📣‹‹ጣሊያን በጨረቃ ሲገሰግስ አድሮ እሰፈሬ ድረስ መጥቶ ገጠመኝ፡፡ አምላከ ኃያላን ረድቶኝ ፈጀሁት፡፡ ደስ ብሎኛል ደስ ይበልህ!››
ዳግማዊ አፄ ምኒልክ፣ ባሕር ተሻግሮ ድንበር አቋርጦ የመጣውን ወራሪውን የጣሊያን ሠራዊት የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም. በዓድዋ ጦርነት ድል ማድረጋቸውን አስመልክቶ በወሩ መጋቢት 23 ቀን 1888 ዓ.ም. ለፈረንሣዊው ሙሴ ሞንዶን ከጻፉለት የምሥራች ደብዳቤ የተገኘ ኃይለ ቃል ነው፡፡
ከ129 ዓመታት በፊት የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም.፣ (በአውሮፓዎቹ ቀመር ማርች 1 ቀን 1896) ኢትዮጵያ የነጩን ዓለም ያናወጠ፣ ለጥቁር ሕዝቦች ሞገስ የሆነውን የዓድዋ ጦርነት በጣሊያን ወራሪ ሠራዊት በድል የተወጣችበት ዕለት ነበር፡፡
ይህንን የ19ኛው ምዕት ዓመት ታሪካዊ ገድል ነበር ጆርጅ በርክሌ በመጣጥፉ ያንፀባረቀውና “አጤ ምኒልክ” ከተሰኘው መጽሐፍ ላይ ያሠፈረው፡፡
ይኸው የዓድዋ ጦርነት ድል 129ኛ ዓመት እንደወትሮው በብሔራዊ በዓልነት ዛሬ የካቲት 23 ቀን 2017 ዓ.ም. ከዓድዋ እስከ አዲስ አበባ አገሪቱን አቅፎ እየተከበረ ይገኛል፡፡
@seledadotio
@seledadotio
ዳግማዊ አፄ ምኒልክ፣ ባሕር ተሻግሮ ድንበር አቋርጦ የመጣውን ወራሪውን የጣሊያን ሠራዊት የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም. በዓድዋ ጦርነት ድል ማድረጋቸውን አስመልክቶ በወሩ መጋቢት 23 ቀን 1888 ዓ.ም. ለፈረንሣዊው ሙሴ ሞንዶን ከጻፉለት የምሥራች ደብዳቤ የተገኘ ኃይለ ቃል ነው፡፡
ከ129 ዓመታት በፊት የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም.፣ (በአውሮፓዎቹ ቀመር ማርች 1 ቀን 1896) ኢትዮጵያ የነጩን ዓለም ያናወጠ፣ ለጥቁር ሕዝቦች ሞገስ የሆነውን የዓድዋ ጦርነት በጣሊያን ወራሪ ሠራዊት በድል የተወጣችበት ዕለት ነበር፡፡
ይህንን የ19ኛው ምዕት ዓመት ታሪካዊ ገድል ነበር ጆርጅ በርክሌ በመጣጥፉ ያንፀባረቀውና “አጤ ምኒልክ” ከተሰኘው መጽሐፍ ላይ ያሠፈረው፡፡
ይኸው የዓድዋ ጦርነት ድል 129ኛ ዓመት እንደወትሮው በብሔራዊ በዓልነት ዛሬ የካቲት 23 ቀን 2017 ዓ.ም. ከዓድዋ እስከ አዲስ አበባ አገሪቱን አቅፎ እየተከበረ ይገኛል፡፡
@seledadotio
@seledadotio