አርምሞ ጽርአት በሌለበት
አርምሞ ጽርአት በሌለበት
በልሳነ መላእክት
የምትኖር በምስጋና በክብር
አንተ ነህ እግዚአብሔር
አዝ........
የሆንከን አንባ መጠጊያችን
መለስከን ወደ ርስታችን
ውዳሴ ቅኔ አለን ለስምህ
በዝቶልን ቸርነት ሰላምህ
ቅዱስ እግዚአብሔር
አዝ.........
በርአድ በፍርሀት ልቡና
ፍጥረቱ የሚሰጥህ ምስጋና
ሆነሀል የህይወታችን ወደብ
ስጦታህ በቃል የማይገደብ
ቅዱስ እግዚአብሔር
አዝ..............
ገናና ስምህም የተፈራ
በመአልት በሌሊት የሚጠራ
ከኛ ላይ አርቀህ ጨለማን
ሰጠኸን የሚያስደንቅ ብርሀን
ቅዱስ እግዚአብሔር
አዝ........
የፈጠርክ ሰውና መላእክትን
ሊያከብሩ ሊያወድሱ ስምህን
በሰማይ በምድርም ውስጥ ያሉ
ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ ይላሉ
ቅዱስ እግዚአብሔር
አዝ......
አርምሞ ጽርአት በሌለበት
በልሳነ መላእክት
የምትኖር በምስጋና በክብር
አንተ ነህ እግዚአብሔር
አዝ........
የሆንከን አንባ መጠጊያችን
መለስከን ወደ ርስታችን
ውዳሴ ቅኔ አለን ለስምህ
በዝቶልን ቸርነት ሰላምህ
ቅዱስ እግዚአብሔር
አዝ.........
በርአድ በፍርሀት ልቡና
ፍጥረቱ የሚሰጥህ ምስጋና
ሆነሀል የህይወታችን ወደብ
ስጦታህ በቃል የማይገደብ
ቅዱስ እግዚአብሔር
አዝ..............
ገናና ስምህም የተፈራ
በመአልት በሌሊት የሚጠራ
ከኛ ላይ አርቀህ ጨለማን
ሰጠኸን የሚያስደንቅ ብርሀን
ቅዱስ እግዚአብሔር
አዝ........
የፈጠርክ ሰውና መላእክትን
ሊያከብሩ ሊያወድሱ ስምህን
በሰማይ በምድርም ውስጥ ያሉ
ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ ይላሉ
ቅዱስ እግዚአብሔር
አዝ......