የኢትዮጵያውያን አንድነት ዳግም የታየበት የካራማራ ድል !
የካቲት 26 ቀን 1970 ዓ/ም የሱማሊያን ዚያድባሬ ጦር ለመመከት በካራማራ ጀግኖች የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጆች የህይወት መሰዋዕትነት ከፍለው ወራሪውን ጦር ከሀገር ያባረሩበት እና የሀገራቸውን ሰንደቅ ያውለበለቡበት ቀን ነው።
በሶቪየት ህብረት ከፍተኛ የሆነ ድጋፍ የመጣው የዚአድባሪ ጦር የእናት ሀገር ጥሪ እያለ በተሰበሰበው የኢትዮጵያ ጦረኛ " ካራማራ " ላይ ድባቅ ተመትቶ ወደ መጣበት ተመልሷል።
በጦርነቱ መጀመሪያ ሶቪየት ህብረት ሶማሊያን ስትደግፍ ነበር በኃላ ላይ ወደ ኢትዮጵያ አዘንብላ ለኢትዮጵያ ከፍተኛ እገዛ አድርጋለች ፤ ከኢትዮጵያ ጋር ጥሩ ግንኙነት የነበራት አሜሪካ ደግሞ ወደ ሶማሊያ ፊቷን አዙራ ነበር።
በጦርነቱ ኩባ፣ ሰሜን ኮሪያ፣ የመን እና ምሥራቅ ጀርመንን ጨምሮ ሌሎች አገራት አጋርነታቸውን ለኢትዮጵያ አሳይተዋል።
ከ16,000 በላይ የኩባ ወታደሮች በውጊያው እንደተሳተፉ መዛግብት ያሳያሉ። ደቡብ የመንም ጦሯን #ለኢትዮጵያ አሰልፋ ነበር።
በተለያየ የፖለቲካ የትግል ሁኔታ፣ በተለያየ ቅራኔ ውስጥ የነበሩ የኢትዮጵያ ሀይሎች ሁሉ ስለ ሀገር አንድ ሆነው የዚያድባሬን ጦር የመከቱበት የካራማራ ጦርነት የኢትዮጵያ አንድነት ዳግም በጉልህ የታየበት ስለመሆኑ ይነገርለታል፡፡
በየአመቱ የካቲት 26 ቀን የሚታሰበው የ " ካራማራ ድል " ዘንድሮም ለ47ኛ ጊዜ እየታሰበ ይገኛል፡፡
የካቲት 26 ቀን 1970 ዓ/ም የሱማሊያን ዚያድባሬ ጦር ለመመከት በካራማራ ጀግኖች የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጆች የህይወት መሰዋዕትነት ከፍለው ወራሪውን ጦር ከሀገር ያባረሩበት እና የሀገራቸውን ሰንደቅ ያውለበለቡበት ቀን ነው።
በሶቪየት ህብረት ከፍተኛ የሆነ ድጋፍ የመጣው የዚአድባሪ ጦር የእናት ሀገር ጥሪ እያለ በተሰበሰበው የኢትዮጵያ ጦረኛ " ካራማራ " ላይ ድባቅ ተመትቶ ወደ መጣበት ተመልሷል።
በጦርነቱ መጀመሪያ ሶቪየት ህብረት ሶማሊያን ስትደግፍ ነበር በኃላ ላይ ወደ ኢትዮጵያ አዘንብላ ለኢትዮጵያ ከፍተኛ እገዛ አድርጋለች ፤ ከኢትዮጵያ ጋር ጥሩ ግንኙነት የነበራት አሜሪካ ደግሞ ወደ ሶማሊያ ፊቷን አዙራ ነበር።
በጦርነቱ ኩባ፣ ሰሜን ኮሪያ፣ የመን እና ምሥራቅ ጀርመንን ጨምሮ ሌሎች አገራት አጋርነታቸውን ለኢትዮጵያ አሳይተዋል።
ከ16,000 በላይ የኩባ ወታደሮች በውጊያው እንደተሳተፉ መዛግብት ያሳያሉ። ደቡብ የመንም ጦሯን #ለኢትዮጵያ አሰልፋ ነበር።
በተለያየ የፖለቲካ የትግል ሁኔታ፣ በተለያየ ቅራኔ ውስጥ የነበሩ የኢትዮጵያ ሀይሎች ሁሉ ስለ ሀገር አንድ ሆነው የዚያድባሬን ጦር የመከቱበት የካራማራ ጦርነት የኢትዮጵያ አንድነት ዳግም በጉልህ የታየበት ስለመሆኑ ይነገርለታል፡፡
በየአመቱ የካቲት 26 ቀን የሚታሰበው የ " ካራማራ ድል " ዘንድሮም ለ47ኛ ጊዜ እየታሰበ ይገኛል፡፡