Forward from: ግጥም በ ኤዶምገነት
#አትጥቀሰኝ
ሳይሰነዝር 'ሚጥል
ሳይገል የሚረታ፣
አንዳች ጉልበት አለው
ያይንህ ስልምልምታ።
እንኳንስ ጨክነህ
አርገብግበህብኝ፣
ድሮም እኔ ልጅት
ፍርሃት አለብኝ፣
እኒያ ውብ ዓይኖችህ
ወደኔ ካመሩ፣
ይመስሉኛል ውስጤን
የሚመረምሩ፣
ያስጎነብሱኛል እንደ
ጨረር ግለት፣
አንተን ለመጋፈጥ
ያሳጡኛል ጉልበት።
ታዲያ ለምንድን ነው....
እንደምንም ችዬ
ሆኜ እንደጠንካራ፣
ወዳንተው ለማዬት
በድንገት ሳመራ፣
ተዘጋጂ ሳትል
ወይ ሳታሳውቀኝ፣
በአይኖችህ ጠቅሰህ
ቀልቤን የምትሰርቀኝ?
አስበኸው ይሆን
ወይስ ሳታስበው፣
የእኔን ሁለመና
ወዳንተ ምትስበው?
ደጋግሞ እጅ መስጠት
ባይኖችህ ብለምድም፣
በአንተ አይነት ጩልሌ
መሸነፍ አልፈቅድም፣
አካሌ እንደባዳ ልቀቂኝ እያለ
ሁሌ ከሚወቅሰኝ፣
ልለምንህ በቃ በምትወደው ነገር
ተወኝ አትጥቀሰኝ።
#ኤዶምገነት_ፃፈችው
@arifgtmbcha
ሳይሰነዝር 'ሚጥል
ሳይገል የሚረታ፣
አንዳች ጉልበት አለው
ያይንህ ስልምልምታ።
እንኳንስ ጨክነህ
አርገብግበህብኝ፣
ድሮም እኔ ልጅት
ፍርሃት አለብኝ፣
እኒያ ውብ ዓይኖችህ
ወደኔ ካመሩ፣
ይመስሉኛል ውስጤን
የሚመረምሩ፣
ያስጎነብሱኛል እንደ
ጨረር ግለት፣
አንተን ለመጋፈጥ
ያሳጡኛል ጉልበት።
ታዲያ ለምንድን ነው....
እንደምንም ችዬ
ሆኜ እንደጠንካራ፣
ወዳንተው ለማዬት
በድንገት ሳመራ፣
ተዘጋጂ ሳትል
ወይ ሳታሳውቀኝ፣
በአይኖችህ ጠቅሰህ
ቀልቤን የምትሰርቀኝ?
አስበኸው ይሆን
ወይስ ሳታስበው፣
የእኔን ሁለመና
ወዳንተ ምትስበው?
ደጋግሞ እጅ መስጠት
ባይኖችህ ብለምድም፣
በአንተ አይነት ጩልሌ
መሸነፍ አልፈቅድም፣
አካሌ እንደባዳ ልቀቂኝ እያለ
ሁሌ ከሚወቅሰኝ፣
ልለምንህ በቃ በምትወደው ነገር
ተወኝ አትጥቀሰኝ።
#ኤዶምገነት_ፃፈችው
@arifgtmbcha