#4
"በመጨረሻም ያመንኩት ሁሉ ዉሸት መሆኑን ደረስኩበት "
አለች ከተቀመጠችበት አግዳሚ ወንበር ላይ ፈንጠር ብላ በመነሳት ። አይኖች ሁሉ ወደሷ ሆኑ ። አበደች እንዴ በሚል አይነት አየናት ። ሰንበት ነው አጥቢያችን በሚገኘው ደብር የእለቱን የቤተ-ክርስቲያን ስርአት ካከናወንን ቡሃላ የንስሀ አባታችንን ለማግኘት ልጆቻቸው ሰብሰብ ብለን እየጠበቅናቸው በዚ መሀል ነበር ግቢ ውስጥ ማትጠፋው ፀይም ቆንጅዬ ልጅ ጮክ ብላ ማውራት የጀመረችው (በዝምተኝነቷ ስለምናቃት ደነገጥን)
"አልደከማችሁም ? ሁሉንም ነገር እርግፍ አድርጎ
መተው አላማራችሁም ? አለች ሁላችንንም እያየች
ምን እንደሆነች ስለማናቅ ሁላችንም ግራ ተጋባን !
"እግዜሩም ደሀ ላይ ይበረታል በችግር ላይ ችግር
መደራረብ ያውቅበታል " አለች ወደ ሰማይ አንጋጣ
በትዝበት እያየች
ንሰሀ አባታችን "ደህና አረፈዳችሁ ?" ብለው ወደ አዳራሹ ሲገቡ አንጋጣ ስታነባ አዩዋት
"ወለተ ጊዮርጊስ ምነው ልጄ ምን ነካሽ ?"
"አባ ተዉኝ ዛሬ እንኳን ይውጣልኝ "አለች
ወደኛ ዞር ብላ "እብድ መሰልኳቹ አደል ?(በጥልቅ ሀዘን ማውራት ጀመረች) በውሸት አለም ምኖር ሰው አደለም ፈጣሪ የረሳኝ በሁሉ የተገፋው ነኝ ታዲያ ማበድ ይነሰኝ ? "
"የሆንሽውን ንገሪን እስኪ ልጄ" አሉ በእድሜ ገፋ ያሉ እናት ። በስስት ና በጉጉት ሄዳ እግራቸው ስር ቁጭ አለች ። "እውነት እማማ ይሰሙኛል ?" አለቻቸው እያነባች ። አሳዘነችኝ ለካ ጆሮም ይናፍቃል....ሴትዮዋ አንገታቸውን ነቀነቁላት ። አደለም እሳችው እኛ ሁላችንም ለመስማት ጆሮዋችን አሹለን እየጠበቅናት ነው ።
"እየውሎትማ እማማ...አንድ ጨካኝ ወንድም ነበረኝ በጣም ቁማርተኛ ነበር ቤት ውስጥ ምንም ነገር እስከማይቀር ድረስ እየሸጠ ተጫውቶበታል ። ከሁሉም የከፋው ግን የቤታችን ነበር....የሆነ ጥቁር ጠዋት ሱፍ የለበሱ ሰዎች ብጣሽ ወረቀት ይዘው መተው ቤቱን በቁማር እዳ እንደወሰዱት አረዱን ። እናቴ ላቧን ልጅነቷን ደሟን የጨረሰችበት ቤት ያንቺ አደለም ስትባል ልቧ ቀጥ ብሎ በዛው አሸለበች...ታሳዝናለች አይደል ?! በቃ ከዛ የኔን ነገር ተዉት ህይወቴ ግራ ገባው እዛ ና እዚ መባዘን ተግባሬ ሆነ....ከብዙ መባዘኖቼ መሀል አንድ ሰው ተዋወኩ ችግሬን ነገርኩት አለውልሽ አለኝ ትከሻውን ሰጠኝ ሳላመነታ ተደገፍኩት (የንዴት የበቀል እና የእልህ ፈገግታ ፊቷ ላይ በግልፅ ይታያል) ጥሩ ኑሮ መኖር ጀመርኩ " ብላ ጸጥ አለች ፋታ የመውሰድ አይነት ዝምታ ። ሁላችንም በጉጉት እጠበቅናት ነው ። (እኔ በበኩሌ ስንቱን አሰብኩት)
እንባዋን ጠራርጋ ተረኳን ቀጠለች "ከጊዜያት በኋላ ጸነስኩ ደስታ ምሆነውን አሳጣኝ አለም የኔ መሰለችኝ ፈጣሪዬን በብዙ አመሰገንኩ ። ስወልድ ግን ደስታዬ ተሻረ። የሞተ ነው የወለድሽው ብለው ሬሳ አስታቀፉኝ" (እንባዋ እንደጅረት ይወርዳል) ንግሯሯ በጣም ስለሰቀጠጠኝ አይኖቼን በህመም ጨፈንኳቸው እናትነት ሚገባቸው ሴቶች ፊታቸውን በነጠላ ሸፍነው ያነባሉ ።
"ይሄ ይገርሞታል እማማ....ይባስ ብሎ ባሌ ሸጠኝ ።!"
"ሸጠኝ ?!" አሉ እማማ በድንጋጤ
"አዎ ሸጠኝ " አለች ቃላቱን ረገጥ አርጋ
"ለማን ? "
"ለሴተኛ አዳሪነት " አለች ስብር ብላ
እማማ በስመአብ ብለው አማተቡ !
"ለካ ያገባውት ሰው ወንጀለኛ ቁማርተኛ ከህገ ወጥ ስራ ውስጥ ማይጠፋ ሰይጣን ነበር ። ለብዙ ጊዜ ገላዬን እየቸበቸቡ ተጫወቱብኝ እሱም ልጃችን ሲሞት ብቻዬን ጥላኝ ምንም ሳይጎልባት ሽርሙጥና ገባች እያለ ስሜን አጠፋው።"
"ኧረ በዲማው" አሉ እማማ እኛም ብንሆን ምንሰማው ነገር ክብድ ብሎናል ።
" ደሞ እኮ ልጄ ሞቶ አደለም እሱንም ሽጦት ነው። (ፊቷ ትንሽም ቢሆን ተስፋ ተነበበት) ለነፍሴ ያለች ነርስ ናት አሳዘንሽኝ ብላ የነገረችኝ ። አሳየኝ እያልኩ ብዙ ለምንኩት አስለመንኩት ጭራስ አበደች ለየላት የሞተ ልጅ ከየት ላምጣ የኔንስ ሀዘን ለምን ተቀሰቅሳለች እያለ ራሱን እንደ ፃድቅ አስቆጠረ ። እሱ ምስኪን የተገፋ አባት እኔ ግን ( ሳግ ተናነቃት) እኔ ግን እብድ ሱሰኛ ሴተኛ አዳሪ ብዙ ብዙ ተባልኩ። በጣም ስታምም ገላዬ እንደ ድሮ ተፈላጊነት ሲያጣ አውጥተው ጎዳና ጣሉኝ አባ ናቸው ከምንም አንስተው ለዚ እንኳን ያበቁኝ።" ብላ ተነፈሰች
ሁላችንም ወደ አባ ዞርን አቀርቅረው እንባቸውን ያፈሳሉ።
"በቃ እኔ ማለት እቺ ነኝ አለኝ ምለው ወንድሜ የተደገፍኩት ባሌ የፈጠረኝ አምላኬ ተባብረው ያረገፉኝ ማያቁኝ የገፉኝ ያምንኩት ሁሉ የኖርኩት ሁሉ ውሸት የሆነብኝ ሰሚ እንኳን የሌለኝ ብቸኛ " ብላ ተንሰቀሰቀሰች ። አብረናት አነባን....
ስንቶቻችን ነን የኑሮዋችንን ዉሸት ማመን ሳንፈልግ እዛው በሀሰት ምንቦራጨቅ ብናምንም መውጫው የጠፋን....ለካ አንዳንዴ ኑሮ ሀሰት መሆኑን አምኖ መቀበል እረፍት አለው....
ከቤተ መቅደስ የተከፈተው "ከንቱ ነኝ ከንቱ ከንቱ ነኝ ዋስትና መከታ እግዚአብሔር ካልሆነኝ " ሚለው መዝሙር እንባችንን አገዘው ።
✍️ ወርቅ_አለማው
https://t.me/justhoughtsss
"በመጨረሻም ያመንኩት ሁሉ ዉሸት መሆኑን ደረስኩበት "
አለች ከተቀመጠችበት አግዳሚ ወንበር ላይ ፈንጠር ብላ በመነሳት ። አይኖች ሁሉ ወደሷ ሆኑ ። አበደች እንዴ በሚል አይነት አየናት ። ሰንበት ነው አጥቢያችን በሚገኘው ደብር የእለቱን የቤተ-ክርስቲያን ስርአት ካከናወንን ቡሃላ የንስሀ አባታችንን ለማግኘት ልጆቻቸው ሰብሰብ ብለን እየጠበቅናቸው በዚ መሀል ነበር ግቢ ውስጥ ማትጠፋው ፀይም ቆንጅዬ ልጅ ጮክ ብላ ማውራት የጀመረችው (በዝምተኝነቷ ስለምናቃት ደነገጥን)
"አልደከማችሁም ? ሁሉንም ነገር እርግፍ አድርጎ
መተው አላማራችሁም ? አለች ሁላችንንም እያየች
ምን እንደሆነች ስለማናቅ ሁላችንም ግራ ተጋባን !
"እግዜሩም ደሀ ላይ ይበረታል በችግር ላይ ችግር
መደራረብ ያውቅበታል " አለች ወደ ሰማይ አንጋጣ
በትዝበት እያየች
ንሰሀ አባታችን "ደህና አረፈዳችሁ ?" ብለው ወደ አዳራሹ ሲገቡ አንጋጣ ስታነባ አዩዋት
"ወለተ ጊዮርጊስ ምነው ልጄ ምን ነካሽ ?"
"አባ ተዉኝ ዛሬ እንኳን ይውጣልኝ "አለች
ወደኛ ዞር ብላ "እብድ መሰልኳቹ አደል ?(በጥልቅ ሀዘን ማውራት ጀመረች) በውሸት አለም ምኖር ሰው አደለም ፈጣሪ የረሳኝ በሁሉ የተገፋው ነኝ ታዲያ ማበድ ይነሰኝ ? "
"የሆንሽውን ንገሪን እስኪ ልጄ" አሉ በእድሜ ገፋ ያሉ እናት ። በስስት ና በጉጉት ሄዳ እግራቸው ስር ቁጭ አለች ። "እውነት እማማ ይሰሙኛል ?" አለቻቸው እያነባች ። አሳዘነችኝ ለካ ጆሮም ይናፍቃል....ሴትዮዋ አንገታቸውን ነቀነቁላት ። አደለም እሳችው እኛ ሁላችንም ለመስማት ጆሮዋችን አሹለን እየጠበቅናት ነው ።
"እየውሎትማ እማማ...አንድ ጨካኝ ወንድም ነበረኝ በጣም ቁማርተኛ ነበር ቤት ውስጥ ምንም ነገር እስከማይቀር ድረስ እየሸጠ ተጫውቶበታል ። ከሁሉም የከፋው ግን የቤታችን ነበር....የሆነ ጥቁር ጠዋት ሱፍ የለበሱ ሰዎች ብጣሽ ወረቀት ይዘው መተው ቤቱን በቁማር እዳ እንደወሰዱት አረዱን ። እናቴ ላቧን ልጅነቷን ደሟን የጨረሰችበት ቤት ያንቺ አደለም ስትባል ልቧ ቀጥ ብሎ በዛው አሸለበች...ታሳዝናለች አይደል ?! በቃ ከዛ የኔን ነገር ተዉት ህይወቴ ግራ ገባው እዛ ና እዚ መባዘን ተግባሬ ሆነ....ከብዙ መባዘኖቼ መሀል አንድ ሰው ተዋወኩ ችግሬን ነገርኩት አለውልሽ አለኝ ትከሻውን ሰጠኝ ሳላመነታ ተደገፍኩት (የንዴት የበቀል እና የእልህ ፈገግታ ፊቷ ላይ በግልፅ ይታያል) ጥሩ ኑሮ መኖር ጀመርኩ " ብላ ጸጥ አለች ፋታ የመውሰድ አይነት ዝምታ ። ሁላችንም በጉጉት እጠበቅናት ነው ። (እኔ በበኩሌ ስንቱን አሰብኩት)
እንባዋን ጠራርጋ ተረኳን ቀጠለች "ከጊዜያት በኋላ ጸነስኩ ደስታ ምሆነውን አሳጣኝ አለም የኔ መሰለችኝ ፈጣሪዬን በብዙ አመሰገንኩ ። ስወልድ ግን ደስታዬ ተሻረ። የሞተ ነው የወለድሽው ብለው ሬሳ አስታቀፉኝ" (እንባዋ እንደጅረት ይወርዳል) ንግሯሯ በጣም ስለሰቀጠጠኝ አይኖቼን በህመም ጨፈንኳቸው እናትነት ሚገባቸው ሴቶች ፊታቸውን በነጠላ ሸፍነው ያነባሉ ።
"ይሄ ይገርሞታል እማማ....ይባስ ብሎ ባሌ ሸጠኝ ።!"
"ሸጠኝ ?!" አሉ እማማ በድንጋጤ
"አዎ ሸጠኝ " አለች ቃላቱን ረገጥ አርጋ
"ለማን ? "
"ለሴተኛ አዳሪነት " አለች ስብር ብላ
እማማ በስመአብ ብለው አማተቡ !
"ለካ ያገባውት ሰው ወንጀለኛ ቁማርተኛ ከህገ ወጥ ስራ ውስጥ ማይጠፋ ሰይጣን ነበር ። ለብዙ ጊዜ ገላዬን እየቸበቸቡ ተጫወቱብኝ እሱም ልጃችን ሲሞት ብቻዬን ጥላኝ ምንም ሳይጎልባት ሽርሙጥና ገባች እያለ ስሜን አጠፋው።"
"ኧረ በዲማው" አሉ እማማ እኛም ብንሆን ምንሰማው ነገር ክብድ ብሎናል ።
" ደሞ እኮ ልጄ ሞቶ አደለም እሱንም ሽጦት ነው። (ፊቷ ትንሽም ቢሆን ተስፋ ተነበበት) ለነፍሴ ያለች ነርስ ናት አሳዘንሽኝ ብላ የነገረችኝ ። አሳየኝ እያልኩ ብዙ ለምንኩት አስለመንኩት ጭራስ አበደች ለየላት የሞተ ልጅ ከየት ላምጣ የኔንስ ሀዘን ለምን ተቀሰቅሳለች እያለ ራሱን እንደ ፃድቅ አስቆጠረ ። እሱ ምስኪን የተገፋ አባት እኔ ግን ( ሳግ ተናነቃት) እኔ ግን እብድ ሱሰኛ ሴተኛ አዳሪ ብዙ ብዙ ተባልኩ። በጣም ስታምም ገላዬ እንደ ድሮ ተፈላጊነት ሲያጣ አውጥተው ጎዳና ጣሉኝ አባ ናቸው ከምንም አንስተው ለዚ እንኳን ያበቁኝ።" ብላ ተነፈሰች
ሁላችንም ወደ አባ ዞርን አቀርቅረው እንባቸውን ያፈሳሉ።
"በቃ እኔ ማለት እቺ ነኝ አለኝ ምለው ወንድሜ የተደገፍኩት ባሌ የፈጠረኝ አምላኬ ተባብረው ያረገፉኝ ማያቁኝ የገፉኝ ያምንኩት ሁሉ የኖርኩት ሁሉ ውሸት የሆነብኝ ሰሚ እንኳን የሌለኝ ብቸኛ " ብላ ተንሰቀሰቀሰች ። አብረናት አነባን....
ስንቶቻችን ነን የኑሮዋችንን ዉሸት ማመን ሳንፈልግ እዛው በሀሰት ምንቦራጨቅ ብናምንም መውጫው የጠፋን....ለካ አንዳንዴ ኑሮ ሀሰት መሆኑን አምኖ መቀበል እረፍት አለው....
ከቤተ መቅደስ የተከፈተው "ከንቱ ነኝ ከንቱ ከንቱ ነኝ ዋስትና መከታ እግዚአብሔር ካልሆነኝ " ሚለው መዝሙር እንባችንን አገዘው ።
✍️ ወርቅ_አለማው
https://t.me/justhoughtsss