🍙 ክርስቶስ አንድ አካል ነው፤ ያም አካል የማይለወጥ የእግዚአብሔር ልጅ ነው።ወልድ ሰው በሆነ ጊዜ የአምላክነት አካሉ ወይም እኔነቱ ወደ ሰውነት አካል ወይም እኔነት አልተቀየረም።እንዲሁም ሰብአዊ አካልን/እኔነትን/ አልተቀበለም።ነገር ግን የሰውነትን ባሕርይ ወይም ፍጹም ሰውነትን ወሰደ።ይሄ የሰውነት ባሕርይ በተናጠል የግል አካል አልተመሠረለትም፤ ነገር ግን በወልድ አካልነት አካሊዊ ሆነ።ከዘላለም ጀምሮ አንድ የመለኮት ባሕርይ ብቻ ይዞ አንድ አካል የነበረው የሰውነትን ባሕርይ ወሰደ፤ ስለዚህ አሁን ሁለቱም ባሕርያት አሉት።የሰውን ባሕርይ ከወሰደ በኃላ ክርስቶስ በአካሉ ወይም በእኔነቱ መለኮትነት ብቻ ሳይሆን አምላክም ሰውም ነው።ያ ማለት አሁን እርሱ ፍጹም ሰው ፍጹም አምላክ ነው።ክርስቶስ አንድ ነጠላ አካል ነው፤ አንድ እኔነት አለው።ነገር ግን አምላክን አምላክ የሚያሰኙትን ሁሉ እንዲሁም ሰውን ሰው የሚያሰኙት ሁሉ በሙላት ይዟል።አንድ እኔነት ይኑሮው እንጂ እኔነቱ በአምላክነቱ ሆነ በሰውነቱ ባሕርያት ያለ ነው።አካሉም ደግሞ የመለኮትና የሰውነት ፈቃድ አሉት።ክርስቶስ ሁለት እኔነት የሉትም።ነገር ሁለት ባሕርያት በአንድ እኔነት ተገልጠዋል።በንግግሩ የሚገለጠው የመለኮት ሕልውናው ወይም የሰውነት ሕልውናው ቢሆንም፥ ተናጋሪው ያው አንዱ ክርስቶስ ነው።ታድያ ማስተዋል ያለብን የሰውነትን አካል አልተቀበለም ማለት ወልድ ሰው በሆነ ጊዜ አዲስ እኔነትን አላገኘም ማለት ነው።ከመጀመርያ ገና በአምላክነት ይኖር ስለነበረ፤ ሰው ከሆነም በኃላ በዚያው እኔነት ቀጥሏል።ያም እኔነት መለኮታዊ እኔነት ነው።የሰውነት እኔነቱ እራሱን የሚገልጠው በመለኮትነት እኔነቱ በኩል እንጂ በሰውነቱ ተጨማሪ የሆነ ሌላ የራሱ እኔነት የለውም።የመለኮት ባሕርዩ የማይለወጥ ስለሆነ ወልድ ሰው በሆነ ጊዜ የመለኮት ባሕርዩ መሠረታዊ ለውጥ አልደረሰበትም።ስለዚህ ክርስቶስ ሁለት አካላት ወይም ሁለት እኔነቶች የሉትም ማለት ነው።ክርስቶስ የፈጸመው የደኅንነት ተግባር የአንዱ የማይነጣጠለው የክርስቶስ ተግባር ነው።ክርስቶስ ሥራውን ሁሉ ያከናወነው በሁለቱ ባሕርያቱ ነው።ክርስቶስ ሁለት ባሕርያት አሉት ስንል ፍጹም አምላክና ፍጹም ሰው ነው ማለታችን ነው፤ ከዚያም አንድ አካል ነው ስንል አምላክነቱና ሰውነቱ በአንድ አካል ወይም በአንድ እኔነት ተዋሕደዋል ማለታችን ነው።ኢየሱስ ሲጸልይ፣ ሲርበው፣ ሲጠማው፣ ሲያለቅስና ሲያዝን፣ ሲበላ ሰው መሆኑን እያስመሰለ ሳይሆን የፍጹም ሰው ባሕርይ መሆናቸውን የሚያሳዩ ናቸው።አለመገለጥም አይችሉም።እርሱ ፍጹም አምላክ መሆኑ፤ ያቀረበው መስዋአቱ ዘላለማዊና እንከን አልባ እንዲሆን አድርጎታል።
@ZoeLife123
✳️✳️ @Yezelalemhiywet✳️✳️
✳️✳️ @Yezelalemhiywet✳️✳️
@ZoeLife123
✳️✳️ @Yezelalemhiywet✳️✳️
✳️✳️ @Yezelalemhiywet✳️✳️