የባህር ዳር አህለሱና መሻይኾች ገፅ


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic
Category: not specified


Similar channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Category
not specified
Statistics
Posts filter


የረመዷን ምክር 05

ስለተውሒድ እንዲሁም በተውሒድ ሊኖረን ስለሚገባ አቋም የተዳሰሰበት

√እጅግ ወሳኝ_ነጥብ_የተዳሰሰበት_አጠር_ያለ_ሙሓዶራ

ሸይኽ ሀሰን ገላው ሃፊዞሁሏህ

መጠን_4.73 mb

1446_ሒ.

የባህር ዳር አህለሱና መሻይኾች ገፅ

https://t.me/alateriqilhaq

كن على بصيرة




አሏህ ከባሮቹ የተብቃቃ ነው

አሏህ ለባሮቹ በጎ ሰሪ  ፤ ከባሮቹ የማይፈልግ ፣ በራሱ የተብቃቃ ነው፤
ቸር  ፣ አሸናፊ ፣ አዛኝ የሆነ ጌታ ነው።

ከባሪያው የማይከጅል ከመሆኑ ጋር ፣ ለባሪያው በጎ ይሰራ ፣ ለባሪያው መልካምን ይሻል ፣  ከባሪያው ላይ ጉዳትን ያስወግዳል። ይህን የሚፈጽመው   ከእርሱ በሆነ እዝነትና በጎ አድራጊነት እንጅ ከባሪያው  ጥቅምን ሽቶ ፣ (የሚመጣ) ጉዳት ኖሮ ጉዳትን ከእርሱ ላይ እንዲከላከሉለት ፈልጎ አይደለም።

አሏህ ፍጡራንን የፈጠረው እርሱ አነስተኛ ሆኑ ቁጥሩን ለማብዛት አይደለም ወይም የሚዋረድ ሆኖ በእነርሱ ልቅና ለማግኘት አይደለም ወይም እርሱን ለመመገብ ፣ እርሱን ለመጥቀም አይደለም ወይም ከእርሱ ላይ ጉዳትን እንዲከላከሉለት አይደለም።

አሏህ የሚከተለውን ተናግሯል :-
وَمَا خَلَقْتُ الْجِنَّ وَالْإِنسَ إِلَّا لِيَعْبُدُونِ
مَا أُرِيدُ مِنْهُم مِّن رِّزْقٍ وَمَا أُرِيدُ أَن يُطْعِمُونِ
إِنَّ اللَّهَ هُوَ الرَّزَّاقُ ذُو الْقُوَّةِ الْمَتِينُ
"ጅንንና ሰውንም ሊግገዙኝ እንጅ ለሌላ አልፈጠርኳቸውም፡፡ ከነርሱም ምንም ሲሳይ አልፈልግም፡፡ ሊመግቡኝም አልሻም፡፡ አላህ እርሱ ሲሳይን ሰጪ የብርቱ ኀይል ባለቤት ነው፡፡"
(ዛሪያት 56-58)

አሏህ የሚከተለውን ተናግሯል :
وَقُلِ الْحَمْدُ لِلَّهِ الَّذِي لَمْ يَتَّخِذْ وَلَدًا وَلَمْ يَكُن لَّهُ شَرِيكٌ فِي الْمُلْكِ وَلَمْ يَكُن لَّهُ وَلِيٌّ مِّنَ الذُّلِّ ۖ وَكَبِّرْهُ تَكْبِيرًا
«'ምስጋና ለአላህ ለዚያ ልጅን ላልያዘው፣ ለእርሱም በንግሥናው ተጋሪ ለሌለው፣ ለእርሱም ከውርደት ረዳት ለሌለው ይገባው' በልም፡፡ ማክበርንም አክብረው፡፡»
(ኢስራእ :111)

አሏህ ወዳጆቹን የሚወደው ከእርሱ በሆነ በጎነትና  እዝነት ነው።

አሏህ የሚከተለውን ተናግሯል:-
وَاللَّهُ الْغَنِيُّ وَأَنتُمُ الْفُقَرَاءُ ۚ 
"አላህም ሐብታም ነው፡፡ እናንተም ድሆች ናችሁ፡፡"
(ሙሀመድ :38)

ፍጡራን እርስ በርስ የሚደጋገፉት ድሃ በመሆናቸው ነው። አፋጣኝ ወይም ዘግይቶ የሚገኝ ጥቅም ሽተው ነው። ጥቅምን  ታሳቢ ባያደርጉ ኖሮ አንዱ ለሌለው በጎ ባልሰራ ነበር።

በሀቂቃ ካየነው የሰው ልጅ ለሌሎች በጎ የሚሰራው ከእነርሱ ጥቅም ለማግኘት መዳረሻ መንገድን ለማመቻቸት ነው።
የሰው ልጅ  በጎ የሚሰራው በዚህ አለም የመልካም ዋጋውን ፈጥኖ ለማግኘት  ወይም ለበጎ ስራው  ለውጥ ፈልጎ ወይም ከሌላው ምስጋና እና ውዳሴን ጠብቆ ነው
ወይም በአኼራ ከአላህ ዘንድ ምንዳ ለማግኘት ፈልጎ ነው።  በዚህ ምክንያት እርሱ ለነፍሱ በጎ ይሰራል።

ይሁን እንጅ ደካማ ሳይሆን በሚጠቅመው (አሏህ በፈቀደው) ነገር ላይ መጓጓቱ እርሱን የተሟላ ያደርገዋል እንጅ የሚያስወቅሰው አይደለም።

አሏህ የሚከተለውን ተናግሯል :-

إِنْ أَحْسَنتُمْ أَحْسَنتُمْ لِأَنفُسِكُمْ ۖ
"መልካም ብትሠሩ ለነፍሶቻችሁ መልካምን ሠራችሁ፡፡"
(ኢስራእ :7)

አሏህ የሚከተለውን ተናግሯል

وَمَا تُنفِقُوا مِنْ خَيْرٍ يُوَفَّ إِلَيْكُمْ وَأَنتُمْ لَا تُظْلَمُونَ
"ከገንዘብም የምትለግሱት ሁሉ (ምንዳው) ወደናንተ ይሞላል፡፡ እናንተም አትበደሉም፡፡"
(በቀራ :272)

አሏህ በሀዲሰል ቁድስ የሚከተለውን ተናግሯል:-
(يا عبادي! إنكم لن تبلغوا نفعي فتنفعوني ، ولن تبلغوا ضري فتضروني ، يا عبادي! إنما هي أعمالكن أحصيها لكم ، ثم أوفيكم إياها ، فمن وجد خيرا فليحمد الله ، ومن وجد غير ذلك فلا يلومن إلا نفسه)
أخرجه مسلم (٢٥٧٧)
(ባሮቸ ሆይ! እናንተ እኔን መጥቀም (ብትፈልጉ) መጥቀም አትችሉም ፤ መጉዳት (ብትፈልጉ) መጉዳት አትችሉም ፤ ባሮቸ ሆይ ! እርሷ ስራችሁ ነች፣ ለእናንተም እዘግባታለሁ ፤ ከዚያም እርሷን እመነዳችኋለሁ። መልካምን ያገኘ አላህን ያመስግን ፤ ከእርሱ ውጭ ያገኘ ፣ ነፍሱን እንጅ ሌላን እንዳይወቅስ)

"ጢቡል ቁሉብ : 227-228)

https://t.me/alateriqilhaq

كن على بصيرة


የረመዷን ምክር 04

የቢድዓ ምንነት የተዳሰሰበት
በዲን ላይ የሚጨመሩ ፈጠራወች ከነገሮች ሁሉ መጥፎ/ፀያፍ መሆናቸው የተነገረበት

√ወሳኝ_ነጥብ_የተዳሰሰበት_አጠር_ያለ_ሙሓዶራ

በወንድም አቡበክር ዩሱፍ ሃፊዞሁሏህ

መጠን_4.30 mb

1446_ሒ.

የባህር ዳር አህለሱና መሻይኾች ገፅ

https://t.me/alateriqilhaq

كن على بصيرة






የረመዷን ምክር 03

(የሰለፎችን መንገድ መከተል ግድ እንደሆነ እና የቀደምቶችን መንገድ መከተል ነፃ እንደሚያወጣን ነባሩ እምነት የሚባለው የአህሉሱና የሰለፊዮች መንገድ መሆኑ የተዳሰሰበት)

√እጅግ_ወሳኝ_ነጥብ_የተዳሰሰበት_አጠር_ያለ_ሙሓዶራ

በሸይኽ ዩሱፍ አህመድ ሃፊዞሁሏህ

መጠን_6.34 mb

1446_ሒ.

የባህር ዳር አህለሱና መሻይኾች ገፅ

https://t.me/alateriqilhaq

كن على بصيرة


"ሉዙሙ አስ-ሱና ፊ ሸርሂ ኡሱል አስ-ሱና"
"የሱና መሰረቶችን በማብራራት ላይ ሱናን አጥብቆ መያዝ"


አዘጋጅ: ዶክተር ሑሰይን ሙሀመድ አስ-ስልጢ ሀፊዞሁሏህ

የሚያቀራው : ኡስታዝ ዩሱፍ አህመድ ሀፊዞሁሏህ

የሚቀራው : በባህር ዳር  ቡኻሪ መስጅድ

ክፍል 15

የኪታቡ Pdf
https://t.me/alateriqilhaq/5634

የባህር ዳር አህለሱና መሻይኾች ገፅ

https://t.me/alateriqilhaq

كن على بصيرة


የረመዷን ምክር 02

(ወደ አሏህ መመለስ እንዳለብን የተዳሰሰበት እና ይህም ወር (ረመዷን) የተውባ ወር እንደሆነ እና ለተመላሽ ባሮች አሏህ ትልቅ ሽልማት ያዘጋጀ መሆኑን የተዳሰሰበት)

√እጅግ_በጣም_ወሳኝ_ነጥብ_የተዳሰሰበት_አጠር_ያለ_ሙሓዶራ

በኡስታዝ ሰዕድ አብዱለጢፍ ሃፊዞሁሏህ

መጠን_5.10 mb

1446_ሒ.

የባህር ዳር አህለሱና መሻይኾች ገፅ

https://t.me/alateriqilhaq

كن على بصيرة






የረመዷን ምክር 01

(የፆም ህግጋቶች የተዳሰሱበት እና በፆማችን ላይ እያጋጠሙ ያሉ እክሎች የተዳሰሱበት)

#እጅግ_በጣም_ወሳኝ_ነጥብ_የተዳሰሰበት_አጠር_ያለ_ሙሓዶራ

በሸይኽ ሐሰን ገላው ሃፊዞሁሏህ

#መጠን_3.54 mb

#1446_ሒ.

የባህር ዳር አህለሱና መሻይኾች ገፅ

https://t.me/alateriqilhaq

كن على بصيرة




የጁሙዓ ኹጥባ (ምክር)

ርዕስ  ከፊል የፆም ህጎች

በሸይኽ ሀሰን ገላው ሀፊዞሁሏህ

በቡኻሪ መስጅድ

መጠን 6.20 Mb

የካቲት -21-2017

የባህር ዳር አህለሱና መሻይኾች ገፅ

https://t.me/alateriqilhaq

كن على بصيرة


የጁሙዓ ኹጥባ (ምክር)

ርዕስ  የረመዷን ወር አቀባበል

በሸይኽ ዩሱፍ አህመድ ሀፊዞሁሏህ

በሰለፊያ መስጅድ

መጠን 5.58 Mb

የካቲት -21-2017

የባህር ዳር አህለሱና መሻይኾች ገፅ

https://t.me/alateriqilhaq

كن على بصيرة




ሁለቱ ንጽህናዎች
አሏህ ﷻ በጥበቡ ወደርሱ መቃረብን በንጽህና ላይ የተመሰረተ አድርጎታል። ሰጋጅ ወደርሱ መቃረብ አይችልም ንጽህናውን ጠብቆ እንጅ። እንደዚሁ መልካም እና ንጹህ የሆነ ሰው እንጅ ጀነትን አይገባም።
ሁለቱም ንጽህናዎች ናቸው :
- የአካል ንጽህና
- የልብ ንጽህና
በዚህ ምክንያት ውዱእ ለሚያደርግ ሰው ከውዱእ መጨረሻ ላይ የሚከተለውን እንዲል ታዟል :
"አሽሀዱ አንላ ኢላሀ ኢልለሏህ  ፣ ወአሽሀዱ አንነ ሙሀመደን አብዱሁ ወረሱሉሁ ፤ አሏሁምመ ኢጅአልኒ ሚነተዋቢን ወጅአልኒ ሚነል ሙተጦሂሪን"
ትርጉም
"ከአሏህ በቀር በእውነት የሚመለክ የለም ብየ እመሰክራለሁ ፣ ሙሀመድ የአላህ መልክተኛውና አገልጋዩ ናቸው ብየ እመሰክራለሁ ፤ አሏህ ሆይ! ከተጸጻቾች አድርገኝ ፣ ከሚጥራሩትም አድርገኝ"
የልብ ንጽህና ወደ አላህ ተጸጽቶ በመመለስ ይገኛል ፤
የአካል ንጽህና ደግሞ በውሀ ይገኛል።
ሁለቱ ንጽህናዎች ከተጣመሩ  ወደ አሏህ ለመቃረብ ፣ ከፊት ለፊቱ ለመቆምና እርሱን ለማነጋገር ምቹ ሁኔታ ይፈጠራል።
"ጢቡል ቁሉብ"  ገጽ/ 170

https://t.me/alateriqilhaq

كن على بصيرة


በባህር ዳር በአህለ ሱና ማህበር ስር የሚገኙ መስጊዶች የረመዷን ወር የኢሻ ሶላት የሚሰገደው 2:15 ይሆናል።




ምናልባት ልንሞት እንችላለን

ለረመዳን የመድረስ ዋስትና የለንምና
ሁሌም እንበለው ጌታችንን اللهم بلغنا

ያ አኺ! ምን ታውቃለህ ረመዳን ነገ ሊሆን
አንተ ልትሞት ትችላለህ ምንም ዐይነት ዋስትና የለንም። ስለዚህ አላህ እንዲያደርሰን ዱዐን እናብዛ! ደጋግ ቀደምቶቻችን እኮ ለረመዳን አሏህ እንዲያደርሳቸው 6 ወራቶችን ዱዐእ ያደርጉ ነበር ይባላል 6 ወራቶችን ደግሞ የሰሩትን መልካም ስራ አላህ እንዲቀበላቸው ይለምኑታል።

ታዲያ እኛስ ከነዚህ ከዋክብቶች አንጻር
ስንታይ የት ነው ያለነው❓

ነው ረመዳንን ለማግኘት ለኛ Guarantee ተሰጥቶናል❓

ይህን የነብዩን ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም ንግግር ከአይናችን ፊት ለፊት እናድርገው። እሱም፦

"كُنْ فِي الدُّنْيَا كَأَنَّكَ غَرِيبٌ أَوْ عَابِرُ سَبِيلٍ "
በዱንያ ስትኖር ልክ እንደ እንግዳ ወይም እንደመንገደኛ ሁነህ ኑር!!

ዐብደሏህ ኢብኑ ዑመር رضي الله عنهما እንዲህ ይል ነበር፡

إِذَا أَمْسَيْتَ فَلَا تَنْتَظِرِ الصَّبَاحَ، وَإِذَا أَصْبَحْتَ فَلَا تَنْتَظِرِ الْمَسَاءَ،
ስታመሽ ንጋትን አትጠብቅ! ስታነጋ ደግሞ ምሽትን አትጠብቅ!

ሁሌም ይህ☝️ ምክር ከኛ ጋር ቢኖር ኑሮ እኮ መልካም ስራዎች ከኛ ባልተለዩ ነበር ከመጥፎ ስራዎችም በራቅነ ነበር!

ሞትን ስላስታወስክ እኮ ትሞታለህ ማለት አይደለም። አስታወስክም አላስታወስክም መሞትህ አይቀሬ ነው። ግን ማስታወሱ ላንተ ጠቃሚ ነው።

ለዚህም ሲባል እኮ ነው ነብዩና ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም እንዲህ ያሉት፦

أَكْثِرُوا ذِكْرَ هَاذِمِ اللَّذَّاتِ ". يَعْنِي الْمَوْتَ
ጥፍጥናን ቆራጭ የሆነውን (ሞትን) ማስታዎስ አብዙ!!

☝️🫵 ~ከዚህ ሀዲስ አንጻር አንተ እንዴት ነህ?

~ሞትን በብዛት እያስታወስክ ነው?

~ለረመዳን እንደምትደርስ ተነግሮሃል?

~መሟቻህን ጊዜ አውቃሃል?

ለሁሉም ጥያቄዎች መልስ አዘጋጅተሃል።
ሂሳብ በማድረግ ወደ ተግባር ለውጠሃል።
እንዲህ ካልሆነማ ወሏህ በጣም ከስረሃል።
ካሁኑ ተሎ ወደ አላህ መመለስ ይሻልሃል።


👇👇Join & Share👇👇

https://t.me/sead429

20 last posts shown.