ኢየሱስ ክርስቶስ:-
ለሁሉ ያስባል ሁሉንም ያጠግባል
ለዕውራን ያዩ ዘንድ ብርሃንን ይሰጣቸዋል፡፡
የተዘጉ መስኮቶችን ይከፍታል ህሙማንን ይሰማቸዋል፡፡
የተደፈነችውን ጆሮ እንድትሰማ ያደርጋል፡፡
ከሰውነት የለምፅን ልብሶች ገፍፎ የስጋን መጎናፀፊያ ያለብሳል፡፡
የደረቀውን የእጅ ክንድ ያቀናል፣
የአንካሳውን እግር እንዲሄድ ያደርጋል
ነፍስን ወደ ሕዋስዋ ይመልሳታል
መንፈስንም በማደሪያዋ ያኖራታል፡፡
አለቆች ባሏቸው አጋንንት የእርያን መንጋ ያሰጥማል ከደከመችውም ሰውነት ደዌን ያርቃል፡፡
ቅዳሴ ዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ
ለሁሉ ያስባል ሁሉንም ያጠግባል
ለዕውራን ያዩ ዘንድ ብርሃንን ይሰጣቸዋል፡፡
የተዘጉ መስኮቶችን ይከፍታል ህሙማንን ይሰማቸዋል፡፡
የተደፈነችውን ጆሮ እንድትሰማ ያደርጋል፡፡
ከሰውነት የለምፅን ልብሶች ገፍፎ የስጋን መጎናፀፊያ ያለብሳል፡፡
የደረቀውን የእጅ ክንድ ያቀናል፣
የአንካሳውን እግር እንዲሄድ ያደርጋል
ነፍስን ወደ ሕዋስዋ ይመልሳታል
መንፈስንም በማደሪያዋ ያኖራታል፡፡
አለቆች ባሏቸው አጋንንት የእርያን መንጋ ያሰጥማል ከደከመችውም ሰውነት ደዌን ያርቃል፡፡
ቅዳሴ ዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ