በኢትዮጵያ ውስጥ ትልቁ የእርዳታ አቅራቢ ድርጅት በሆነዉ ዩኤስኤይድ የሚደረጉ የእርዳታ ስራዎች እንዲቋረጡ መድረጉ ጫናዉ በሌሎች አለም አቀፍ የእርዳታ ድርጅቶች ላይ ሆኗል!
የአሜሪካ ዓለም አቀፍ የተራድዖ ድርጅት የሆነው "ዩኤስኤይድ" የሚያደርገዉን የስራ እንቅስቃሴ በድንገት እንዲያቆም መደረጉ ከፍተኛ ክፍት መፍጠሩ የተገለፀ ሲሆን ይህም በሌሎች አለም አቀፍ መንግስታዊ ያልሆኑ የእርዳታ ድርጅቶች ላይ እንዲወድቅ ማድረጉን ካፒታል ከምንጮቿ መረዳት ችላለች።እነዚሁ ድርጅቶች እንደ ጤና፣ ትምህርት፣ ግብርና፣ ሰብአዊ ርዳታ እና የአካባቢ ጥበቃ ያሉ የተለያዩ የልማት ዘርፎች ላይ እየተሳተፉ የሚገኙ ቢሆንም በኢትዮጵያ ዩኤስኤይድ የተጀመሩ ፕሮጀክቶችን እንዲጨርሱ ወይም እንዲሸፍኑ እየተደረጉ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል።
የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ከሳምንት በፊት ባስተላለፉት ልዩ ትዕዛዝ ለዘጠና ቀናት ( ለ 3 ወር ) ያህል ማናቸውም የውጭ እርዳታዎች እንዳይሰጡ መከልከላቸውንና በእነዚህ ቀናት በአለም ላይ ያሉት የእርዳታ ስራዎች በሙሉ ግምገማ እንደሚከናወንባቸው አስረድቷል፡፡ይህን ዉሳኔዉ በተመሳሳይ በኢትዮጵያ ተግባራዊ መደረግ የጀመረ ሲሆን በድርጅቱ ቀድሞ የተጀመሩ ፕሮጀክቶች በሌሎች መሰል የእርዳታ ድርጀቶች ላይ ኃላፊነቱ ወድቋል።
እንደ አለም አቀፍ የነፍስ አድን ኮሚቴ ጨምሮ ዩኤንኤችአር ፣ ዩኤንኤፍፒኤ እንዲሁም ፋኦ የመሳሰሉ በርካታ አለም አቀፍ ተራድዖ ድርጅቶች ኢትዮጵያን በተለያዩ ዘርፎች እየደገፉ እንደሚገኙ ይታወቃል።
Via Capital
@YeneTube @FikerAssefa
የአሜሪካ ዓለም አቀፍ የተራድዖ ድርጅት የሆነው "ዩኤስኤይድ" የሚያደርገዉን የስራ እንቅስቃሴ በድንገት እንዲያቆም መደረጉ ከፍተኛ ክፍት መፍጠሩ የተገለፀ ሲሆን ይህም በሌሎች አለም አቀፍ መንግስታዊ ያልሆኑ የእርዳታ ድርጅቶች ላይ እንዲወድቅ ማድረጉን ካፒታል ከምንጮቿ መረዳት ችላለች።እነዚሁ ድርጅቶች እንደ ጤና፣ ትምህርት፣ ግብርና፣ ሰብአዊ ርዳታ እና የአካባቢ ጥበቃ ያሉ የተለያዩ የልማት ዘርፎች ላይ እየተሳተፉ የሚገኙ ቢሆንም በኢትዮጵያ ዩኤስኤይድ የተጀመሩ ፕሮጀክቶችን እንዲጨርሱ ወይም እንዲሸፍኑ እየተደረጉ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል።
የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ከሳምንት በፊት ባስተላለፉት ልዩ ትዕዛዝ ለዘጠና ቀናት ( ለ 3 ወር ) ያህል ማናቸውም የውጭ እርዳታዎች እንዳይሰጡ መከልከላቸውንና በእነዚህ ቀናት በአለም ላይ ያሉት የእርዳታ ስራዎች በሙሉ ግምገማ እንደሚከናወንባቸው አስረድቷል፡፡ይህን ዉሳኔዉ በተመሳሳይ በኢትዮጵያ ተግባራዊ መደረግ የጀመረ ሲሆን በድርጅቱ ቀድሞ የተጀመሩ ፕሮጀክቶች በሌሎች መሰል የእርዳታ ድርጀቶች ላይ ኃላፊነቱ ወድቋል።
እንደ አለም አቀፍ የነፍስ አድን ኮሚቴ ጨምሮ ዩኤንኤችአር ፣ ዩኤንኤፍፒኤ እንዲሁም ፋኦ የመሳሰሉ በርካታ አለም አቀፍ ተራድዖ ድርጅቶች ኢትዮጵያን በተለያዩ ዘርፎች እየደገፉ እንደሚገኙ ይታወቃል።
Via Capital
@YeneTube @FikerAssefa