የሶማሊላንድ ፖሊስ ህገ-ወጥ ያላቸውን የኢትዮጵያ ስደተኞችን የማባረር ዘመቻ ጀምሯል።
እሁድ ጠዋት የፖሊስ ተሽከርካሪዎች በሐርጌሳ ገበያ አካባቢዎች ሲዞሩና በህገ-ወጥ መንገድ የሚገኙ ኢትዮጵያውያንን ሲይዙ ታይተዋል።
ብዙ ኢትዮጵያውያን በሶማሊላንድ በስደተኞች ካርድ፣ በቪዛ ወይም በስራ ፈቃድ ቢኖሩም፣ በየዓመቱ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ሰዎች ወደ ሶማሌላንድ በህገ-ወጥ መንገድ ይገባሉ።
የሶማሊላንድ ባለስልጣናት አዲስ ስለተጀመረው እንቅስቃሴ በይፋ የሰጡት አስተያየት የለም።
የሶማሊላንድ ፖሊስ ህገ-ወጥ የኢትዮጵያ ስደተኞችን ለማባረር ዘመቻ የጀመረው የፑንትላንድ ባለስልጣናት ከ1,000 በላይ ኢትዮጵያውያን ዜጎችን ከጋሮዌ እና ቦሳሶ ከተሞች ካባረሩ ከጥቂት ሳምንታት በኋላ ነው።
የፑንትላንድ መንግስት በአል-ሚስካት ተራሮች ውስጥ ከሚንቀሳቀሰው የአይሲስ ቡድን ጋር አንዳንድ የውጭ ዜጎች እንደተቀላቀሉ በሚገልጹ ሪፖርቶች ምክንያት የጸጥታ ስጋትን በምክንያትነት በመጥቀስ ህገ-ወጥ ስደተኞችን ላይ ያለውን እርምጃ ማጠናከሩን ገልጿል።
Source : Hiiraan Online
@tikvahethmagazine
እሁድ ጠዋት የፖሊስ ተሽከርካሪዎች በሐርጌሳ ገበያ አካባቢዎች ሲዞሩና በህገ-ወጥ መንገድ የሚገኙ ኢትዮጵያውያንን ሲይዙ ታይተዋል።
ብዙ ኢትዮጵያውያን በሶማሊላንድ በስደተኞች ካርድ፣ በቪዛ ወይም በስራ ፈቃድ ቢኖሩም፣ በየዓመቱ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ሰዎች ወደ ሶማሌላንድ በህገ-ወጥ መንገድ ይገባሉ።
የሶማሊላንድ ባለስልጣናት አዲስ ስለተጀመረው እንቅስቃሴ በይፋ የሰጡት አስተያየት የለም።
የሶማሊላንድ ፖሊስ ህገ-ወጥ የኢትዮጵያ ስደተኞችን ለማባረር ዘመቻ የጀመረው የፑንትላንድ ባለስልጣናት ከ1,000 በላይ ኢትዮጵያውያን ዜጎችን ከጋሮዌ እና ቦሳሶ ከተሞች ካባረሩ ከጥቂት ሳምንታት በኋላ ነው።
የፑንትላንድ መንግስት በአል-ሚስካት ተራሮች ውስጥ ከሚንቀሳቀሰው የአይሲስ ቡድን ጋር አንዳንድ የውጭ ዜጎች እንደተቀላቀሉ በሚገልጹ ሪፖርቶች ምክንያት የጸጥታ ስጋትን በምክንያትነት በመጥቀስ ህገ-ወጥ ስደተኞችን ላይ ያለውን እርምጃ ማጠናከሩን ገልጿል።
Source : Hiiraan Online
@tikvahethmagazine