ጸጸት የሚያስከትለው የሥነ-ልቦና ጫና!
የቅርብ ዘመዱን መታመም የሰማው አቤነዘር ሄዶ መጠየቅ እንዳለበት ያምናል፤ ነገር ግን በወቅቱ የተጠመደበት ስራ ፋታ ሊሰጠው አልቻለም።
አቤነዘር አስፋው ከአክስቱ ልጅ ጋር የቅርብ ዘመድ ብቻ አልነበሩም የቅርብ ጓደኛሞችም እንጂ። ነገር ግን ከዛሬ ነገ ሲመቻችልኝ እጎበኘዋለሁ ሲል የነበረው አቤነዘር ሳያስበው አስደንጋጭ መርዶ ሰማ።
ሳይታሰብ ጓደኛ እና የአክስቱን ልጅ በሞት ያጣው አቤነዘር “ያኔ እንደ ምንም ሄጄ አለመጠየቄ አሁንም ድረስ ይፀፅተኛል” በማለት ይናገራል።
እንደ አቤነዘር አይነት ወይም በተለየ መልኩ በሚፈጠሩ ክስተቶች በርካታ ሰዎች ጸጸት ውስጥ ሲገቡ ይስተዋላል።
ጸጸት በተደረገ እና ባለፈ ጉዳይ ላይ ትክክል አልነበርኩም ከሚል የጥፋተኝነት ስሜት ጋር ተያይዞ የሚመጣ ሰውኛ የሆነ ስሜት ነው።
ፀፀት ውስጥ ለረዥም ጊዜ መቆየት ከፍተኛ ለሆነ የድባቴ ስሜት የሚያጋልጥ እና ነገን እንዳያዩ የሚያደርግ ነው።
ሰዎች ካለፈው ስህተት ከመማር ይልቅ ዛሬም ድረስ የጸጸት እስረኛ ሲሆኑ እና ከራሳቸው ጋር ያላቸውን ግንኙነት ጤናማ በሆነ መልኩ ለማስቀጠል ከተቸገሩ ወደ ሥነ-ልቦና ችግር አድጓል ሊባል ይችላል።
ከጸጸት ስሜት ለመውጣትም ያጋጠሙ ችግሮችን እንደመልካም አጋጣሚ በመቁጠር የተሻለ ሰው ለመሆን እና በዙሪያችን ላሉ ሰዎች የሚጠቅም ነገር ለማድረግ መነሳሻ ሊሆነን ይገባል።
እንዲሁም በሰራሁት ስህተት ምክንያት እኔ መጥፎ ሰው ነኝ ብሎ ከመወሰን ይልቅ የሰራነውን ስህተት ተቀብሎ ትምህርት መውሰድ ጠቃሚ ነው።
ኤርሚያስ ኪሮስ (ካውንስሊንግ ሳይኮሎጂስት)
Via: WMCC
@melkam_enaseb
የቅርብ ዘመዱን መታመም የሰማው አቤነዘር ሄዶ መጠየቅ እንዳለበት ያምናል፤ ነገር ግን በወቅቱ የተጠመደበት ስራ ፋታ ሊሰጠው አልቻለም።
አቤነዘር አስፋው ከአክስቱ ልጅ ጋር የቅርብ ዘመድ ብቻ አልነበሩም የቅርብ ጓደኛሞችም እንጂ። ነገር ግን ከዛሬ ነገ ሲመቻችልኝ እጎበኘዋለሁ ሲል የነበረው አቤነዘር ሳያስበው አስደንጋጭ መርዶ ሰማ።
ሳይታሰብ ጓደኛ እና የአክስቱን ልጅ በሞት ያጣው አቤነዘር “ያኔ እንደ ምንም ሄጄ አለመጠየቄ አሁንም ድረስ ይፀፅተኛል” በማለት ይናገራል።
እንደ አቤነዘር አይነት ወይም በተለየ መልኩ በሚፈጠሩ ክስተቶች በርካታ ሰዎች ጸጸት ውስጥ ሲገቡ ይስተዋላል።
ጸጸት በተደረገ እና ባለፈ ጉዳይ ላይ ትክክል አልነበርኩም ከሚል የጥፋተኝነት ስሜት ጋር ተያይዞ የሚመጣ ሰውኛ የሆነ ስሜት ነው።
ፀፀት ውስጥ ለረዥም ጊዜ መቆየት ከፍተኛ ለሆነ የድባቴ ስሜት የሚያጋልጥ እና ነገን እንዳያዩ የሚያደርግ ነው።
ሰዎች ካለፈው ስህተት ከመማር ይልቅ ዛሬም ድረስ የጸጸት እስረኛ ሲሆኑ እና ከራሳቸው ጋር ያላቸውን ግንኙነት ጤናማ በሆነ መልኩ ለማስቀጠል ከተቸገሩ ወደ ሥነ-ልቦና ችግር አድጓል ሊባል ይችላል።
ከጸጸት ስሜት ለመውጣትም ያጋጠሙ ችግሮችን እንደመልካም አጋጣሚ በመቁጠር የተሻለ ሰው ለመሆን እና በዙሪያችን ላሉ ሰዎች የሚጠቅም ነገር ለማድረግ መነሳሻ ሊሆነን ይገባል።
እንዲሁም በሰራሁት ስህተት ምክንያት እኔ መጥፎ ሰው ነኝ ብሎ ከመወሰን ይልቅ የሰራነውን ስህተት ተቀብሎ ትምህርት መውሰድ ጠቃሚ ነው።
ኤርሚያስ ኪሮስ (ካውንስሊንግ ሳይኮሎጂስት)
Via: WMCC
@melkam_enaseb