀትና ክህሎት ያገኙ ሰዎች እውቅና የሚያገኙበት ስርዓት በተያዘው ዓመት ይፋ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡
ልንከባከበውና ልንጠብቀው የሚገባ ሀገር በቀል እውቀቶች እንዳሉ ገልጸው፤ 26 የሚደርሱ ሀገር በቀል እውቀቶች ተለይተው ካሪኩለም ተቀርጾላቸዋል ሲሉ አንስተዋል፡፡
በቀጣይም በሀገር በቀል እውቀቶች የማሻሻያ ስራዎች የሚሰራ ሲሆን፤ ይህም ሙያና ሙያተኞችን ለማክበር ጉልህ ሚና አለው ብለዋል፡፡
በሌላ በኩል አዲስና ነባር ቢዝነሶችን ማጣመር እና ስታርት አፖችን ማጠናከር የግድ እንደሚል ጠቁመዋል፡፡
ኢትዮጵያን ከፍ ማድረግ የሚቻለው ስራን በክህሎት ሲመራ በመሆኑ ያለንን እውቀት ያለምን ቁጠባ ሀገር ላይ ኢንቨስት እናድረግ ብለዋል፡፡
ኢትዮጵያ እያሸነፈች ትሻገራለች ምንም ጥርጥር የለውም ሲሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡
በሄለን ወንድምነው
- የትርክት መዛባት የቴክኒክና ሙያ ዘርፉን ጎድቶታትል ብለዋል
****
(ኢፕድ)
ጊዜው የሚጠይቀው አርበኝነት ለሙያ እና ሙያተኛ ክብር መስጠት መሆኑን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ወይዘሮ ሙፈሪሃት ካሚል ገለጹ። የትርክት መዛባት የቴክኒክና ሙያ ዘርፉን እንደጎዳውም ተናግረዋል።
የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪሃት ካሚል ባደረጉት የማጠቃለያ ንግግር እንደገለጹት፤ ክህሎት በህብረት እና በአንድነት ሆነን ሀገር የምንሰራበት መንገድ ነው፡፡
ጊዜው የሚጠይቀው አርበኝነት ለሙያ እና ሙያተኛ ክብር መስጠት መሆኑን ገልጸው፤ ዜጎች ወርቃማ እጃቸውን ብሩህ አዕምሯቸውን ተጠቅመው የሚያደርጉት የችግር ፈቺነት ተግባር አርበኝነት ነው ብለዋል።
አሁን ያለንበት ወቅት የተዛቡ ትርክቶችን የምንጋፈጥበት ሲሆን፤ ከተዘቡ ትርክቶች አንዱ በሙያ እና ሙያተኞች ያለው ግንዛቤ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
የተዘባ ትርክትን ለማስተካከል በኮሚኒኬሽንና በተግባር አሰናስሎ በማስኬድ ተቀራርቦ መስራት እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥተዋል፡፡
አይቻልም፣ አይሆንም አትንካ የሚሉት ጉዳዮች የፈጠራን በር የሚዘጉ በመሆናቸው፤ ልጆችን ከልጅነታቸው ጀምሮ ለፈጠራ ያላቸውን ሀሳብ በመደገፍና በማበረታት ማሳደግ እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡
ምርታማነት ለማሳደግ እና ዘላቂነት ያለው ኢኮኖሚ ለመገንባት ክህሎት መግቢያ በር መሆኑን አመላክተዋል፡፡
ክህሎት ችግር ፈቺና መፍትሄ አመንጪ ነው ያሉት ሚኒስትሯ፤ እያንዳንዱ አምራች ኢንዱስትሪ የሚፈልገውን ብቁ የሰው ኃይል ለመገንባት በትብብር መስራት ይገባል ነው ያሉት፡፡
ኢንዱስትሪዎች የሚፈልጓቸው አዳዲስ የስልጠና መስኮች እንዳሉ ገልጸው፤ ትብብርን በማጠናከር ፍላጎት መር የሰው ሃይል ለማቅረብ ይሰራል ብለዋል፡፡
በልምድ እውቀትና ክህሎት ያገኙ ሰዎች እውቅና የሚያገኙበት ስርዓት በተያዘው ዓመት ይፋ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡
ልንከባከበውና ልንጠብቀው የሚገባ ሀገር በቀል እውቀቶች እንዳሉ ገልጸው፤ 26 የሚደርሱ ሀገር በቀል እውቀቶች ተለይተው ካሪኩለም ተቀርጾላቸዋል ሲሉ አንስተዋል፡፡
በቀጣይም በሀገር በቀል እውቀቶች የማሻሻያ ስራዎች የሚሰራ ሲሆን፤ ይህም ሙያና ሙያተኞችን ለማክበር ጉልህ ሚና አለው ብለዋል፡፡
በሌላ በኩል አዲስና ነባር ቢዝነሶችን ማጣመር እና ስታርት አፖችን ማጠናከር የግድ እንደሚል ጠቁመዋል፡፡
ኢትዮጵያን ከፍ ማድረግ የሚቻለው ስራን በክህሎት ሲመራ በመሆኑ ያለንን እውቀት ያለምን ቁጠባ ሀገር ላይ ኢንቨስት እናድረግ ብለዋል፡፡
ኢትዮጵያ እያሸነፈች ትሻገራለች ምንም ጥርጥር የለውም ሲሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡
በሄለን ወንድምነው