†
† 🕊 መንፈሳዊው መሰላል 🕊 †
💖
[ ዓ ለ ም ን ስ ለ መ ተ ው ! ]
[ ክፍል ስድስት ]
▬▬▬▬▬▬ ♱ ▬▬▬▬▬▬
❝ አንዳንዶች ጡቦችን በዓለቶች ላይ ገነቡ፡፡ ሌሎች በገላጣ መሬት ላይ ዐምዶችን አቆሙ፡፡ ሌሎችም አጭር ርቀት ተጉዘው ጡንቻዎቻቸውና ጅማቶቻቸው ፈጥኖ የሚግልባቸው አሉ፡፡ ማስተዋል የሚችል ሁሉ ይህን ምሳሌአዊ ቃል ያስተውል፡፡
ምክንያቱም ጊዜአችን አጭር ነውና በጊዜ ሞታችን ያለ ፍሬና በሚያጠፋ ረሀብ ሆነን እንዳንገኝ በአምላካችንና በንጉሣችን እንደ ተጠሩ ሰዎች ሆነን መንገዳችንን በጉጉት እንሩጥ፡፡ ከዘመቻው በኋላ ተገቢውን የአገልግሎታችን ዋጋ የምንሻ ነንና ወታደሮች ንጉሣቸውን ደስ እንደሚያሰኙት ጌታን ደስ እናሰኘው፡፡ አራዊትን ከምንፈራበት ባላነሰ ጌታን እንፍራው፡፡ እግዚአብሔርን ሳይፈሩ ለመስረቅ ይሄዱ የነበሩ ሰዎችን ተመለከትሁ ፣ ነገር ግን እግዚአብሔርን መፈራታቸው እንስሳትን እንደ መፍራታቸው መጠን ሊደርስ አልቻለም ነበርና የውሾችን ጩኸት ሲሰሙ በአንዴ ወደ ኋላ ተመለሱ፡፡
ቢያንስ ባልንጀሮቻችንን የምናከብረውን ያህል እግዚአብሔርን እንውደደው፡፡ ዘወትር እግዚአብሔርን የሚያሳዝኑና ይህም በመሆኑ ጥቂት እንኳ የማያስጨንቃቸው ሰዎችን ተመለከትሁ፡፡
እነዚያኑ ራሳቸው ሰዎች ወዳጆቻቸውን በማይረባ ጉዳይ ሲያስቆጡና ቀጥሎም ሁሉንም ዓይነት ማስመሰያ በማድረግ ፣ በማንኛውም ዘዴ ፣ በማንኛውም መሥዋዕት ፣ በማንኛውም ይቅርታ ፣ በሁለቱም በራሳቸውም ሆነ በወዳጆቻቸውና በዘመዶቻቸው በኩል የቀደመ ወዳጅነታቸውን መልሰው ለማግኘት ብለው ያልተቆጠቡ ስጦታዎችን መሥዋዕት ሲያደርጉ ተመለከትሁ፡፡ ❞
[ ዮሐንስ ክሊማኮስ [ ቅዱስ ዮሐንስ ዘሰዋስው ]
🕊 💖 🕊
† 🕊 መንፈሳዊው መሰላል 🕊 †
💖
[ ዓ ለ ም ን ስ ለ መ ተ ው ! ]
[ ክፍል ስድስት ]
▬▬▬▬▬▬ ♱ ▬▬▬▬▬▬
❝ አንዳንዶች ጡቦችን በዓለቶች ላይ ገነቡ፡፡ ሌሎች በገላጣ መሬት ላይ ዐምዶችን አቆሙ፡፡ ሌሎችም አጭር ርቀት ተጉዘው ጡንቻዎቻቸውና ጅማቶቻቸው ፈጥኖ የሚግልባቸው አሉ፡፡ ማስተዋል የሚችል ሁሉ ይህን ምሳሌአዊ ቃል ያስተውል፡፡
ምክንያቱም ጊዜአችን አጭር ነውና በጊዜ ሞታችን ያለ ፍሬና በሚያጠፋ ረሀብ ሆነን እንዳንገኝ በአምላካችንና በንጉሣችን እንደ ተጠሩ ሰዎች ሆነን መንገዳችንን በጉጉት እንሩጥ፡፡ ከዘመቻው በኋላ ተገቢውን የአገልግሎታችን ዋጋ የምንሻ ነንና ወታደሮች ንጉሣቸውን ደስ እንደሚያሰኙት ጌታን ደስ እናሰኘው፡፡ አራዊትን ከምንፈራበት ባላነሰ ጌታን እንፍራው፡፡ እግዚአብሔርን ሳይፈሩ ለመስረቅ ይሄዱ የነበሩ ሰዎችን ተመለከትሁ ፣ ነገር ግን እግዚአብሔርን መፈራታቸው እንስሳትን እንደ መፍራታቸው መጠን ሊደርስ አልቻለም ነበርና የውሾችን ጩኸት ሲሰሙ በአንዴ ወደ ኋላ ተመለሱ፡፡
ቢያንስ ባልንጀሮቻችንን የምናከብረውን ያህል እግዚአብሔርን እንውደደው፡፡ ዘወትር እግዚአብሔርን የሚያሳዝኑና ይህም በመሆኑ ጥቂት እንኳ የማያስጨንቃቸው ሰዎችን ተመለከትሁ፡፡
እነዚያኑ ራሳቸው ሰዎች ወዳጆቻቸውን በማይረባ ጉዳይ ሲያስቆጡና ቀጥሎም ሁሉንም ዓይነት ማስመሰያ በማድረግ ፣ በማንኛውም ዘዴ ፣ በማንኛውም መሥዋዕት ፣ በማንኛውም ይቅርታ ፣ በሁለቱም በራሳቸውም ሆነ በወዳጆቻቸውና በዘመዶቻቸው በኩል የቀደመ ወዳጅነታቸውን መልሰው ለማግኘት ብለው ያልተቆጠቡ ስጦታዎችን መሥዋዕት ሲያደርጉ ተመለከትሁ፡፡ ❞
[ ዮሐንስ ክሊማኮስ [ ቅዱስ ዮሐንስ ዘሰዋስው ]
🕊 💖 🕊