#ዓለም ላይ እርሱን የመሰለ ጠቢብ ፈጽሞ አይነሳም
እስከ ዓለም ፍጻሜ በተሰጠው ጥበብ እርሱን የሚመስል ከሰው ልጅ ወገን እንደማይነሳ ይነገርለታል፡፡ መፍቀሬ ጥበብ፣ ጠቢበ ጠቢባን፣ ንጉሠ እሥራኤል፣ የጽድቅ ነቢየ፣ ሰላማዊው ንጉስ እየተባለ ይጠራል፡፡ አባቱ ታላቁ ነቢይና ንጉሥ ልበ አምላክ ቅዱስ_ዳዊት ነው፡፡ እናቱ ደግሞ ቤርሳቤህ ወይም ቤትስባ ትባላለች፡፡ ከ3ሺ ዓመታት በፊት የተወለደው ቅዱስ ሰሎሞን እስከ 12 ዓመቱ ድረስ በቤተ መንግሥት ከአባቱ ጋር አድጓል፡፡ ቅዱስ ዳዊት 70 ዘመን በሞላው ጊዜ የአካሉን መድከም አይቶ አዶንያስ በጉልበት እነግሣለሁ ቢልም አልተሳካለትም:: እግዚአብሔር ሰሎሞንን መርጧልና ገና በ12 ዓመቱ ነገሠ:: ልበ አምላክ አባቱ ዳዊት ነፍሱ ከሥጋው ከመለየቷ በፊት መከረው:: "ልጄ ሆይ! ልብህን ስጠኝ:: ፈጣሪህንም አምልክ" አለው::
በሰፊው የሚታወቀው ልክ እንደ አባቱ እስራኤልን ለአርባ ዓመት በማስተዳደሩና ታላቁን ቤተ መውደስ በመገንባቱ ነው፡፡ እንደ ነገሠም በገባዖን ለእግዚአብሔር መስዋዕትን አቀረበ፡፡ ጌታም ተገልጾ "ምን ትፈልጋለህ?" አለው፡፡ ሰሎሞንም እንደ አባቱ ማስተዋልን፣ ልቡናን ለመነ፡፡ ጌታም ደስ ስለተሰኘ "ከአንተ በፊትም ሆነ ከአንተም በኋላ እንዳንተ ያለ ጠቢብና ባለጸጋ ሰው አይኖርም" ብሎታል፡፡ ግሩም በሆነ ፍርዱ፣ በልዩ ጥበቡ ስለርሱ የሰማው ዓለም ሁሉ ተገዛለት፡፡ የእኛዋ ታላቅ ንግስተ ሳባ /ማክዳም/ ትፈትነው ዘንድ ሒዳ ምኒልክን ጸንሳ መምጣቷ በሁዋላም ለታቦተ ጽዮንና ሥርዓተ ኦሪት መምጣት ምክንያት ሆኗል፡፡ ቅዱስ ሰሎሞን በተለይ ስለ ድንግል ማርያም የጻፈው ምስጋና እንደ አባቱ ቅዱስ ዳዊት ዛሬም ድረስ በቅድስት ቤተክርስቲያንችን ጥቅም ላይ ይውላል፡፡
ንጉስ ሰሎሞን ድንግል ማርያም ከእርሱ ዘር እንደምትወለድ ሲነገረው፣ አንድም ሥጋ ለባሽ ሰው ነውና ሁለተኛም ከብዙ ሴቶች መካከል ከአንዷ እመ ብርሃን ትገኛለች መስሎት መፍቀሬ አንስት ሆነ፡፡ ከአሕዛብ ወገን ከፈርዖን ልጅ ጋር በመወዳጀቱም ለጣዖት ሰግዶ እግዚአብሔርን ቢያሳዝንም በራዕይ ተገልጦ "ስለ ወዳጄ ስለ ዳዊት ስል በአንተ ላይ ክፉን አላደርግም" አለው፡፡ ታላቁ ነቢይ ሰሎሞን ይህንን ሲሰማ ወደ ልቡ በመመለስ ማቅ ለብሶ፣ አመድ ነስንሶ በፍጹም ልቡ ንስሃ በመግባቱ ጌታችን ንስሃውን ተቀበለው፡፡ አሁን ድረስ ድንቅ ጥበብ የያዙትን መኃልየ መኃልይ ዘሰሎሞን፣ መጽሐፈ ጥበብ፣ መጽሐፈ ምሳሌ፣ መጽሐፈ ተግሣጽ፣ መጽሐፈ መክብብ የተባሉ አምስት መጻሕፍት ገለጸለት፡፡
“ወዳጄ ሆይ፥ እነሆ ውብ ነሽ፤ እነሆ አንቺ ውብ ነሽ፤ ዓይኖችሽም እንደ ርግቦች ናቸው።” ናቸው ሲል ቅድስት ድንግል ማርያምን አመስግኗታል፡፡ ዘመናትን መዋጀት እንደሚገባ ሲነግረንም በተለይ ትልቁን የወጣትነት ጊዜ በጥበብ ቃላት ሲገልጸው “የጭንቀት ቀን ሳይመጣ በጉብዝናህ ወራት ፈጣሪህን አስብ፡፡ ደስ አያሰኙም የምትላቸውም ዓመታት ሳይደርሱ፤ ፀሐይ፣ ጨረቃና ከዋክብትም ሳይጨልሙ፤ አፈርም ወደ ነበረበት ምድር ሳይመለስ፤ ነፍስም ወደ ሰጠው ወደ እግዚአብሔር ሳይመለስ ፈጣሪህን አስብ፡፡” ይለናል፡፡ በመጽሐፈ ምክብብም በዚህ ዓለም ምንም ብንሰበስብ እግዚአብሔር ከሌለበት እንደማይረባ ሲነግረን "ከንቱ፣ ከንቱ፣ ሁሉ ከንቱ ነው" ይላል:: ጠቢብ፣ ነቢይና ንጉስ ሰሎሞን በዚህች ዕለት በ52 ዓመቱ ዐርፎ ወደ ፈጣሪው መሔዱን “ድርሳነ መስቀል” ላይ ሰፍሮ ይገኛል፡፡
በገዳማዊ ኑሮ ያሉትን እየረዳንና በዓታቸውን እያጸናን የበረከታቸው ተሳታፊ እንሁን፡፡
ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444
እስከ ዓለም ፍጻሜ በተሰጠው ጥበብ እርሱን የሚመስል ከሰው ልጅ ወገን እንደማይነሳ ይነገርለታል፡፡ መፍቀሬ ጥበብ፣ ጠቢበ ጠቢባን፣ ንጉሠ እሥራኤል፣ የጽድቅ ነቢየ፣ ሰላማዊው ንጉስ እየተባለ ይጠራል፡፡ አባቱ ታላቁ ነቢይና ንጉሥ ልበ አምላክ ቅዱስ_ዳዊት ነው፡፡ እናቱ ደግሞ ቤርሳቤህ ወይም ቤትስባ ትባላለች፡፡ ከ3ሺ ዓመታት በፊት የተወለደው ቅዱስ ሰሎሞን እስከ 12 ዓመቱ ድረስ በቤተ መንግሥት ከአባቱ ጋር አድጓል፡፡ ቅዱስ ዳዊት 70 ዘመን በሞላው ጊዜ የአካሉን መድከም አይቶ አዶንያስ በጉልበት እነግሣለሁ ቢልም አልተሳካለትም:: እግዚአብሔር ሰሎሞንን መርጧልና ገና በ12 ዓመቱ ነገሠ:: ልበ አምላክ አባቱ ዳዊት ነፍሱ ከሥጋው ከመለየቷ በፊት መከረው:: "ልጄ ሆይ! ልብህን ስጠኝ:: ፈጣሪህንም አምልክ" አለው::
በሰፊው የሚታወቀው ልክ እንደ አባቱ እስራኤልን ለአርባ ዓመት በማስተዳደሩና ታላቁን ቤተ መውደስ በመገንባቱ ነው፡፡ እንደ ነገሠም በገባዖን ለእግዚአብሔር መስዋዕትን አቀረበ፡፡ ጌታም ተገልጾ "ምን ትፈልጋለህ?" አለው፡፡ ሰሎሞንም እንደ አባቱ ማስተዋልን፣ ልቡናን ለመነ፡፡ ጌታም ደስ ስለተሰኘ "ከአንተ በፊትም ሆነ ከአንተም በኋላ እንዳንተ ያለ ጠቢብና ባለጸጋ ሰው አይኖርም" ብሎታል፡፡ ግሩም በሆነ ፍርዱ፣ በልዩ ጥበቡ ስለርሱ የሰማው ዓለም ሁሉ ተገዛለት፡፡ የእኛዋ ታላቅ ንግስተ ሳባ /ማክዳም/ ትፈትነው ዘንድ ሒዳ ምኒልክን ጸንሳ መምጣቷ በሁዋላም ለታቦተ ጽዮንና ሥርዓተ ኦሪት መምጣት ምክንያት ሆኗል፡፡ ቅዱስ ሰሎሞን በተለይ ስለ ድንግል ማርያም የጻፈው ምስጋና እንደ አባቱ ቅዱስ ዳዊት ዛሬም ድረስ በቅድስት ቤተክርስቲያንችን ጥቅም ላይ ይውላል፡፡
ንጉስ ሰሎሞን ድንግል ማርያም ከእርሱ ዘር እንደምትወለድ ሲነገረው፣ አንድም ሥጋ ለባሽ ሰው ነውና ሁለተኛም ከብዙ ሴቶች መካከል ከአንዷ እመ ብርሃን ትገኛለች መስሎት መፍቀሬ አንስት ሆነ፡፡ ከአሕዛብ ወገን ከፈርዖን ልጅ ጋር በመወዳጀቱም ለጣዖት ሰግዶ እግዚአብሔርን ቢያሳዝንም በራዕይ ተገልጦ "ስለ ወዳጄ ስለ ዳዊት ስል በአንተ ላይ ክፉን አላደርግም" አለው፡፡ ታላቁ ነቢይ ሰሎሞን ይህንን ሲሰማ ወደ ልቡ በመመለስ ማቅ ለብሶ፣ አመድ ነስንሶ በፍጹም ልቡ ንስሃ በመግባቱ ጌታችን ንስሃውን ተቀበለው፡፡ አሁን ድረስ ድንቅ ጥበብ የያዙትን መኃልየ መኃልይ ዘሰሎሞን፣ መጽሐፈ ጥበብ፣ መጽሐፈ ምሳሌ፣ መጽሐፈ ተግሣጽ፣ መጽሐፈ መክብብ የተባሉ አምስት መጻሕፍት ገለጸለት፡፡
“ወዳጄ ሆይ፥ እነሆ ውብ ነሽ፤ እነሆ አንቺ ውብ ነሽ፤ ዓይኖችሽም እንደ ርግቦች ናቸው።” ናቸው ሲል ቅድስት ድንግል ማርያምን አመስግኗታል፡፡ ዘመናትን መዋጀት እንደሚገባ ሲነግረንም በተለይ ትልቁን የወጣትነት ጊዜ በጥበብ ቃላት ሲገልጸው “የጭንቀት ቀን ሳይመጣ በጉብዝናህ ወራት ፈጣሪህን አስብ፡፡ ደስ አያሰኙም የምትላቸውም ዓመታት ሳይደርሱ፤ ፀሐይ፣ ጨረቃና ከዋክብትም ሳይጨልሙ፤ አፈርም ወደ ነበረበት ምድር ሳይመለስ፤ ነፍስም ወደ ሰጠው ወደ እግዚአብሔር ሳይመለስ ፈጣሪህን አስብ፡፡” ይለናል፡፡ በመጽሐፈ ምክብብም በዚህ ዓለም ምንም ብንሰበስብ እግዚአብሔር ከሌለበት እንደማይረባ ሲነግረን "ከንቱ፣ ከንቱ፣ ሁሉ ከንቱ ነው" ይላል:: ጠቢብ፣ ነቢይና ንጉስ ሰሎሞን በዚህች ዕለት በ52 ዓመቱ ዐርፎ ወደ ፈጣሪው መሔዱን “ድርሳነ መስቀል” ላይ ሰፍሮ ይገኛል፡፡
በገዳማዊ ኑሮ ያሉትን እየረዳንና በዓታቸውን እያጸናን የበረከታቸው ተሳታፊ እንሁን፡፡
ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ ማር ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት ገዳም
ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391
ወይም
አቢሲኒያ ባንክ
141029444
የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444