ሰበብ አስባብ እያበዛ በራሱ ተነሣሽነት ዝሙት እንዳልፈጸሙ በመናገር ድንግል መሆን እንደ ነበረባቸው ወይም እንደ ሆኑ እንደሚናገሩ ሰዎች እግዚአብሔር የሚያፍርባቸው ስዎች የሉም።
ለሌሎች ሰዎች ያልተደረገ ገቢረ ተአምር እንዲደረግልን ማለት በራሳችን ስሕተት ያጠፋነውን ድንጋሌ ሥጋ እንዲመለስልን የምንሻ እኛ ከእነሱ የተለየ በጎ ሥራ ምን ሠርተን ነው? ይህ ሐሳብ በእውነት የትዕቢት ሐሳብ ነው በዚህ መልኩ በትዕቢት ማሰብ እንደማይገባ ደግሞ «እንደ ባለ አእምሮ እንዲያስብ እንጂ ማሰብ ከሚገባው አልፎ በትዕቢት እንዳያስብ በመካከላችሁ ላለው ለእያንዳንዱ በተሰጠኝ ፀጋ እናገራለሁ::» ሮሜ12፥3 በማለት ሐዋርያው ምክር ለግሷል፡፡
መደንገል እስከ መቼ?
ድንግልናን ስለመጠበቅ ሲነሣ ብዙ ጥያቄዎች በሕሊና መውጣትና መውረዳቸው አይቀርም፡፡ ከእነሱም ውስጥ አንዱ እስከ መቼ? የሚል ነው:: የዚህ ጥያቄ መልስ እንደ ሰዉ የአኗኗር ዘይቤ ይለያያል:፡ ለአንዱ ጋብቻውን እስኪፈጽም ድረስ ሲሆን ለሌላው ደግሞ ለዘለዓለም ይሆናል፡፡ ይህም ማለት ለሚመነኩሱ ሰዎች እስከ ዕድሜያቸው ፍጻሜ ድረስ ማለት ነው::
እስከ ዕድሜ ልክ መደንገል
ድንግልናቸውን እስከ ሞት ድረስ መጠበቅ የሚኖርባቸው በድንግልና የመነኮሱ መነኮሳት ናቸው:: ምንኩስና ከሴት ርቆ እስክ ሕይወት ፍጻሜ ለመኖር የሚደረግ ውሳኔ ነውና፡፡በእርግጥ ምንኩስና ድንግሌ ሥጋ ያላቸው ሰዎች ብቻ የሚጓዙበት ጐዳና አይደለም:: ባለ ትዳር የነበሩ ወይም ሳያገበ ለዝሙት ተጋልጠው ድንጋሌ ሥጋቸውን ያጡ ብዙ ሰዎችም በንስሐ ተመልሰው ይኖሩበታል:: ይህም ቢሆን እንደ ቀላል የሚታይ ውሳኔ አይደለም:: ነገር ግን ምንኩስና የዓለምን ኑሮ እንደ ልብ ኖረውት ሲስለች ብቻ የሚገባበት አድርጐ ማሰብ ስሕተት ነው፡፡
ምንኩስና በድንግልና ሲሆን ብዙ ጸጋና ክብር ያመጣል፡፡ በቤተ ክርስቲያን ከመመንኮስ በተጨማሪ የግድ ድንግል ሆኖ መገኘትን የሚጠይቁ ብዙ ታላላቅ መንፈሳዊ የሹመት ደረጃዎችና የአኗኗር ዘይቤዎች ይገኛሉ፡፡
በድንግልና መመንኮስ ጣዕመ ዓለምን ሳይቀምሱ በመሆኑ ከምንኩስናም በኋላ ለሚኖሩት የንጽሕና ኑሮ አጋዥነት ይኖረዋል፡፡ ምክንያቱም ከመነኮሱበት ዓላማ ጋር የማይስማማ በልቡናቸው የሚቀር የዓለማዊ ኑሮ አሻራ ባለመኖሩ ነው:: «ያላዩት አገር አያናፍቅም» ይባል የለ?
በእርግጥ ይህን የመሰለ የምናኔ ኑሮ ለመኖር ስጦታ ያስፈልጋል፡፡ «ነገር ግን ለእያንዳንዱ ከእግዚአብሔር ዘንድ ስጦታ አለው፥ አንዱ እንደዚህ ሁለተኛውም እንደዚያ› በማለት ቅዱስ ጳውሎስ እንደተናገረው መመንኮስ የተሰጠው ይኖራል፡ ማግባትም የተሰጠው ይኖራል:: 1ቆሮ7÷27
ምንም እንኳን በጋብቻም ሆነ በምንኩስና መኖር ሁለቱም የእግዚአብሔር ስጦታዎች ቢሆኑም በጋብቻ መኖር ለሁሉ የተሰጠ ሲሆን ምንኩስና ግን መመረጥና መታደል የሚጠይቅ ነው:: ይህን በተመለከተ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ «ይህ ነገር ለተሰጣቸው እንጂ ለሁሉ አይደለም....ሊቀበለው የሚችል ይቀበለው::» በማለት ተናግሯል:: ማቴ19፥11
«ለአባታችን ለቅዱስ ጴጥሮስ የመንግሥተ ሰማያት መክፈቻ፣ ለዮሐንስ ደግሞ ድንግልና፥ ለአባታችን ለጳውሎስም የቤተ ክርስቲያን ብርሃኗ እርሱ ነውና መልእክታትን አብዝቶ መጻፍ ተሰጠው› በማለት ሥርዓተ ቅዳሴ በስም ለተጠቀሱት ሐዋርያት የመንግሥተ ሰማያት መክፈቻ! በድንግልና መኖርና መልእክታትን መጻፍ ለእያንዳንዳቸው እንደ ተሰጣቸው ይገልጻል:: ከዚህም በድንግልና መኖር ለጥቂቶች የሚሰጥ ጸጋ መሆኑን መረዳት ይቻላል፡፡
ሰው ሁሉ በተሰጠው ጸጋ መኖር ይገባዋል፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውለስ በድንግልና መኖር (ምንኩስና) የተሰጠው በድንግልና ጋብቻም የተሰጠው በትዳሩ ጸንቶ እንዲኖር «ወንድሞች ሆይ እያንዳንዱ በተጠራበት እንደዚህ ሆኖ በእግዚአብሔር ዘንድ ይኑር፡፡» በማለት መክሯል:: 1ቆሮ7÷24
ድንግልናን በሕይወት ዘመን በሙሉ ጠብቆ በምንኩስና መኖር ከስጦታነቱ በተጨማሪ በፈቃደኝነት ሊደረግ የሚገባው ነገር ነው እንጃ. የሚገደዱበት ተግባር አይደለም፡፡ ሐዋረያው ድንግልናዊ ኑሮ ውዴታ እንጂ ትእዛዝ አለመሆኑን ሲገልጽ ‹‹ስለ ደናግልም የጌታ ትእዛዝ የለኝም» በማለት ተናግሯል::
በድንግልና ተወስኖ ለመኖርም ሆነ ወደ ጋብቻ ለመሄድ የድንግልና መኖር አስፈላጊ በመሆኑ ድንግልናን ጠብቆ ለመኖር ስጦታችን የትኛው እንደሆነ ማወቅም አያስፈልገንም፡ በድንግልና ኖረን ከመነኮስን እሰይ ያሰኛል፡ ካገባንም ይበል የሚያሰኝ ነውና ድንግልናን ክወዲሁ ጠብቆ መኖር ይገባል፡፡
እስከ ጋብቻ ድረስ ድንግልናውን ጠብቆ ኖሮ ያገባ ሰው ሐዋርያው እንደተናገረው መልካም አደረገ:: 1ቆሮ7÷38 የታዘዘውን በሚገባ ፈጽሟልና ክበጎ ባርያዎች ጋር ይቆጠራል:: ያላገባ ወይም መላ ዘመኑን በድንግልና ለመኖር የወሰነ ደግሞ ከታዘዘው በላይ የትሩፋት ሥራ ሠርቷልና የተሻለ አደረገ፡፡ 1ቆሮ7÷38
በጎ ሎሌን ጌታው ሸማ አጥበህ፤ ማገር ቆርጠህ ና ብሎ ያዘዋል:: እርሱ ግን ጌታዬ አይችልም በማለት አዝኖልኝ ነው እንጂ
ዓሣን ለወጥ፣ ለማገር ደግሞ ልጥ ጨምሬ ይዤ ብሄድ ይከፋልን? ብሎ ልብሱን ካጠበና ማገሩን ከቆረጠ በኋላ ዓሣውንና ልጡን ጨምሮ ይመለሳል:: እንደዚሁ ሁሉ መነኮሳትም የፈጣሪ ታማኝ ባሪያዎች ናቸው:: ስለዚህ ፈጣሪ ሚስት አግብታችሁ፣ አሥራት፣ በኩራቱንና ቀዳምያቱን አውጥታችሁ፣ ሥጋውን ደሙን በሚገባ ተቀብላችሁ ኑሩ ቢላቸው ሚስት ማግባትን ተዉ፡ ይህንንም ያደረጉት ባሕሪያቸው ደካማ ነውና አይቻላቸውም ብሎ ፈጣሪያችን አዝኖልን ነው እንጂ ከሕገ ሥጋ ሕገ ነፍስ፣ ከሕገ እንስሳ ሕገ መላእክት እንደሚበልጥ የታወቀ አይደለምን? በማለት ስለ እግዚአብሔር ፍቅር ብለው በበጎ ፈቃደኝነት ነው እንጂ ተገደው አይደለም:: በዚህ ሥራቸው የተሻለ አድርገዋልና እንደ ታማኝ ሎሌ ይመሰገናሉ አንጂ አይነቀፉም:: ማቴ13፥4-8 (ትርጓሜ)
መላ ዘመንን ከሴት ርቆ ንጽሕ ጠብቆ በድንግልና መኖር በግዴታ ወይም በትእዛዝ የሚደረግ ሳይሆን ከፍቅረ እግዚአብሔር የተነሣ በፈቃደኝነት የሚደረግ መሆኑን «በእናት ማሕፀን ጃንደረቦች ሆነው የተወለዱ አሉ፥ ሰውም የሰለባቸው ጃንደረቦች አሉ፥ ስለ መንግሥተ ሰማያትም ራሳቸውን የሰለቡ ጃንደረቦች አሉ» በማለት ጌታችን የተናገረው ቃል ያስረዳል:: ማቴ 19÷12
«በእናት ማሕፀን ጃንደረቦች ሆነው የተወለዱ አለ› ማለት አንደ ኤርምያስ እና ዮሐንስ መጥምቅ ከማሕፀን ጀምሮ በምናኔ ለምንኩስናና ለድንግልዊ ኑሮ ተመርጠው የተለዩ አሉ ማለት ነው፡፡ “በሆድ ሳልሠራህ አውቄሃለሁ፥ ከማሕፀንም ሳትወጣ ቀድሼሃለሁ› እንዳለው ማለት ነው:: ኤር1፥5
«ሰውም የሰለባቸው ጃንደረቦች አሉ» ማለት መምህራን መክረውና አስተምረው ንጹሐን ያደረጓቸው ለድንግልናዊ ኑሮ ያበቋቸው አሉ ማለት ነው:: ለምሳሌ:- ሙሴ ኢያሱን፣ ኤልያስ ደግሞ ኤልሳዕን ቀርጸው ለዚህ ዓይነት የመዓርግ ኑሮ አብቅተዋቸዋል፡፡
«ስለ መንግሥተ ሰማያትም ራሳቸውን የሰለቡ ጃንደረቦች አሉ» ማለት ፈጣሪያችን አይችሉትም በማለት አዝኖልን ነው እንጂ ሳያገቡ መኖር የተሻለ ነው በማለት በራሳቸው ፈቃድ ድንግልናቸውን ጠብቀው ከሴት ርቀው መንግሥተ ሰማያትን የሚጠባበቁ አሉ ማለት ነው፡፡
ለሌሎች ሰዎች ያልተደረገ ገቢረ ተአምር እንዲደረግልን ማለት በራሳችን ስሕተት ያጠፋነውን ድንጋሌ ሥጋ እንዲመለስልን የምንሻ እኛ ከእነሱ የተለየ በጎ ሥራ ምን ሠርተን ነው? ይህ ሐሳብ በእውነት የትዕቢት ሐሳብ ነው በዚህ መልኩ በትዕቢት ማሰብ እንደማይገባ ደግሞ «እንደ ባለ አእምሮ እንዲያስብ እንጂ ማሰብ ከሚገባው አልፎ በትዕቢት እንዳያስብ በመካከላችሁ ላለው ለእያንዳንዱ በተሰጠኝ ፀጋ እናገራለሁ::» ሮሜ12፥3 በማለት ሐዋርያው ምክር ለግሷል፡፡
መደንገል እስከ መቼ?
ድንግልናን ስለመጠበቅ ሲነሣ ብዙ ጥያቄዎች በሕሊና መውጣትና መውረዳቸው አይቀርም፡፡ ከእነሱም ውስጥ አንዱ እስከ መቼ? የሚል ነው:: የዚህ ጥያቄ መልስ እንደ ሰዉ የአኗኗር ዘይቤ ይለያያል:፡ ለአንዱ ጋብቻውን እስኪፈጽም ድረስ ሲሆን ለሌላው ደግሞ ለዘለዓለም ይሆናል፡፡ ይህም ማለት ለሚመነኩሱ ሰዎች እስከ ዕድሜያቸው ፍጻሜ ድረስ ማለት ነው::
እስከ ዕድሜ ልክ መደንገል
ድንግልናቸውን እስከ ሞት ድረስ መጠበቅ የሚኖርባቸው በድንግልና የመነኮሱ መነኮሳት ናቸው:: ምንኩስና ከሴት ርቆ እስክ ሕይወት ፍጻሜ ለመኖር የሚደረግ ውሳኔ ነውና፡፡በእርግጥ ምንኩስና ድንግሌ ሥጋ ያላቸው ሰዎች ብቻ የሚጓዙበት ጐዳና አይደለም:: ባለ ትዳር የነበሩ ወይም ሳያገበ ለዝሙት ተጋልጠው ድንጋሌ ሥጋቸውን ያጡ ብዙ ሰዎችም በንስሐ ተመልሰው ይኖሩበታል:: ይህም ቢሆን እንደ ቀላል የሚታይ ውሳኔ አይደለም:: ነገር ግን ምንኩስና የዓለምን ኑሮ እንደ ልብ ኖረውት ሲስለች ብቻ የሚገባበት አድርጐ ማሰብ ስሕተት ነው፡፡
ምንኩስና በድንግልና ሲሆን ብዙ ጸጋና ክብር ያመጣል፡፡ በቤተ ክርስቲያን ከመመንኮስ በተጨማሪ የግድ ድንግል ሆኖ መገኘትን የሚጠይቁ ብዙ ታላላቅ መንፈሳዊ የሹመት ደረጃዎችና የአኗኗር ዘይቤዎች ይገኛሉ፡፡
በድንግልና መመንኮስ ጣዕመ ዓለምን ሳይቀምሱ በመሆኑ ከምንኩስናም በኋላ ለሚኖሩት የንጽሕና ኑሮ አጋዥነት ይኖረዋል፡፡ ምክንያቱም ከመነኮሱበት ዓላማ ጋር የማይስማማ በልቡናቸው የሚቀር የዓለማዊ ኑሮ አሻራ ባለመኖሩ ነው:: «ያላዩት አገር አያናፍቅም» ይባል የለ?
በእርግጥ ይህን የመሰለ የምናኔ ኑሮ ለመኖር ስጦታ ያስፈልጋል፡፡ «ነገር ግን ለእያንዳንዱ ከእግዚአብሔር ዘንድ ስጦታ አለው፥ አንዱ እንደዚህ ሁለተኛውም እንደዚያ› በማለት ቅዱስ ጳውሎስ እንደተናገረው መመንኮስ የተሰጠው ይኖራል፡ ማግባትም የተሰጠው ይኖራል:: 1ቆሮ7÷27
ምንም እንኳን በጋብቻም ሆነ በምንኩስና መኖር ሁለቱም የእግዚአብሔር ስጦታዎች ቢሆኑም በጋብቻ መኖር ለሁሉ የተሰጠ ሲሆን ምንኩስና ግን መመረጥና መታደል የሚጠይቅ ነው:: ይህን በተመለከተ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ «ይህ ነገር ለተሰጣቸው እንጂ ለሁሉ አይደለም....ሊቀበለው የሚችል ይቀበለው::» በማለት ተናግሯል:: ማቴ19፥11
«ለአባታችን ለቅዱስ ጴጥሮስ የመንግሥተ ሰማያት መክፈቻ፣ ለዮሐንስ ደግሞ ድንግልና፥ ለአባታችን ለጳውሎስም የቤተ ክርስቲያን ብርሃኗ እርሱ ነውና መልእክታትን አብዝቶ መጻፍ ተሰጠው› በማለት ሥርዓተ ቅዳሴ በስም ለተጠቀሱት ሐዋርያት የመንግሥተ ሰማያት መክፈቻ! በድንግልና መኖርና መልእክታትን መጻፍ ለእያንዳንዳቸው እንደ ተሰጣቸው ይገልጻል:: ከዚህም በድንግልና መኖር ለጥቂቶች የሚሰጥ ጸጋ መሆኑን መረዳት ይቻላል፡፡
ሰው ሁሉ በተሰጠው ጸጋ መኖር ይገባዋል፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውለስ በድንግልና መኖር (ምንኩስና) የተሰጠው በድንግልና ጋብቻም የተሰጠው በትዳሩ ጸንቶ እንዲኖር «ወንድሞች ሆይ እያንዳንዱ በተጠራበት እንደዚህ ሆኖ በእግዚአብሔር ዘንድ ይኑር፡፡» በማለት መክሯል:: 1ቆሮ7÷24
ድንግልናን በሕይወት ዘመን በሙሉ ጠብቆ በምንኩስና መኖር ከስጦታነቱ በተጨማሪ በፈቃደኝነት ሊደረግ የሚገባው ነገር ነው እንጃ. የሚገደዱበት ተግባር አይደለም፡፡ ሐዋረያው ድንግልናዊ ኑሮ ውዴታ እንጂ ትእዛዝ አለመሆኑን ሲገልጽ ‹‹ስለ ደናግልም የጌታ ትእዛዝ የለኝም» በማለት ተናግሯል::
በድንግልና ተወስኖ ለመኖርም ሆነ ወደ ጋብቻ ለመሄድ የድንግልና መኖር አስፈላጊ በመሆኑ ድንግልናን ጠብቆ ለመኖር ስጦታችን የትኛው እንደሆነ ማወቅም አያስፈልገንም፡ በድንግልና ኖረን ከመነኮስን እሰይ ያሰኛል፡ ካገባንም ይበል የሚያሰኝ ነውና ድንግልናን ክወዲሁ ጠብቆ መኖር ይገባል፡፡
እስከ ጋብቻ ድረስ ድንግልናውን ጠብቆ ኖሮ ያገባ ሰው ሐዋርያው እንደተናገረው መልካም አደረገ:: 1ቆሮ7÷38 የታዘዘውን በሚገባ ፈጽሟልና ክበጎ ባርያዎች ጋር ይቆጠራል:: ያላገባ ወይም መላ ዘመኑን በድንግልና ለመኖር የወሰነ ደግሞ ከታዘዘው በላይ የትሩፋት ሥራ ሠርቷልና የተሻለ አደረገ፡፡ 1ቆሮ7÷38
በጎ ሎሌን ጌታው ሸማ አጥበህ፤ ማገር ቆርጠህ ና ብሎ ያዘዋል:: እርሱ ግን ጌታዬ አይችልም በማለት አዝኖልኝ ነው እንጂ
ዓሣን ለወጥ፣ ለማገር ደግሞ ልጥ ጨምሬ ይዤ ብሄድ ይከፋልን? ብሎ ልብሱን ካጠበና ማገሩን ከቆረጠ በኋላ ዓሣውንና ልጡን ጨምሮ ይመለሳል:: እንደዚሁ ሁሉ መነኮሳትም የፈጣሪ ታማኝ ባሪያዎች ናቸው:: ስለዚህ ፈጣሪ ሚስት አግብታችሁ፣ አሥራት፣ በኩራቱንና ቀዳምያቱን አውጥታችሁ፣ ሥጋውን ደሙን በሚገባ ተቀብላችሁ ኑሩ ቢላቸው ሚስት ማግባትን ተዉ፡ ይህንንም ያደረጉት ባሕሪያቸው ደካማ ነውና አይቻላቸውም ብሎ ፈጣሪያችን አዝኖልን ነው እንጂ ከሕገ ሥጋ ሕገ ነፍስ፣ ከሕገ እንስሳ ሕገ መላእክት እንደሚበልጥ የታወቀ አይደለምን? በማለት ስለ እግዚአብሔር ፍቅር ብለው በበጎ ፈቃደኝነት ነው እንጂ ተገደው አይደለም:: በዚህ ሥራቸው የተሻለ አድርገዋልና እንደ ታማኝ ሎሌ ይመሰገናሉ አንጂ አይነቀፉም:: ማቴ13፥4-8 (ትርጓሜ)
መላ ዘመንን ከሴት ርቆ ንጽሕ ጠብቆ በድንግልና መኖር በግዴታ ወይም በትእዛዝ የሚደረግ ሳይሆን ከፍቅረ እግዚአብሔር የተነሣ በፈቃደኝነት የሚደረግ መሆኑን «በእናት ማሕፀን ጃንደረቦች ሆነው የተወለዱ አሉ፥ ሰውም የሰለባቸው ጃንደረቦች አሉ፥ ስለ መንግሥተ ሰማያትም ራሳቸውን የሰለቡ ጃንደረቦች አሉ» በማለት ጌታችን የተናገረው ቃል ያስረዳል:: ማቴ 19÷12
«በእናት ማሕፀን ጃንደረቦች ሆነው የተወለዱ አለ› ማለት አንደ ኤርምያስ እና ዮሐንስ መጥምቅ ከማሕፀን ጀምሮ በምናኔ ለምንኩስናና ለድንግልዊ ኑሮ ተመርጠው የተለዩ አሉ ማለት ነው፡፡ “በሆድ ሳልሠራህ አውቄሃለሁ፥ ከማሕፀንም ሳትወጣ ቀድሼሃለሁ› እንዳለው ማለት ነው:: ኤር1፥5
«ሰውም የሰለባቸው ጃንደረቦች አሉ» ማለት መምህራን መክረውና አስተምረው ንጹሐን ያደረጓቸው ለድንግልናዊ ኑሮ ያበቋቸው አሉ ማለት ነው:: ለምሳሌ:- ሙሴ ኢያሱን፣ ኤልያስ ደግሞ ኤልሳዕን ቀርጸው ለዚህ ዓይነት የመዓርግ ኑሮ አብቅተዋቸዋል፡፡
«ስለ መንግሥተ ሰማያትም ራሳቸውን የሰለቡ ጃንደረቦች አሉ» ማለት ፈጣሪያችን አይችሉትም በማለት አዝኖልን ነው እንጂ ሳያገቡ መኖር የተሻለ ነው በማለት በራሳቸው ፈቃድ ድንግልናቸውን ጠብቀው ከሴት ርቀው መንግሥተ ሰማያትን የሚጠባበቁ አሉ ማለት ነው፡፡