ኢትዮቴሌኮም ከሜታ ከኩባንያ ጋር በመተባበር የደንበኞች ተሞክሮ የሚያሻሽል ፕሮግራም ተግባራዊ ሊያደርግ ነው!
ኢትዮቴሌኮም ዋና ስራ አስፈጻሚ ፍሬህይወት ታምሩ ከሜታ-ፌስቡክ የመካከለኛው ምስራቅና አፍሪካ የንግድ ልማትና ስትራቴጂክ አጋርነት ዳይሬክተር ቪካስ ሜኖን ጋር የደንበኞችን የዲጂታል ተሞክሮ ለማሻሻል በሚረዱ ጉዳዮች ላይ ስትራቴጂያዊ ውይይት አደረጉ።በውይይቱ ሜታ-ፌስቡክ ከኢትዮቴሌኮም ጋር በመተባበር የደንበኞችን ዳታ አጠቃቀም የሚያሻሻል ፕሮግራም በኢትዮጵያ መጀመሩ ያለውን ትብብር ወደላቀ ደረጃ እንደሚያሳድገው ተገልጿል።
ደንበኞች አካውንታቸው ውስጥ ሂሳብ ባይኖርም የሜታ-ፌስቡክ አገልግሎቶችን ለተወሰነ ጊዜ በነጻ በመጠቀም ግንኙነታቸውን እንዲያስቀጥሉ ከማስቻል ባሻገር ጤና፣ ትምህርትና የስራ ዐድሎች ጠቃሚ መረጃዎችን ከክፍያ ነጻ በማቅረብ በመረጃ የበለጸገ ንቁ ዜጋ ለመፍጠር ያስችላል፡፡የዲጂታል ሊትሬሲንና አካታችነትን ማሳደግ ለዲጂታል ኢትዮጵያ ግንባታ ወሳኝ ነው። ሀገራዊ የይዘት ፈጠራ እንዲጎለብትና የዲጂታል ስነምህዳሩን የሚያሻሽሉ ፋይዳ ያላቸው ፕሮግራሞችን መተግበር የሳይበር ደህንነትና መረጃ አያያዝን በጋራ አስተማማኝ ስለማድረግ አጽንኦት ሰጥተዋል፡፡
የስምምነቱ ትግበራ የዲጂታል አገልግሎት ተደራሽነትንና አካታችነትን በመጨመር የሀገራችንን ዲጂታል ሊትሬሲ በማሳደግ እንዲሁም ለደንበኞች የላቀ ተሞክሮ በማምጣት ለዲጂታል ትራንስፎርሜሽን እድገት የላቀ ሚና እንደሚኖረው ከኢትዮቴሌኮም ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
@YeneTube @FikerAssefa
ኢትዮቴሌኮም ዋና ስራ አስፈጻሚ ፍሬህይወት ታምሩ ከሜታ-ፌስቡክ የመካከለኛው ምስራቅና አፍሪካ የንግድ ልማትና ስትራቴጂክ አጋርነት ዳይሬክተር ቪካስ ሜኖን ጋር የደንበኞችን የዲጂታል ተሞክሮ ለማሻሻል በሚረዱ ጉዳዮች ላይ ስትራቴጂያዊ ውይይት አደረጉ።በውይይቱ ሜታ-ፌስቡክ ከኢትዮቴሌኮም ጋር በመተባበር የደንበኞችን ዳታ አጠቃቀም የሚያሻሻል ፕሮግራም በኢትዮጵያ መጀመሩ ያለውን ትብብር ወደላቀ ደረጃ እንደሚያሳድገው ተገልጿል።
ደንበኞች አካውንታቸው ውስጥ ሂሳብ ባይኖርም የሜታ-ፌስቡክ አገልግሎቶችን ለተወሰነ ጊዜ በነጻ በመጠቀም ግንኙነታቸውን እንዲያስቀጥሉ ከማስቻል ባሻገር ጤና፣ ትምህርትና የስራ ዐድሎች ጠቃሚ መረጃዎችን ከክፍያ ነጻ በማቅረብ በመረጃ የበለጸገ ንቁ ዜጋ ለመፍጠር ያስችላል፡፡የዲጂታል ሊትሬሲንና አካታችነትን ማሳደግ ለዲጂታል ኢትዮጵያ ግንባታ ወሳኝ ነው። ሀገራዊ የይዘት ፈጠራ እንዲጎለብትና የዲጂታል ስነምህዳሩን የሚያሻሽሉ ፋይዳ ያላቸው ፕሮግራሞችን መተግበር የሳይበር ደህንነትና መረጃ አያያዝን በጋራ አስተማማኝ ስለማድረግ አጽንኦት ሰጥተዋል፡፡
የስምምነቱ ትግበራ የዲጂታል አገልግሎት ተደራሽነትንና አካታችነትን በመጨመር የሀገራችንን ዲጂታል ሊትሬሲ በማሳደግ እንዲሁም ለደንበኞች የላቀ ተሞክሮ በማምጣት ለዲጂታል ትራንስፎርሜሽን እድገት የላቀ ሚና እንደሚኖረው ከኢትዮቴሌኮም ያገኘው መረጃ ያመለክታል።
@YeneTube @FikerAssefa