ልሣነ አምሐራ ሚዲያ


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic
Category: Politics


በዚህ ቻናል ፈጣንና ወቅታዊ የአማራ ፋኖ እለታዊ ዘገባዎች እንድሁም ፈጣን ዜናዎች ይቀርባሉ።
ለማንኛውም ጥቆማ በ @lisaneamhara ያናግሩን‼️

Related channels  |  Similar channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Category
Politics
Statistics
Posts filter




የቀኝ አዝማች ይታገሱ አረጋው ተወርዋሪ ክፍለ ጦር የመጀመሪያ ጉባኤውን ማካሄዱ ተገለፀ::

በዋርካው ምሬ ወዳጆ የሚመራው የአማራ ፋኖ በወሎ (ቤተ አምሓራ) ቅርንጫፍ የሆነው ምዕራብ ወሎ ኮር ቀኝ አዝማች ይታገሱ አረጋው ተወርዋሪ ክፍለ ጦር የምዕራብ ወሎ ቀጠና ውስጥ ባሉ 11 ወረዳዎች ውስጥ የሚንቀሳቀስ ሲሆን ከጃማ እስከ ሳይንት እንድሁም ለጋምቦ እና ከላላ ድረስ ሌሎች ወረዳዎችንም አካሎ ከየአቅጣጫው በተውጣጡ ፋኖዎች የተዋቀረ ክፍለ ጦር ነው ተብሏል::

ክፍለ ጦሩ በኮማንዶዎች እንደሚመራም ነው ለማወቅ የቻልነው::

የጀግኖች ስብስብ የሆነውና በንፁሁ ታጋይ ስም የተሰየመው የዚህ ክፍለ ጦር አንዱ ከፍተኛ አመራር ጥር 6 ቀን 2017 ዓ/ም በርካቶችን ጥሎ መስዋዕትነት ሲከፍል ከ4 ወረዳዎች በውጭጩ የመጣው ጠላት ከ60 በላይ ኃይሉ ተደምስሶበታል::

በጥር ስድስቱ ውጊያ የተወርዋሪ ክፍለ ጦሩ ወታደራዊ አዛዥ ኮማንዶ ተመስገን አለምነው መስዋዕትነት የከፈለው ከበባ ሰብሮ እና በርካቶችን በመጣል ጀብዱ ፈጽሞ መሆኑን የምዕራብ ወሎ ኮር ባወጣው የሀዘን መግለጫ ላይ አስታውቋል::

የምዕራብ ወሎ ኮር አዛዥ አርበኛ አደም አሊ በተገኘበት ጉባኤውን ያካሄደው ተወርዋሪ ክፍለ ጦሩ በጎደሉ አመራሮች ቦታ አዳዲሶችን ተክቷል::

ጎርጎራ ቲቪ - ከእውነት ጋር
የጠብመንጃ አንጋቾች ድምጽ




የመብረቁ ተፈራ ኮማንዶና አንደኛ ሻለቃ ጥምር ጦር አራጢ (ወይንውሀ መገንጠያ) ላይ ጠላትን እየረፈረፉት ነው።


የደብረ ኤልያስ ቀስተ ደመና ብርጌድ ፋኖዎች በጠላት ላይ ድልን ተቀዳጁ!
==============================================

ራሱን መከላከያ እያለ የሚጠራው የፋሽስታዊው አብይ አህመድ ወንበር አስጠባቂ የሽብር ቡድን ደብረ ኤልያስ ከተማ ገብቶ በጀግኖቹ የአማራ የቁርጥ ቀን ልጆች መገረፍ ከጀመረ ድፍን ሁለት ወራት አልፈዋል።በእነዚህ ጊዜያት ውስጥ በርካታ የወራሪው ጦር እስከ ወዲያኛው ተሸኝቷል።በርካቶችም ቆስለዋል።
ቀደም ብሎ ካስገባው የጠላት ኃይል በተጨማሪ ከሰሞኑ በርካታ ሰራዊት ማስገባቱ ይታወቃል።ይህም የወረዳውን ገጠራማ አካባቢ ለመቆጣጠርና በዋናነት ግን የብሔረ ብጹዓን አጼ መልክዓ ስላሴ አንድነት ገዳምን በድጋሚ ለማውደም እየተደረገ ያለ እንቅስቃሴ ነው።

ዛሬም ከደብረ ኤልያስ ከተማ ሙሉ ጦሩንና መሳርያዎቹን ጭኖ ወደ ጓይ መገንጠያ በተንቀሳቀሰው የጠላት ኃይል ላይ ጀግኖቹ የቀስተ ደመና ብርጌድ ፋኖዎች ከፍተኛ የሆነ ውጊያን በመክፈት ታላቅ ኪሳራን አድርሰውበታል።በአርበኛ ድረስ አለማየሁና አርበኛ ነጋ መኮንን የተመራው ይህ ውጊያ የጠላትን ቅስም የሰበረ ነበር።ጠላት በዙ-23ና በሞርተር የታገዘ ውጊያ ቢያደርግም ቀስተኞቹ ግን ከምሽጋቸው ፍንክች ሊሉ አልቻሉም።

በዚህ ውጊያ በወገን በኩል ቀላል ቁስለኛ ከሆኑ ጥቂት ፋኖዎቻችን ውጭ የተከፈለ መስዋዕትነት የሌለ ሲሆን በጠላት በኩል ግን 16 አምቡላንስና ፓትሮል በቁጠር ደረጃ ከ112 በላይ ቁስለኛ የተነሳ ሲሆን የሟቹን መጠን ግን በተረጋገጠ መረጃ ማወቅ አልተቻለም።ምክንያቱም በየቦታውና ምሽግ ባደረጉት የሳሰር ቤተ ክርስቲያን ይቀብሩት ስለነበር ነው።ይሁን እንጅ ከቁስለኛው በላይ ሊሆን እንደሚችል ግን የአካባቢው ነዋሪዎች ገልጸውልናል።

ጠላት በአሁኑ ሰዓት በጎፍጭማ ታዳጊ ከተማና የቀጋት ቤተ ክርስቲያን ላይ የሚገኝ ሲሆን የትኩረት አቅጣጫውም የብሔረ ብጹዓን አጼ መልክዓ ሥላሴ አንድነት ገዳምን በድጋሚ ለማውደም እንደሆነ ይታወቃል።

ደብረ ኤልያስ ግን ጠላትን ውጣ ማስቀረቷን ቀጥላለች ትቀጥላለችም።

ድል ለሕዝባችን!
ክብር ለሰማዕቶቻችን!
አዲስ ትውልድ፣አዲስ ተሰፋ፣አዲስ አስተሳሰብ!

ፋኖ ኢ/ር ዘመን ባሳዝነው
የአማራ ፋኖ በጎጃም የቀኝ ጌታ ዮፍታሔ ንጉሴ 6ኛ ክፍለ ጦር
የቀስተደመና ብርጌድ ፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ

ጥር 19/2017 ዓ.ም




ጀግናው ተሰውቷል:: እኔም የሰማሁት ዘግይቼ ነው!!

ለነገሩ እሱ ቢሰዋም የልቡን ሰርቶ ነው:: በአጠቃላይ ሰሞኑን በአማራ ሳይንት ቀጠና በሰፊው የምዕራብ ወሎ ግንባር ነገሮች በፍጥነት ተቀይረዋል::

2 መከላከያ እና ሚሊሻዎች የአማራ ፋኖ በወሎ ምዕራብ ወሎ ኮር አማራ ሳይንት መቅደላ ክፍለ ጦር አትሮንስ ብርጌድን በመሀል ሳይንት ወረዳ ግንባር ተቀላቅለው ደማቅ አቀባበል ተደርጎላቸዋል የሚል መረጃ አሁን ደርሶኛል:: የአትሮንስ ብርጌድ አዛዥ ፋኖ ጎሹ ታረቀኝ የጠላትን አቅም እያሽመደመደው ነው:: ቁልፍ አዋጊዎችን አምጥቶበታል::

ይህ በእንዲህ እንዳለ በዚሁ በአማራ ሳይንት ቀጠና በለጋምቦ ወረዳ ግንባር ገነቴ አቅራቢያ ሰሞኑን ታሪክ ሲሰራ ሰንብቶ ኖሯል:: ጥር 6 ለ7 ሌሊት በተደረገ ጦርነት የአማራ ፋኖ በወሎ ምዕራብ ወሎ ኮር ቀኝ አዝማች ይታገሱ አረጋው ተወርዋሪ ክፍለ ጦር አደራጅ ኮሚቴ አባል እና የክፍለ ጦሩ ስራ አስፈጻሚ የሆነው ኮማንዶ ተመስገን ሳይንቴው ጀብዱ ፈፅሞ በጀግንነት ተሰውቷል::

የኮሩ ጊዜያዊ ኮሚቴው ተሰባስቦ አዳዲስ ስራ አስፈጻሚዎችን በመሰየም በሰራዊቱ ሊያፀድቅ ከየቦታው ተሰባስቦ ለጋምቦ ወረዳ እና ወግዲ ወረዳ ድንበር አቅራቢያ የምትገኝ ብስቁልል የምትባል መንደር ውስጥ ከኮሩ አዛዥ አርበኛ አደም አሊ ጋር ውይይት ላይ ሳሉ የኮሩ አዛዥ አጃቢ የነበረና ከቀናት በፊት ከድቶ ወደ መንግስት የገባ የየሹም አካባቢ ተወላጅ ባንዳ ከወግዲ ወረዳ በኩል ጠላትን እየመራ መጥቶ ከሌሎች የጎረቤት ወረዳዎችም ተጨማሪ ኃይል በቦታው በመድረስ ሌሊት ከባባ ቢፈፅምም ጀግኖች በታትነውታል::

ሞት አይፈሬው ሳይንቴ ከ4 ወረዳዎች የጥምር ጦሩ ጊዜያዊ ካምፓች ተውጣጥቶ በመጣ ከ400 የማያንስ መከላከያ እና እልቆ የለሽ አ.ሚ.ፓ. (አጥቦ አይለብሴ ሚሊሻ...አድማ ብተና እና ፓሊስ) ድብልቅ ሰራዊት ጋር በነበረው ትንቅንቅ በርካታ ጠላት ደምስሶ ተሰውቷል::

የአማራ ፋኖ በወሎ ምዕራብ ወሎ ኮር አዛዥ አርበኛ አደም አሊ ጋር ውጊያን በመምራት ላይ ሳለ ነው ኮማንዶ ተመስገን የተሰዋው:: ፊት ለፊት ሲዋጋ ቆይቶ ከበባ ሰብረው እና ጠላትን ከምሽጉ ነቅለው በማስፈርጠጥ ታላቅ ገድል እየፈፀሙ ባሉበት ቅጽበት ነው በድንገት የተመታው::

በዚህ አውደ ውጊያ ከወግዲ በኩል ከመጣው ጥምር ጦር ብቻ 30 በጥይት ቀምሶ 17ቱ ሙት ሲሆን ቀሪው ቆስሏል::

በለጋምቦ በኩልም ከዚህ ያላነሰ ቁጥር ያለው ጠላት ተደምስሶ 20ዎቹ ጊምባ ተቀብረዋል:: ከ5 ቀናት በኋላ ከትናንት በስቲያ አስከሬን ለቀማ ወደ ውጊያው ቀጠና የተጓዘው ጠላት አርሶአደሮችን አፋልጉኝ ብሎ አስገድዶ ሲፈልግ ቆይቶ የ6 ወታደሮችን እግር አግኝቷል::

በብስቁልሉ ኦፕሬሽን በድምሩ ከ60 በላይ ጠላት እንደተመታ ነው መረጃዎች የሚያሳዩት:: የአማራ ፋኖ በወሎ ምዕራብ ወሎ ኮር ቀኝ አዝማች ይታገሱ አረጋው ተወርዋሪ ክፍለ ጦር ኦርዲናንስ ኃላፊን ጨምሮ አንድ የንጉሥ ሚካኤል አሊ ክፍለ ጦር ፋኖ መቁሰሉ የተገለፀ ሲሆን ከኮማንዶ ተመስገን ሳይንቴው ጋር መስዋዕትነት የከፈለም ሳይኖር እንዳልቀረ ነው የሰማሁት::

በጥቂት መስዋዕትነት አስገራሚ የሚባል ጀብዱ ተፈፅሟል ኮማንዶ ተመስገን እንደተሰዋም አንቆጥረውም ሲሉ ነው ጓዶቹ የገለፁት:: ሞት አይፈሬው ጀግና የሳይንቴይቱ ልጅ ከአዲስ አበባ ድረስ ወደ ግንባር ከገባ ሁለት ወር አልሆነውም:: የቀኝ አዝማች ይታገሱን ደም የምንመልሰው ህዝባችን ነጻ ሲወጣ ነው ብሎ የወንድሙን ደም ሊመልስ ገብቶ የልቡን ሰርቶ ተሰውቷል:: ለቃሉ ታምኖ የወንድሙንም አደራ ተሸክሞ እስከ ሞት ድረስ በሀቅ ታግሎ አርፏል:: ይህ ወርቃማ ዕድል ነው:: የዚህ ታሪክ ባለቤት ሆኖ ስም አስሮ መሰዋት መታደል ነው እንጅ ሞት አይባልም!!

ለወዳጅ ዘመድ እና ለጓዶቹ በሙሉ መጽናናትን እመኛለሁ!! ነፍስ ይማር!!


የጎንደር ፋኖ አንድ ሆነ✊




ምዕራብ ጎጃም ከቡሬ ከተማ ወጣ ብሎ ደረቋ ላይ ሀይለኛ ጦርነት በመካሄድ ላይ ሲሆን ከቡሬ ከተማ ታንክ እዬሄደ ይገኛል አስፈላጊው ጥንቃቄ እንዲደረግ መረጃው በአስቸኳይ ይዛመት።


የጣናው መብረቅ ብርጌድ ከባህር ዳር አፍጫ ስር በምትገኘው መሸንቲ ከተማ ውስጥ ትናትን 8 ሰአት ላይ የተሰካ ኦፕሬሽን ሰርቷል::




🔥🔥የዞዝ አምባ ንጉስ ክ/ጦር አስደናቂ የደፈጣ ኦፕሬሽን🔥🔥

👉የአማራ ፋኖ በጎንደር፦ የዞዝ አምባ ንጉሥ ክ/ጦር ትንታጎች ጥር 01/2017 ዓ.ም በሁለት ግንባሮች በተጠና ደፈጣ ወራሪ ሠራዊቱ ላይ ከፍተኛ ጉዳት አድርሷል።

👉 የመጀመሪያ ግንባር ከእብናት በአራት ኦራል ተጭኖ ቋሊሳን ለመያዝ የተንቀሳቀሰን ወራሪ ሠራዊት ልዩ ቦታው ገላ ማጠቢያ የተባለ ቦታ ላይ ደፈጣ የጣሉት የዞዝ አምባ ንጉሥ ክ/ጦር፣ ተከዜ ግንባር ናደው ብርጌድ ባለ ልዩ ተልዕኮ መብረቆች አማካይነት በተወሰደ መብረቃዊ ጥቃት በርካታ ሙትና ቁስለኛውን እያዝረከረከ ፈርጥጦ ወደ እብናት ገብቷል።

👉 ሁለተኛው  ግንባር በተመሳሳይ ከእብናት በአራት ኦራል ተጭኖ ቆላ መልዛ ኒቋራ ከተማን ለመያዝ የተንቀሳቀሰን ወራሪ ሠራዊት በሌላኛዋ አግኝቸው ቢተዋ ብርጌድ በተጣለ ደፈጣ ከ20 በላይና በርካታ ቁስለኛውን እያዝረከረከ ፈርጥጦ እንደለመደው እብናት ከተማ ገብቷል።

     ኅልውናችን በተባበረ ክንዳችን!!!

የአማራ ፋኖ በጎንደር የሚዲያና ሕ/ግንኙነት መምሪያ


ወሎ ቤተ አምራ ውስጥ አስደናቂ ድል ተመዘገበ:-

በደቡብ ወሎ ዞን መቅደላ ወረዳ የአማራ ፋኖ በወሎ ምዕራብ ወሎ ኮር አማራ ሳይት መቅደላ ክፍለ ጦር ሼህ ሁሴን ጅብሪል ብርጌድ ታሪካዊ ድል አስመዝግቧል::
-
ትናንት ታህሳስ 30 ቀን 2017 ዓመተ ምህረት ከወረዳው መቀመጫ ማሻ ከተማ ወደ ኮሬብ በሲኖትራክ ሲንቀሳቀስ የነበረ አድማ ብተና ላይ በተፈፀመ ድንገተኛ ጥቃት ሲኖትራኩ ላይ ያሉት አድማ ብተናዎችን እሳት በልቷቸዋል::
-
ደምወዝ ተቀብለው ሲገሰግሱ ድስም የምትባል ቦታ ላይ ነው ጭዳ የተደረጉት:: የአማራ ሳይት መቅደላ ክፍለ ጦር ምክትል አዛዥ ፋኖ ሙሀመድ አሊ (ጭንቅየለሽ) እና የሼህ ሁሴን ጅብሪል ብርጌድ ዋና አዛዥ ፋኖ በለጠ ምትክ (ድሮን) በመሩት በዚህ ኦፕሬሽን አስደናቂ ድል ሊመዘገብ መቻሉን የአማራ ፋኖ በወሎ ምዕራብ ወሎ ኮር አማራ ሳይት መቅደላ ክፍለ ጦር ህዝብ ግንኙነት ሀላፊ ፋኖ ቃለአብ ወርቅዬ አስታውቋል::
-
በዚሁ በመቅደላ ወረዳ ውስጥ ታህሳስ 28 ቀን አቶ ኢብራሂም የተባለ ግለሰብ ከኮሬብ ወደ ማሻ ከተማ የቤተሰቡን እና የጎረቤቹን የሴፍቲኔት ገንዘብ ለመቀበል እንደመጣ መነሀሪያ ፊት ለፊት ህይወቱን በግፍ ተነጥቋል::

ይህ ግለሰብ ከፋኖ ጋር ምንም አይነት ግንኙነት የሌለው ሲሆን ከዚህ ቀደምም አንድ የባጃጅ ሾፌርን ሙዚቃ ለምን ከፈትክ ብለው ህይወቱን ተነጥቋል ተብሏል::

ጥምር ጦሩ በንፁሀን ላይ አሰቃቂ ግፍ መፈፀሙን ቀጥሏል ያለው ፋኖ ቃለአብ ይህን ግፍ የሚፈፅም ጠላት ጋር ንግግር ስለሌለን በምክክር ኮሚሽን ስም ደሴ ተሰባስቦ የሚመክር አካል ወደ እኛ ቢመጣ ቅጣታችን የከበደ እና እስከ ሞት የሚደርስ ነው ብሏል::




ፋኖ ጋዜጠኛ ወግደረስ ጤናው የአማራ ፋኖ በጎጃም የህዝብ ግንኙነት ክፍል ስራ አስፈፃሚ አባል በመሆን የቴሌቪዥን ፕሮግራም አዘጋጅና ሀላፊ በመሆን ተሹሟል!


ሰበር~ የድል ዜና

ጣርማበር፣ ደብረሲና ፣ ሸዋሮቢትና ራሳ !!

ሳምንት ያስቆጠረው የሸዋ ጠቅላይ ግዛት ዕዝ ተጋድሎ

ታህሳስ 25/2017 ዓ.ም

ከሳምንት በላይ በሸዋ ወደ ራሳ ያለ የሌለ ሀይሉን ለቃቅሞ ወደ ራሳ ለመግባት የሞከረው የምርኮኛው ብርሃኑ ጁላ ሰራዊት መውጫ ጠፍቶት በራሳ ሸለቆዎች ላይ እየረገፈ ይገኛል። በረሃብና በውሃ ጥም የተዝለፈለፈው ወራሪው ሴት ደፋሪ የአብይ አህመድ ስልጣን ጠባቂ ቅጥረኛ ሰራዊት ወደ አልሞ ተኳሾቹ ቀዬ ዘው ብሎ ገብቶ መውጫ ጠፍቶት እየተገረፈ ይገኛል።

ድሽቃን እንደክላሽ የሚተኩሱት የመከታው ማሞ ልጆች ዛሬ አድማሱን ባሰፋው አውደ ውጊያ በጣርማበር ፣ደብረሲና ሾላሜዳ ላይ በሞርተር የታገዘ ትልቅ ትንቅንቅ እያደረጉ ይገኛሉ። አርበኛ ስንታየሁ ማሞ(ራንቦ) ክፍለጦር ፤ማንበግር ንጉስ ሻለቃ ከደብረሲና ጣርማበርና ሻላሜዳ የጠላትን ሀይል እየገረፈችው ትገኛለች። በተጨማሪ የአፄ ዘረያዕቆብ ክፍለጦር ጣይቱ ብርጌድ አንድ ሻለቃ በራሳው አውደውጊያ እየተሳተፈች ነው።

በሌላ ግንባር ደጃዝማች ተሳማ አርገጤ ክፍለጦርና 7ለ70 ክፍለጦሮች በሸዋሮቢት ዙሪያ ማፉድና ገደባ የጠላትን ጦር እያረገፉት ይገኛሉ። በአውደውጊያው የጠላት ዙ-23 ከጥቅም ውጪ ሲሆን ከሸዋሮቢት አካባቢ ያለው የጠላት ሀይል መድፍ እያስወነጨፈ ይገኛል። በተመሳሳይ ገደባ ጊዮርጊስ ላይ የጠላት አንድ ኦራል ሲማረክ ከአንድ ሻለቃ በላይ ሀይል ተደምስሷል። 

ድል ለአማራ ህዝብ !!
ድል ለአማራ ፋኖ !!




"እረ አንተ ጎንደሬ፣
እንዴትስ አድርገህ ተኩሰሀት ይሆን:
አለቅን አለቅን አለ ጠላት በራዲዮን"

"አርበኛ ውባንተ ሞተ ያለው ማነው፡
ያ ምሽግ ደርማሹ ሞተ ያለው ማነው፡
ዛሬም ከጉድጓዱ እንደታጠቀ ነው"

የዛ የጦሩ ገበሬ፣ የዛ የጦሩ ጠቢብ፡ የመውዜሩ ዳኛ፣ የምሽጉ ንጉስ፣ የእርሳሱ ሎሌ የሜጀር ጄነራል ውባንተ አባተ እስትንፋኖሶች ካለፉት አራት ጀምሮ የጠላት ጦርን የእምብርክክ ሲነዱት ሰንብተዋል።

በህግ ማስከበር ስም በአማራ ሕዝብ ላይ ጦርነት ያወጀው በኦሮሞ ብልፅግና ፓርቲ የበላይነት የሚዘወረው የአገዛዝ ስርዓቱ ወታደሮች፡ " እርጎ መስሎሽ ከእርሾ ጥልቅ" እንዲሉ አበው ፋኖን አፍናለሁ ብለው በጉና ቀጠና የገቡ ቢሆንም፡ ነገር ግን በሕይወት ተርፎ መውጣት አባይን በማንኪያ ጨልፎ እንደማድረቅ ሆኖባቸው ቀርቷል።

"ወይ መድፍ ብላሽ ወይ ድሮን ብላሽ፡
ወይ ሞርተ ብላሽ ወይ ታንክ ብላሽ፡
ሲደመስሰው ፋኖ በክላሽ።

የውቤ ልጆች ጎራው እያሉ፡
የጉና አርበኞች ጎራው እያሉ፡
ጉና ሰማይ ስር የጠላትን ጦር ሲዎቁት ዋሉ" ብሏል የጠላት ጦር ተቆላልፎ ተቆላልፎ ሲወድቅ የተመለከተ ያገሬው ሰው።

ካለፉት አራት ቀናት ጀምሮ የአማራ ፋኖ በጎንደር ጉና ክ/ጦር ስር የሚገኙት ፀያይም አናብስቱ የእስቴ ደንሳ ብርጌድ አባላት እና ኃያላኑ የሜጀር ጄነራል ውባንተ አባተ ተወርዋሪ ክ/ጦር ፋኖዎች በጋራ በመሆን በጉና ቀጠና ሸንበቆች፣ ዘምባራ፣ ሾለክት፣ ለበጥ፣ ማሸንት፣ ሊባኖስ፣ አፎጠን፣ መንቆላት፣ ጥናፋ፣ ሩፋኤል፣ ገና መምቻ፣ ዘንጨፍ እና ቁስቋም በተባሉ ቦታዎች ላይ የጦር አውድማ ጥለው የጠላትን ወታደር ሲያበራዩት መሰንበታቸውን መረብ ሚዲያ ለማረጋገጥ ችሏል።

ያለፉት ቀናት በሸምበቆች ቀበሌ በተደረገ ትንቅንቅ በርካታ ቁጥር ያለው የጠላት ጦር እንደ ደረቀ የዛፍ ቅጠል የረገፈ ሲሆን፡ አርሶ አደሩ ቀብር ምሶ አፈር በማልበስ ፋታ አጥቷል ተብሏል።

በዚህ ስፍራ አሁንም በርካታ የጠላት አስከሬን በየአርሶ አደሩ ማሳ ወድቆ የሰማይ አሞራ እና የዱር አራዊት እየተራኮተበት መሆኑንም መረብ ሚዲያ ያነጋገራቸው የአከባቢው ነዋሪዎች ገልፀዋል።

በተመሣሣይ እነዚኸው ምሽግ ደርማሾቹ የአርበኛ ውባንተ አባተ ልጆች፡ ሙትና ቁስለኛን ለማንሳት በሆድ አደር ሚሊሻና አድማ ብተና መሪነት ወደ ቀጠናቸው የገባውን አንድ ኦራል እና አንድ አይሱዙ ኤፍ ኤስ አር ሙሉ የአገዛዙን ጦር ወደ አመድነት ሲቀይሩት አፍታ አልፈጀባቸውም ተብሏል።

በዚህ ስፍራ የጠላት ዐብይ አህመድ ጦር፡ በወገን ኃይል ከበባ ውስጥ ገብቶ በአፈሙዝ አለንጋ መገረፍ ሲጀምር "እባካችሁ አድኑኝ" በሚል ትጥቁን እየጣለ በየአርሶ አደሩ መኖሪያ ቤት ለመደበቅ የሚሯሯጠውን ወታደር ለተመለከተ ትዕንግር ነበር ይላሉ መረብ ሚዲያ ያነጋገራቸው የአይን እማኞች ሁንታውን ሲያስረዱ።

ደብረታቦር ከተማ ተቀምጠው ውጊያውን ሲመሩ የነበሩ የአገዛዙ የጦር መኮነኖች ወታደራቸው የፋኖ አፈሙዝ ሲሳይ ሆኖ ሲቀርባቸው ጊዜ በብስጭት "እናንተናችሁ ቀላል ነው እያላችሁ ያስበላችሁን" በሚል ቁጥራቸው በውል ያልታወቀ የወረዳና የዞን ሚሊሻ አስተባባሪዎችን መረሸናቸው ተሰምቷል።

የአገዛዙ ምንጣፍ ጎታች የጦር መኮነኖቹ በሚሊሻ አስተባባሪዎቹ ላይ የወሰዱት እርምጃ ብቻ አልበቃቸውም፡ በየቀጠናው ገብቶ የነበረው ወታደራቸውን ጤና ጣቢያዎችን እያወደመ፡ መድሃኒቶችን እየዘረፈ፡ የጤና ባለሙያዎችን እየገደለነ እና እያሰረ እንዲወጣ ማድረጋቸው ታውቋል።

በአርበኛ ባየ ቀናው በሚመራው አማራ ፋኖ በጎንደር ጉና ክ/ጦር ስር የእስቴ ደንሣ ብርጌድ ቃል አቀባዩ ፋኖ ማረው ክንዱ ከመረብ ሚዲያ ጋር ቆይታ አድርጓል።

ይከታተሉ👉



20 last posts shown.