ጸሎት እንደስካር
ኤልያስ ሽታኹን
~ ~ ~ ~ ~
ሀና በእግዚአብሔር ፊት አለቀሰች።
በደጁም ተንበረከከች።
ካህኑ ኤሊ
የአፏን እንቅስቃሴ አይቶ "ሰክራለች" አለ።
ያውም ካህን ነው።
ሲሆን ተጠግቶ ነው "ምነው" ሊላት ሲገባ ፈረደባት።
እንዲያውም ተናገራት "ወይን መጠጣት አቁሚ" አላት
ልክ ከዚህ በፊት ሰክራ የሚያውቃት ይመስል
"ስካርሽ እስከመቼ ነው" አላት
ይሄ በኛ ቢደርስ ይሄን ብንባል
አኩርፎ ለመውጣት ሀይማኖት ለመቀየር ሁለቴ ባላሰብን ነበር።
ሀና ግን አስረዳችው።
ታጋሽ ናትና እግዚአብሔር ባርያውን እንዲያየኝ ነው የምለምን አለችው።
አንዳንዴ እኮ
የናንተ ሀዘን የናንተ ለቅሶ ለአንዳንዶች ስካር ነው። ጤና ማጣትም ነው። ምን አልባትም ለብዙዎችም "ፋራነት" ነው።
ግን እንዲህ በሉት
"እኔስ ልቧ ያዘነበኝ ሴት ነኝ። ጠጅና የሚያሰክር ነገር አልጠጣሁም። ነገር ግን በእግዚአብሔር ፊት ነፍሴን አፈፈስሁ"
መጽሐፈ ሳሙኤል ቀዳማዊ
1:15
ኤልያስ ሽታኹን
~ ~ ~ ~ ~
ሀና በእግዚአብሔር ፊት አለቀሰች።
በደጁም ተንበረከከች።
ካህኑ ኤሊ
የአፏን እንቅስቃሴ አይቶ "ሰክራለች" አለ።
ያውም ካህን ነው።
ሲሆን ተጠግቶ ነው "ምነው" ሊላት ሲገባ ፈረደባት።
እንዲያውም ተናገራት "ወይን መጠጣት አቁሚ" አላት
ልክ ከዚህ በፊት ሰክራ የሚያውቃት ይመስል
"ስካርሽ እስከመቼ ነው" አላት
ይሄ በኛ ቢደርስ ይሄን ብንባል
አኩርፎ ለመውጣት ሀይማኖት ለመቀየር ሁለቴ ባላሰብን ነበር።
ሀና ግን አስረዳችው።
ታጋሽ ናትና እግዚአብሔር ባርያውን እንዲያየኝ ነው የምለምን አለችው።
አንዳንዴ እኮ
የናንተ ሀዘን የናንተ ለቅሶ ለአንዳንዶች ስካር ነው። ጤና ማጣትም ነው። ምን አልባትም ለብዙዎችም "ፋራነት" ነው።
ግን እንዲህ በሉት
"እኔስ ልቧ ያዘነበኝ ሴት ነኝ። ጠጅና የሚያሰክር ነገር አልጠጣሁም። ነገር ግን በእግዚአብሔር ፊት ነፍሴን አፈፈስሁ"
መጽሐፈ ሳሙኤል ቀዳማዊ
1:15