ኢትዮጵያዊያንና ወረርሽኝ
ከ101 ዓመት በፊት ዓለምን ከወደ ስፔን በመነሳት አሸብሮ፣ከአውሮፓ ህዝብ ሲሶውን(1/3ኛውን) ረምርሞ፣ ከአስር ወራት በሗላ በቅድስቷ አገር ኢትዮጵያ የደረሰው የህዳር በሽታ ዘጠኝ ሺህ አዲስ አበቤን እና 40 ሺህ ኢትዮጵያዊያንን ቀባሪ አሳጥቶ ፈጃቸው።
በተለይ ህዳር 12 ቀን 1911 ዓ.ም በመዲናይቱ አዲስ አበባ ለአስከሬን መቅበሪያነት የተቆፈረ ጉድጓድ የተሰረቀበት፣ጅብ የሰው ሬሳ ለመብላት አቃቂር ያወጣበት እንደነበር መርስኤ ኀዘን ወልደ ቂርቆስ "የ20ኛው ክፍለ ዘመን መባቻ፤ካየሁትና ከሰማሁት" በሚል ርዕስ በፃፉት ውድ የታሪክ ማስታወሻቸው ተከትቧል።
የዚያን ጊዜ በሽታው ወደ ኢትዮጵያ ምድር በንፋስ አማካኝነት የመጣ ሲሆን ጥበበኛው የአገሬ ሰውም በብዙ ዘመን ልምዱ ባካበተው እውቀቱ በመታገል ለ አዕላፍ(ሚሊዮን) የዓለም ህዝብ ህይወት መቀጠፍ ምክንያት የሆነውን ጉንፋን መሠል ወረርሽኝ ተዋግቶ አሸንፎታል።
አዲስ አድማስ ጋዜጣ በ2006ዓ.ም ህዳር ወር ይዞት በወጣው ፅሁፍ እንደሚያትተው በወቅቱ የመንዝ ተወላጅ የነበሩት ወይዘሮ ዘነበች የተባሉ የባህል መድሃኒት አዋቂ ለአዲስ አበቤ ያስተማሩት የአበሻ አረቄን መጠጣት እና ቀይ ሽንኩርት በየ ቤቱ እንዲሁም በእየ አንገቱ ማንጠልጠል በፈረንሳይ ቆንሲል በኩል ሳይቀር ተኮርጆ ወደ አውሮፓ በመላክ "የሠለጠነውን" ዓለም ለመፈወስ በቅቷል።
የሴትዮይቱ ከልምድ የተገኘ መድሃኒት በተለይም አረቄው ከነበረበት በጠርሙስ 10 ሳንቲም ዋጋ ወደ ሰባት ብር አድጎ ሜዲትራኒያንን ተሻግሮ አውሮፓዊያኑን አልቦ(ዜሮ) ከመቅረት ታድጓቸዋል።
ኢትዮጵያዊያን ከዚህም በተጨማሪ የደረቀን የበሬ ቆዳ በታማሚው አካባቢ በማንኳኳትና ጠብ መንጃ ወደ ጆሮው አስጠግቶ በመተኮስ በሽታውን አስደንግጦ ለማባረር ተሳክቶላቸዋል፤ይሄንን ስልት እስካሁን ድረስ ጥቅም ላይ የሚያውል ማህበረሰብ እንዳለ እኔም አውቃለሁ---ጎጃም ሰው ሊሞት ጥቂት ሲቀረው በጠብመንጃ ተኩስ ለማንቃት የመጨረሻ ሙከራ ይደረጋል።
እንግዲህ እኛ እንዲህ ያሉ ከላይኛው ጠቢብ የተላከ ጥበብ ያለን ልዑላን ህዝቦች ነንና ዛሬ መቶ ሰው ይዞ ሁለት(ለዚያውም በዕድሜ የገፉትን) ለሚገድል በሽታ ብለን ከሰውነት ጣሪያ ወርደን ርስ በእርስ እንዳንፈራራ ይሁን።
መጠንቀቅና መሳቀቅን ማመጣጠን ከቻልን ኮሮናን እናሸንፈዋለን።
8335 እንዳይረሳ
።፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
ይቆየን!
@wegoch
@wegoch
ከ101 ዓመት በፊት ዓለምን ከወደ ስፔን በመነሳት አሸብሮ፣ከአውሮፓ ህዝብ ሲሶውን(1/3ኛውን) ረምርሞ፣ ከአስር ወራት በሗላ በቅድስቷ አገር ኢትዮጵያ የደረሰው የህዳር በሽታ ዘጠኝ ሺህ አዲስ አበቤን እና 40 ሺህ ኢትዮጵያዊያንን ቀባሪ አሳጥቶ ፈጃቸው።
በተለይ ህዳር 12 ቀን 1911 ዓ.ም በመዲናይቱ አዲስ አበባ ለአስከሬን መቅበሪያነት የተቆፈረ ጉድጓድ የተሰረቀበት፣ጅብ የሰው ሬሳ ለመብላት አቃቂር ያወጣበት እንደነበር መርስኤ ኀዘን ወልደ ቂርቆስ "የ20ኛው ክፍለ ዘመን መባቻ፤ካየሁትና ከሰማሁት" በሚል ርዕስ በፃፉት ውድ የታሪክ ማስታወሻቸው ተከትቧል።
የዚያን ጊዜ በሽታው ወደ ኢትዮጵያ ምድር በንፋስ አማካኝነት የመጣ ሲሆን ጥበበኛው የአገሬ ሰውም በብዙ ዘመን ልምዱ ባካበተው እውቀቱ በመታገል ለ አዕላፍ(ሚሊዮን) የዓለም ህዝብ ህይወት መቀጠፍ ምክንያት የሆነውን ጉንፋን መሠል ወረርሽኝ ተዋግቶ አሸንፎታል።
አዲስ አድማስ ጋዜጣ በ2006ዓ.ም ህዳር ወር ይዞት በወጣው ፅሁፍ እንደሚያትተው በወቅቱ የመንዝ ተወላጅ የነበሩት ወይዘሮ ዘነበች የተባሉ የባህል መድሃኒት አዋቂ ለአዲስ አበቤ ያስተማሩት የአበሻ አረቄን መጠጣት እና ቀይ ሽንኩርት በየ ቤቱ እንዲሁም በእየ አንገቱ ማንጠልጠል በፈረንሳይ ቆንሲል በኩል ሳይቀር ተኮርጆ ወደ አውሮፓ በመላክ "የሠለጠነውን" ዓለም ለመፈወስ በቅቷል።
የሴትዮይቱ ከልምድ የተገኘ መድሃኒት በተለይም አረቄው ከነበረበት በጠርሙስ 10 ሳንቲም ዋጋ ወደ ሰባት ብር አድጎ ሜዲትራኒያንን ተሻግሮ አውሮፓዊያኑን አልቦ(ዜሮ) ከመቅረት ታድጓቸዋል።
ኢትዮጵያዊያን ከዚህም በተጨማሪ የደረቀን የበሬ ቆዳ በታማሚው አካባቢ በማንኳኳትና ጠብ መንጃ ወደ ጆሮው አስጠግቶ በመተኮስ በሽታውን አስደንግጦ ለማባረር ተሳክቶላቸዋል፤ይሄንን ስልት እስካሁን ድረስ ጥቅም ላይ የሚያውል ማህበረሰብ እንዳለ እኔም አውቃለሁ---ጎጃም ሰው ሊሞት ጥቂት ሲቀረው በጠብመንጃ ተኩስ ለማንቃት የመጨረሻ ሙከራ ይደረጋል።
እንግዲህ እኛ እንዲህ ያሉ ከላይኛው ጠቢብ የተላከ ጥበብ ያለን ልዑላን ህዝቦች ነንና ዛሬ መቶ ሰው ይዞ ሁለት(ለዚያውም በዕድሜ የገፉትን) ለሚገድል በሽታ ብለን ከሰውነት ጣሪያ ወርደን ርስ በእርስ እንዳንፈራራ ይሁን።
መጠንቀቅና መሳቀቅን ማመጣጠን ከቻልን ኮሮናን እናሸንፈዋለን።
8335 እንዳይረሳ
።፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
ይቆየን!
@wegoch
@wegoch