ኤርትራ ለጄኔራል ፃድቃን ገብረትንሳኤ መልስ ሰጠች፡፡
ጄኔራል ፃድቃን በትላንትናው እለት በኢትዮጵያና በኤርትራ መካከል ጦርነት ሊነሳ ጫፍ ላይ እንደደረሰ ገልፀው በዚህም ትግራይ የጦር አውድማ መሆን እንደሌለባት ማስታወቃቸውን መዘገባችን ይታወሳል፡፡
ለዚህ አስተያየት የኤርትራ ማስታወቂያ ሚኒስትር አቶ የማነ ገብረመስቀል ዛሬ መልስ ሰጥተዋል፡፡
በመልሳቸው ያሰፈሩት የመጀመሪያው ነጥብ ጄኔራል ፃድቃን ከዚህ ቀደም ኤርትራን የመውረር አጀንዳ ደጋፊ መሆናቸውን ነው፡፡
በተለይም አሰብን በሀይል ወደኢትዮጵያ ስለመጠቅለል ጄኔራሉ በራሳቸው አንደበት የተናገሩትን አውስተዋል፡፡
በሁለተኝነት ያነሱት ነጥብ ደግሞ የኢትዮጵያና ኤርትራ ግንኙነት ጥሩ በነበረበት ወቅት ጭምር ኢትዮጵያ በአሰብ ላይ ይገባኛል ጥያቄ እንድታነሳ በሚስጥር ሲቀሰቅሱ እንደነበር ነው፡፡
አቶ የማነ ሲቀጥሉም "በኢትዮጵያና ኤርትራ ጦርነት ወቅት ኢትዮጵያ አሰብን ለመጠቅለል እድሉን ባለመጠቀሟ ጄኔራል ፃድቃን ተቆጭተዋል" ያሉ ሲሆን አሁን ደግሞ ሁለቱ አገራት የጦርነት ዝግጅት እንደጨረሱ አስመስለው መግለፃቸውን ጠቅሰዋል፡፡
የዚህ የትላንቱ አስተያየታቸው መነሻም የአዞ እንባ በማንባት የጦርነት አጀንዳ መቀስቀስ መሆኑን የገለፁት አቶ የማነ ይህም በኤርትራና በጎረቤቶቿ መካከል ጠላትነትን የመፍጠር ስሌት አካል ነው ብለዋል፡፡
https://t.me/voa_amharic1
https://t.me/voa_amharic1
ጄኔራል ፃድቃን በትላንትናው እለት በኢትዮጵያና በኤርትራ መካከል ጦርነት ሊነሳ ጫፍ ላይ እንደደረሰ ገልፀው በዚህም ትግራይ የጦር አውድማ መሆን እንደሌለባት ማስታወቃቸውን መዘገባችን ይታወሳል፡፡
ለዚህ አስተያየት የኤርትራ ማስታወቂያ ሚኒስትር አቶ የማነ ገብረመስቀል ዛሬ መልስ ሰጥተዋል፡፡
በመልሳቸው ያሰፈሩት የመጀመሪያው ነጥብ ጄኔራል ፃድቃን ከዚህ ቀደም ኤርትራን የመውረር አጀንዳ ደጋፊ መሆናቸውን ነው፡፡
በተለይም አሰብን በሀይል ወደኢትዮጵያ ስለመጠቅለል ጄኔራሉ በራሳቸው አንደበት የተናገሩትን አውስተዋል፡፡
በሁለተኝነት ያነሱት ነጥብ ደግሞ የኢትዮጵያና ኤርትራ ግንኙነት ጥሩ በነበረበት ወቅት ጭምር ኢትዮጵያ በአሰብ ላይ ይገባኛል ጥያቄ እንድታነሳ በሚስጥር ሲቀሰቅሱ እንደነበር ነው፡፡
አቶ የማነ ሲቀጥሉም "በኢትዮጵያና ኤርትራ ጦርነት ወቅት ኢትዮጵያ አሰብን ለመጠቅለል እድሉን ባለመጠቀሟ ጄኔራል ፃድቃን ተቆጭተዋል" ያሉ ሲሆን አሁን ደግሞ ሁለቱ አገራት የጦርነት ዝግጅት እንደጨረሱ አስመስለው መግለፃቸውን ጠቅሰዋል፡፡
የዚህ የትላንቱ አስተያየታቸው መነሻም የአዞ እንባ በማንባት የጦርነት አጀንዳ መቀስቀስ መሆኑን የገለፁት አቶ የማነ ይህም በኤርትራና በጎረቤቶቿ መካከል ጠላትነትን የመፍጠር ስሌት አካል ነው ብለዋል፡፡
https://t.me/voa_amharic1
https://t.me/voa_amharic1