በአማራ ክልል የዳኞች ያለመከሰስ መብት እንዲጠበቅ ባለመደረጉ ዳኞች ለተለያዩ ችግሮች እየተጋለጡ ነው ተባለ።
የዳኞች ያለመከሰስ መብት በአማራ ክልል ምክር ቤት ቢቀርብም የዳኞችን መብት የሚያስጠብቅ ሕግ አለመውጣቱ ተገልጿል፡፡
ጉዳዩ ሁለት ጊዜ ያህል ለክልሉ ምክር ቤት ቢቀርብም በአዋጅ እስካሁን አለመጽደቁም ተነስቷል፡፡
ከኢትዮ ኤፍ ኤም ጋር ቆይታ የነበራቸው የህግ ባለሞያው አቶ ጥጋቡ ደሳለኝ፤ ክልሎች የፌድራሉን ህገ መንግስትን ተከትለው ህግ እንዲያወጡ በማንሳት አንዱ ክልል ፀድቆ ሌላው ጋር አለመፅደቁ ጥያቄ የሚያስነሳ ነው ብለዋል።
የህግ ባለሞያው አቶ ጥጋቡ ይህ ችግር እንዲስተካከል የዳኞች ማህበር ብቻ ሳይሆን ሌሎች ባለድርሻ አካላት በተለይም ጠቅላይ ፍርድ ቤት እና የክልሉ የዳኞች አስተዳደር ጉባኤ በስፋት መጠየቅ ይገባቸዋል ብለዋል፡፡
አቶ ጥጋቡ ጠንካራ የዳኝነት ተቋም እንዲኖርና ሕዝቡ በፍርድ ቤቶችና በዳኞች ላይ እምነት እንዲኖረው፣ በአንድ አገር ውስጥ የዳኝነት ነፃነት መስፈንና መረጋገጥ አለበትም ብለዋል።
ከዚህ ቀደም የአማራ ክልል ዳኞች ማህበር የዳኞች እስር ችግሩ ሲንከባለል የመጣ ቢሆንም በ2017 ዓ.ም ግን የከፋ ሆኗል ማለቱ ይታወሳል።
https://t.me/voa_amharic1
https://t.me/voa_amharic1
የዳኞች ያለመከሰስ መብት በአማራ ክልል ምክር ቤት ቢቀርብም የዳኞችን መብት የሚያስጠብቅ ሕግ አለመውጣቱ ተገልጿል፡፡
ጉዳዩ ሁለት ጊዜ ያህል ለክልሉ ምክር ቤት ቢቀርብም በአዋጅ እስካሁን አለመጽደቁም ተነስቷል፡፡
ከኢትዮ ኤፍ ኤም ጋር ቆይታ የነበራቸው የህግ ባለሞያው አቶ ጥጋቡ ደሳለኝ፤ ክልሎች የፌድራሉን ህገ መንግስትን ተከትለው ህግ እንዲያወጡ በማንሳት አንዱ ክልል ፀድቆ ሌላው ጋር አለመፅደቁ ጥያቄ የሚያስነሳ ነው ብለዋል።
የህግ ባለሞያው አቶ ጥጋቡ ይህ ችግር እንዲስተካከል የዳኞች ማህበር ብቻ ሳይሆን ሌሎች ባለድርሻ አካላት በተለይም ጠቅላይ ፍርድ ቤት እና የክልሉ የዳኞች አስተዳደር ጉባኤ በስፋት መጠየቅ ይገባቸዋል ብለዋል፡፡
አቶ ጥጋቡ ጠንካራ የዳኝነት ተቋም እንዲኖርና ሕዝቡ በፍርድ ቤቶችና በዳኞች ላይ እምነት እንዲኖረው፣ በአንድ አገር ውስጥ የዳኝነት ነፃነት መስፈንና መረጋገጥ አለበትም ብለዋል።
ከዚህ ቀደም የአማራ ክልል ዳኞች ማህበር የዳኞች እስር ችግሩ ሲንከባለል የመጣ ቢሆንም በ2017 ዓ.ም ግን የከፋ ሆኗል ማለቱ ይታወሳል።
https://t.me/voa_amharic1
https://t.me/voa_amharic1