️ ንስር አማራ🦅


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic
Category: not specified


የተቀደሰን ነገር በእግሩ ለሚረግጥ ፥ተመልሶም ያጎረሰውን እጅ ለሚናከስ ርኩስ መጫወቻ የማይሆን የነቃ ማህበረሰብ እስክንፈጥር ድረስ ብዕራችን አይነጥፍም።
አንድ አማራ ለሁሉም አማራ ፥ሁሉም አማራ ለአንድ አማራ።
💚💛❤️
እኛን በውስጥ ለማናገር @NISIREamhra2
@NISIREamhraa_bot 👈 ይችን አድራሻ ይጠቀሙ🦅
ንስር አማራ🦅
#የግፉአን_ድምፅ
t.me/NISIREamhra

Related channels  |  Similar channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Category
not specified
Statistics
Posts filter


የአማራ ፋኖ በጎጃም ጎጃም አገዉ ምድር ክፍለ ጦር ዘንገና ብርጌድ በሁለት ግንባር እየተፋለመ ይገኛል።

በዚህ ሰሃት የቲሊሊ ዘንገና ብርጌድ ፋኖ ቲሊሊ ከተማ እና አሽፋ ከተማ ላይ ትንቅንቅ እያደረገ ይገኛል። ሞት አልሞት መከራ ዉስጥ ያለዉ አራዊትም በገባያ ቀን ሞርታር በህዝቡ ላይ በመወርወር ጉዳት አድርሷል።

ወጊያዉ እንደቀጠለ ነዉ‼

©የዘንገና ብርጌድ ቃል አቀባይ አለበል አወቀ

#ትግላችን_አይሸጥም_አይለወጥም‼️
#ላንጨርስ_አልጀመርንም‼️
#ምረር_አማራ💪
#ድል_ለአማራ_ፋኖ💪
#ድል_ለአማራ_ህዝብ💪

24/05/2017 ዓ.ም

@NISIREamhra


"በብልፅግና ባለፉት ስድስት አመታት አንድም ታራሚ ቶርች (torch) አልተፈፀመበትም።"

የብልፅግና ፓርቲ ሊቀመንበር ዐብይ አህመድ😁😁

#ትግላችን_አይሸጥም_አይለወጥም‼️
#ላንጨርስ_አልጀመርንም‼️
#ምረር_አማራ💪
#ድል_ለአማራ_ፋኖ💪
#ድል_ለአማራ_ህዝብ💪

23/05/2017 ዓ.ም

@NISIREamhra


Video is unavailable for watching
Show in Telegram
🔥አርበኛ አስረስ ማረ ስለአንድነቱ የተናገረው‼️

“አንድ አማራዊ ተቋም ልንመሰርት 11ኛው ሰዓት ላይ ደርሰናል። መተዳደሪያ ደንቦችን፤ አዋጆችን፤ አርማና ስም መርጠን ጨርሰናል። በቅርቡ በአጭር ቀናት አንድነቱን እናበስራለን!”

#ትግላችን_አይሸጥም_አይለወጥም‼️
#ላንጨርስ_አልጀመርንም‼️
#ምረር_አማራ💪
#ድል_ለአማራ_ፋኖ💪
#ድል_ለአማራ_ህዝብ💪

23/05/2017 ዓ.ም

@NISIREamhra

8.1k 0 5 156 144

🔥#መረጃ_ደብረኤልያስ‼️

ዛሬም ድሉ ቀጥሏል።
ጀግኖቹ የደብረ ኤልያስ ቀስተ ደመና ብርጌድ፣የማቻክል በለይ ዘለቀ ብርጌድና የጎዛምኑ ጅበላ ሙተራ ብርጌድ ዛሬ ከቀኑ 5:00 ገደማ በደብረ ኤልያስ ከተማ በፈጸሙት የተቀናጀ ውጊያ በጠላት ላይ የተሳካ ጥቃት ፈጽመዋል።

አይኑ እያየ የእቶን እሳት በሆነችው ደብረ ኤልያስ ወረዳ ዘው ብሎ የገባው ራሱን ጥምር ጦር እያለ የሚጠራው የጠላት ሠራዊት አሁንም በጀግኖቹ ጥይት እየተገረፈ ይገኛል።

ዛሬም እርሱ ከተማውን ለቆ ወደ ገጠር ሲወጣ "እርሱ ወደ ገጠር ሲወጣ አንተ ከተማ ግባ..." በሚለው የአርበኛው መርህ መሠረት ጀግኖቹ ወደ ከተማ ገብተው በቀሪው ኃይል ላይ ውጊያ ከፍተው ክፉኛ ቀጥቅጠውታል።

በዚህ ውጊያ በርካታ ቁጥር ያለው የጠላት ጦር ሙትና ቁስለኛ ሆኗል።

ገሚሱ ጠላት በአሁኑ ሰዓት ምችግ አፋፍ ላይ ሰፍሮ ይገኛል።ይህም ያንን መከረኛ ገዳም ከተቻለ በእገረኛ ካልተቻለ በሞርተርና በዙ-23 ለመደብደብ መሆኑ ግልጽ ነው።ለዚህ ድብደባ መሳካትም የወረዳ አስተዳዳሪ ተብየው አቶ ሃብታሙ እሱባለው የመከላከያ አመራሮችን በከፍተኛ ሁኔታ እየተለማመነ መሆኑ የመረጃ ምንጮቻችን ገልጸውልናል።

በተያያዘ መረጃ ጓይ የገባው የብልጽግና ቡድን መቶ የማይሞሉ ሠዎችን ሰብስቦ ፋኖ ሌባ ነው እያሉ ሲሰብክ ቆይቶ ስብስባውን ሳይጨርሱ አብሮ የገባው አድማ በትን ተብዮ የባንዳ ስብስብ ቁልፍ ሰብሮ በየቤቱ እየገባ የነዋሪዎችን ፍላት ቲሌቪዥኖችና ሌሎችንም የቤት ቁሳቁሶች ሲዘርፍ ውሏል።ሕዝቤም የንግግራቸውንና ተግባራቸውን መቃረን ታዝቦ ስቆባቸው ተነስቷል።በዚሁ አጋጣሚ የተከበርከው የደብረ ኤልያስ ሕዝብ ሆይ በዚህ የእልህ አስጨራሽ ግብ ግብ ውስጥ እየከፈልከው ላለው ትልቅ*መስዋትነት በብርጌዳችን ስም እጅግ እናመሰግናለን።

ድል ለሕዝባችን!
ድል ለሰማዕቶቻችን!
አዲስ ( ትውልድ፣ተስፋ፣ አስተሳሰብ )

©ፋኖ ኢ/ር ዘመን ባሳዝነው የአፋጎ ቀኝ ጌታ ዮፍታሄ ንጉሴ 6ኛ ክፍለ ጦር የቀስተ ደመና ብርጌድ ፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ

#ትግላችን_አይሸጥም_አይለወጥም‼️
#ላንጨርስ_አልጀመርንም‼️
#ምረር_አማራ💪
#ድል_ለአማራ_ፋኖ💪
#ድል_ለአማራ_ህዝብ💪

23/05/2017 ዓ.ም

@NISIREamhra

9.6k 0 2 14 138

🔥የ85ኛው አገው ፈረሰኞች በዓል የዓመቱ የክብር አምባሳደር የተደረገው ሻለቃ ዝናቡ ልንገረው የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት‼️

#ትግላችን_አይሸጥም_አይለወጥም‼️
#ላንጨርስ_አልጀመርንም‼️
#ምረር_አማራ💪
#ድል_ለአማራ_ፋኖ💪
#ድል_ለአማራ_ህዝብ💪

23/05/2017 ዓ.ም

@NISIREamhra

9.8k 0 8 12 128

🔥የጅቡቲ መንግስት ድንበር ተሻግሮ በኢትዮጵያ
ላይ የድሮን ጥቃት መፈፀሙ ተሰምቷል‼️

በዚህም በአፋር ክልል ኤሊዳዓር ወረዳ ስር በምትገኘው ሲያሩ ተብላ በምትጠራው ቀበሌ ላይ የጅቡቲ መንግስት ፈፅሞታል በተባለው የድሮን ጥቃት ከ8 በላይ የሚሆኑ አርብቶ አደሮች መገደላቸውን ከአከባቢው ነዋሪዎች ያገኘው መረጃ ያመላክታል።በጥቃቱ ከተገደሉት አርብቶ አደሮች በተጨማሪ በርካቶች ቆስለው ሆስፒታል እንደሚገኙም ታዉቋል።

የጅቡቲ መንግስት ፈፅሞታል በተባለው በዚህ የድሮን ጥቃት ከተገደሉና ከቆሰሉ አርብቶ አደሮች በተጨማሪ በርካታ የቤት እንስሳትም በገፍ መገደላቸው ታውቋል።

ሀገሪቱ መንግስት አልባ ከሆነች ቆይታለች ። የሃገር ዳር ድንበር ይጠብቃል ተብሎ ተገንብቶ የነበረው ወታደርም የብልፅግናን ወንበር ለማስጠበቅ አማራ ክልል ገብቶ የአሞራ ቀለብ ሆኖ ቀርቷል። ነገም ሌላ ሀገራት በዚህ እንደሚቀጥሉ እሙን ነዉ።

አሸባሪ አገዛዝ የተቆጣጠራት የኢትዬጲያ ዜጎች በአገዛዙ ቡድንና በተጋባዥ የጎረቤት ሀገር ጨፍጫፊዎች እየተጨፈጨፉ እንዲሁም ዳር ድምበሯ ተደፍሮና መሬቷን ተነጥቃ ትገኛለች።

ይህ አሸባሪ ስርዓት ዘርና ሀይማኖት አይመርጥምና በአንድነት እንታገለው‼️

#ትግላችን_አይሸጥም_አይለወጥም‼️
#ላንጨርስ_አልጀመርንም‼️
#ምረር_አማራ💪
#ድል_ለአማራ_ፋኖ💪
#ድል_ለአማራ_ህዝብ💪

23/05/2017 ዓ.ም

@NISIREamhra

10.3k 0 11 16 200

ደጋዳሞት ብርጌድ ከውጊያ ትንቅንቅ ባሻገር ሲገለፅ!!
የአማራ ፋኖ በጎጃም 2ኛ/(ተፈራዳምጤ) ክፍለጦር ደጋዳሞት ብርጌድ የታዱ አንተነህ ሻለቃ አባላት በትናንትናው ዕለት ማለትም ጥር 22/2017ዓ/ም ከግዳጅ መልስ በደጋዳሞት ወረዳ አቅላት ወይበኝ ቀበሌ ስር የሚኙ የአቅመደካሞችን ሰብል በማጨድ ህዝባዊነታቸውን  በተግባር አሳይተዋል።

አገዛዙና የአገዛዙ ዙፋን ጠባቂ ሰራዊት የህዝባችንን ጉሮሮ ለማነቅ የአፈር ማዳበሪያ የከለከሉትን አርሶ አደር በአምላክ ቸርነት ሰብሉን አብቅሎ ለምን አጭዶ ከመረ ብለው በከባድ መሳሪያ ክምሩን በሚያቃጥሉበት በዚህ ወቅት ከህዝብ በህዝብ  ለህዘብ የወጣው ፋኖ ግን አንድያ ነፍሱን አሳልፎ ከመስጠት ጎንለጎን ማህበረሰባዊ አገልግሎቶችን በመስጠት በተደጋጋሚ ጊዜ ህዝባዊነቱን እያሳየ ይገኛል።

የአንድ ሸማቂ የመጀመሪያውም የመጨረሻውም የአሸናፊነቱ ምንጭ  ህዝባዊ ደጀንነትና ህዝባዊነት መሆኑን የተረዳው ይህ ሸማቂ ትውልድ አገዛዙ እንደሚያደርገው ለታይታና ለፕሮፖጋንዳ ፍጆታ ሳይሆን ከህዝብ ፍቅር በመነጨ አግባብ  የህዝብን ህመም በመታመም ከነፈዋሽ መድሀኒቱ አብሮ ተከስቷልና ሁሉም የዚህ ትግል ባለቤት መሰል የበጎ አድራጎት እንቅስቃሴዎችን አጠናክረው ይቀጥሉ እንላለን።

አዲስ ትውልድ፣አዲስ አስተሳሰብ፣አዲስ ተስፋ
ድል ለአማራ ፋኖ
አርበኛ ዳሞት አልኸኝ
የአማራ ፋኖ በጎጃም 2ኛ ክፍለ ጦር ደጋዳሞት ብርጌድ ህዝብ ግንኙነት!


#ትግላችን_አይሸጥም_አይለወጥም‼️
#ላንጨርስ_አልጀመርንም‼️
#ምረር_አማራ💪
#ድል_ለአማራ_ፋኖ💪
#ድል_ለአማራ_ህዝብ💪

23/05/2017 ዓ.ም

@NISIREamhra


🔥እንኳን ለ85ኛው የአገው ፈረሰኞች ማህበር ክብረ በአል በሰላም አደረሳችሁ‼️
-አርበኛ ዘመነ ካሴ

እንኮን ዲኪቲ አመትባልስ ታምፁናስ!!!
ለአንድ ህዝብ የትናንት ታሪኩ ኩራት፥የዛሬ አብሮነትና ለነገ ተስፋውና ስኬት አመታዊ ክብረ በአላት ግዙፍ ትርጉም አላቸው።

አመታዊ በአላትን በትኩረትና በምእላት ማክበር በትናንቱ ታሪኩና በዛሬ ማህበረሰባዊ አንድነቱ ጥብቀት የሚኮራ፥ ነገውን በህብረት ተስፋ የሚያደርግ ማህበረሰብ ለመፍጠር እጅግ ወሳኝ ነው።

የአገውፈረሰኞች ማህበር አመታዊ ክብረ በአል በዚህ ረገድ ሊጠቀስ የሚችልና የሚገባውም ነው። የአገው ህዝብ ኩሩ ታሪኩን ከሚያንፀባርቅቸው ውብ እሴቶቹ አንዱ ፈረሰኝነቱና ይህንም ለመዘከር በየአመቱ ጥር 23 ቀን በደማቁ የሚያከብረው የአገው ፈረሰኞች ማህበር ፌስቲቫል አንዱ ነው።

ዘንድሮም ለ 85ኛ ጊዜ በደማቁ ይከበራል።ይህን የኩራታችን ምንጭ የሆነ ፌስቲቫል ዛሬ በደማቁ የምናከብረው ነገም ለመጭው ትውልድ ጠብቀንና አዳብረን የምናስተላልፈው ውብ ውርሳችን ነው።
መልካም በአል!

እንኮን ዲኪቲ አመትባልስ ታምፁናስ!!

©የአማራ ፋኖ በጎጃም ዋና
ሰብሳቢ አርበኛ ዘመነ ካሴ

#ትግላችን_አይሸጥም_አይለወጥም‼️
#ላንጨርስ_አልጀመርንም‼️
#ምረር_አማራ💪
#ድል_ለአማራ_ፋኖ💪
#ድል_ለአማራ_ህዝብ💪

23/05/2017 ዓ.ም

@NISIREamhra


🔥እንኳን አደረሰን‼️

እንኳን ለአገው ፈረሰኞች ማሕበር የ85ኛ ዓመት የምስረታ በዓል አደረሳችሁ!

እንኳን ዴክስ ታምፁናስ፣ታምቢናስ‼️
እንኳን አደረሳችሁ ፣አደረሰን‼️

23/05/2017 ዓ.ም

@NISIREamhra


🔥#ቀስተኞቹ💪

እርግብ በመባል የምትታወቀው ጀግናዋ የቀስተ ደመና ብርጌድ ተወርዋሪ ኃይል ዛሬ ከቀኑ 5:00 ገደማ መሀል ደብረ ኤልያስ ከተማ በመግባት ሁለት ባንዳዎችን አሰናብታ ተሳፍረውባት የነበረችውን ፖትሮል ከጥቅም ውጭ ስታደርጋት የቆሰለም እንዳለ ለማወቅ ችለናል።በዚህ ድንገተኛ ኦፐሬሽን የወረዳው የብልጽግና ፓርቲ ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊ አብሮት ከነበረ አጃቢው ጋር ለትንሽ አምልጠዋል።

ጠላት በአሁኑ ሰዓት እንደ ጎባሽ በሬ አገር ምድሩን እየዞረ ዛሬ የብሔረ ብጹዓን አጼ መልክዓ ሥላሴ አንድነት ገዳም ድጋሚ ለማውደም ወደ አፋፍ ተጠግቷል።
እመኑኝ በብልጽግና ላይ የመጨረሻዋን የድል ሳቅ በቅርቡ እንስቃለን። አስራ ስድስት ሽህ ወንድሞቹ እረግፈው የቀሩበትን ቦታ ሊያይ ይሁን ወይም ራሱም ሊደገም አብረን የምናየው ይሆናል።

ዋ!! ባንዳ ዋ!!ካድሬ ዋ!! መከላከያ።

©የአፋጎ የቀኝ ጌታ ዮፍታሄ ንጉሴ 6ኛ ክፍለ ጦር ቀስተ ደመና ብርጌድ ፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ
ፋኖ ኢ/ር ዘመን ባሳዝነው

ፎቶው ለትንሽ ያመለጠው ካድሬ ነው

#ትግላችን_አይሸጥም_አይለወጥም‼️
#ላንጨርስ_አልጀመርንም‼️
#ምረር_አማራ💪
#ድል_ለአማራ_ፋኖ💪
#ድል_ለአማራ_ህዝብ💪

22/05/2017 ዓ.ም

@NISIREamhra



11 last posts shown.