የአ/አ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ም/ቤት ማስጠንቀቂያ
የአዲስ አበባ መጅሊስ ከዚህ በኋላ በመስጂዶች ጉዳይ አይታገስም።
1446ኛው ታላቁ የረመዳን ወር መስጂዶች ደምቀውና ተውበው ህዝበ ሙሊሙን በተገቢው መንገድ በመቀበል እያሰተናገዱ ነወ።
በአብዛኛዎቹ መስጂዶች ህዝበ ሙሰሊሙ እምነቱ በሚያዘው መሠረት ዒባዳውን እያከናወነ ሲሆን በጣት በሚቆጠሩ መስጂዶች ሁከት ለማስነሣት የተደረጉ ሙከራዎችን በየመሰጂዱ የሚገኙ ኮሚቴዎች፣ ሀዲሞችና ህብረተሰቡ ባደረገው ጥረት በቁጥጥር ሰር ሊውሉ ችሏል።
በተለይም ጠሮ መስጂድ ፣ሎሚ ሜዳ(ዓሊ) መስጂድና አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ወረዳ 2 የሚገኘው ሀምዛ መሰጂድ የረመዳንን መግባት ተከትሎ በአንዳንድ ሰውር አላማ ያላቸው ግለሰቦች ሁከትና ብጥብጥ በማሰነሣት ከፍተኛ ችግር ሲፈጥሩ የቆዩ አካላት መሸሸጊያ ሆኖ የቆየ ቢሆንም መጅሊስ ከዛሬ ነገ ይቀየራሉ ብሎ ሁኔታውን አባታዊ በሆነ ትዕግሰት ይዞት ቆይቷል።
መጅሊሰ በእነዚህ ጥቂት መስጂዶች የተፈጠሩትን ችግሮች ለመፍታት የተለያዩ ጥረቶችን ቢያደርግም ዕድሉን ባለመጠቀም ቡድኑ መሰጂድ ሰብሮ በመግባት፣ ጄነሬተር በማጥፋት፣ ለደህንነት የተገጠመ ካሜራን በመሰባበር እና አማኞች የተረጋጋ ዒባዳ(የአምልኮ ስርዓት) እንዳይከውኑና የረመዳንን ወር የብጥብጥና የረብሻ አውድማ የማድረግ እንቅሰቃሴያቸውን ቀጥለውበታል።
ከወራት በፊት ማዕከላቸውንና የብጥብጥ መነሻቸውን ዓሊ መስጂድ በማድረግ ሴቶችና ህፃናትን ከፊት በማሰለፍና የተወሰኑ ግለሰቦችን በገንዘብ በመደለል የተጀመረው ውንብድና ኢማሞችን ማይክ ቀምቶ በመደብደብ የተራዊ ሰላት እንዲቋረጥ እሰከ ማድረግ ደርሰዋል
ይህ በግልፅ በሚታወቁ ግለሰቦች የሚመራው ቡድን በተመረጡና ለማምለጥ ምቹ በሆኑ መስጂዶች ከተለያየ አካባቢ ተጠራርተው በመግባት አወል ሰፍን (የሰላቱን የመጀመሪያ ረድፍ) ለመሰጂድም ሆነ ለሸማግሌዎች ክብር የሌላቸው አሰቀድመው በመያዝ ረብሻ በማሰነሣት መሰጂዱን አውከዋል።
በየጊዜው በየመስጂዱ እየተዘዋወሩ ሁከት የሚፈጥሩ አካላት በሚገባ የሚታወቁና መረጃ ያለን ሲሆን እንደ አስፈላጊነቱ ለህዝብ እንደምናሳውቅ እየገለፅን መጅሊሱ ከዚህ በላይ እንደማይታገሰና ከሚመለከታቸው አካላት ጋር የፀሎት ቦታዎች ሠላማዊ እንዲሆኑ መስራቱን እንደሚቀጥል ለህዝበ ሙስሊሙ ያሣውቃል።
መጅሊሱ ካለበት ሀላፊነትና ተጠያቂነት አኳያ ጉዳዩን በትዕግሰት መያዙ አግባብ ቢሆንም በዚህ የሠላም፣ የፍቅር፣ የአንድነትና የመተዛዘን ወር በሁለቱ መስጂዶች በተፈጠረው አሳፋሪ ተግባር ክፉኛ ማዘኑን እየገለፀ ሙስሊሙ ማሕበረሰብ ዒባዳውን(የአምልኮ ሥርዐቱን) የሚፈፅምባቸው መስጂዶች ሠላማቸው እንዲጠበቅ ከባለ ድርሻ አካላት ጋር በትኩረት እንደሚሠራ በድጋሚ ለመግለፅ ይወዳል።
የአ/አ/ከ/እ/ጉ/ከ/ም ቤት የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
#ዳጉ_ጆርናል
የአዲስ አበባ መጅሊስ ከዚህ በኋላ በመስጂዶች ጉዳይ አይታገስም።
1446ኛው ታላቁ የረመዳን ወር መስጂዶች ደምቀውና ተውበው ህዝበ ሙሊሙን በተገቢው መንገድ በመቀበል እያሰተናገዱ ነወ።
በአብዛኛዎቹ መስጂዶች ህዝበ ሙሰሊሙ እምነቱ በሚያዘው መሠረት ዒባዳውን እያከናወነ ሲሆን በጣት በሚቆጠሩ መስጂዶች ሁከት ለማስነሣት የተደረጉ ሙከራዎችን በየመሰጂዱ የሚገኙ ኮሚቴዎች፣ ሀዲሞችና ህብረተሰቡ ባደረገው ጥረት በቁጥጥር ሰር ሊውሉ ችሏል።
በተለይም ጠሮ መስጂድ ፣ሎሚ ሜዳ(ዓሊ) መስጂድና አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ወረዳ 2 የሚገኘው ሀምዛ መሰጂድ የረመዳንን መግባት ተከትሎ በአንዳንድ ሰውር አላማ ያላቸው ግለሰቦች ሁከትና ብጥብጥ በማሰነሣት ከፍተኛ ችግር ሲፈጥሩ የቆዩ አካላት መሸሸጊያ ሆኖ የቆየ ቢሆንም መጅሊስ ከዛሬ ነገ ይቀየራሉ ብሎ ሁኔታውን አባታዊ በሆነ ትዕግሰት ይዞት ቆይቷል።
መጅሊሰ በእነዚህ ጥቂት መስጂዶች የተፈጠሩትን ችግሮች ለመፍታት የተለያዩ ጥረቶችን ቢያደርግም ዕድሉን ባለመጠቀም ቡድኑ መሰጂድ ሰብሮ በመግባት፣ ጄነሬተር በማጥፋት፣ ለደህንነት የተገጠመ ካሜራን በመሰባበር እና አማኞች የተረጋጋ ዒባዳ(የአምልኮ ስርዓት) እንዳይከውኑና የረመዳንን ወር የብጥብጥና የረብሻ አውድማ የማድረግ እንቅሰቃሴያቸውን ቀጥለውበታል።
ከወራት በፊት ማዕከላቸውንና የብጥብጥ መነሻቸውን ዓሊ መስጂድ በማድረግ ሴቶችና ህፃናትን ከፊት በማሰለፍና የተወሰኑ ግለሰቦችን በገንዘብ በመደለል የተጀመረው ውንብድና ኢማሞችን ማይክ ቀምቶ በመደብደብ የተራዊ ሰላት እንዲቋረጥ እሰከ ማድረግ ደርሰዋል
ይህ በግልፅ በሚታወቁ ግለሰቦች የሚመራው ቡድን በተመረጡና ለማምለጥ ምቹ በሆኑ መስጂዶች ከተለያየ አካባቢ ተጠራርተው በመግባት አወል ሰፍን (የሰላቱን የመጀመሪያ ረድፍ) ለመሰጂድም ሆነ ለሸማግሌዎች ክብር የሌላቸው አሰቀድመው በመያዝ ረብሻ በማሰነሣት መሰጂዱን አውከዋል።
በየጊዜው በየመስጂዱ እየተዘዋወሩ ሁከት የሚፈጥሩ አካላት በሚገባ የሚታወቁና መረጃ ያለን ሲሆን እንደ አስፈላጊነቱ ለህዝብ እንደምናሳውቅ እየገለፅን መጅሊሱ ከዚህ በላይ እንደማይታገሰና ከሚመለከታቸው አካላት ጋር የፀሎት ቦታዎች ሠላማዊ እንዲሆኑ መስራቱን እንደሚቀጥል ለህዝበ ሙስሊሙ ያሣውቃል።
መጅሊሱ ካለበት ሀላፊነትና ተጠያቂነት አኳያ ጉዳዩን በትዕግሰት መያዙ አግባብ ቢሆንም በዚህ የሠላም፣ የፍቅር፣ የአንድነትና የመተዛዘን ወር በሁለቱ መስጂዶች በተፈጠረው አሳፋሪ ተግባር ክፉኛ ማዘኑን እየገለፀ ሙስሊሙ ማሕበረሰብ ዒባዳውን(የአምልኮ ሥርዐቱን) የሚፈፅምባቸው መስጂዶች ሠላማቸው እንዲጠበቅ ከባለ ድርሻ አካላት ጋር በትኩረት እንደሚሠራ በድጋሚ ለመግለፅ ይወዳል።
የአ/አ/ከ/እ/ጉ/ከ/ም ቤት የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
#ዳጉ_ጆርናል